የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በአገር አቀፍ ደረጃ የንባብ ባህል እንዲዳብር “ከመንግሥት እና ከባለድርሻ አካላት ምን ይጠበቃል?” ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠት የሚያስችል አውደ ጥናት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ሥነ - ፅሁፍና ፎክሎር ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር በትላንትናው ዕለት በብሄራዊ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መፃህፍት ኤጀንሲ አዳራሽ አውደ ጥናት አካሂዷል፡፡ በአውደ ጥናቱ ላይ አቶ ደረጀ ገብሬ (ረ/ፕ) “የንባብ ባህልን ለማዳበር የባለድርሻ አካላት ሚና” በሚል ርዕስ እንዲሁም ዶ/ር ሙሉ ሰው አስራቴ፤ “የልሳነ ብዙ የቋንቋ ትምህርትና ፖሊሲ የንባብ ባህልን ለማዳበር የሚኖረው ተግዳሮት እና ዕድል” በሚል ርዕስ የውይይት መነሻ ሃሳቦችን ማቅረባቸው ታውቋል፡፡