Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

Saturday, 01 December 2012 11:48

የሲግደን ሐይቅ

 

 

ትርጉም - ነቢይ መኮንንአሌክሳንደር ሶልዘንስቲን

ስለዚህ ሐይቅ የሚጽፍ ሰው ፈፅሞ የለም፡፡ እንደው በሹክሹክታ ይወራለታል፡፡ በአስማት እንደተሠራ መቅደስ ወደዚህ ሀይቅ የሚወስዱት መንገዶች ሁሉ ተዘግተዋል፡፡ በየአንዳንዱ መንገድ ላይ ቀጥ ያለ አግዳሚ ተጋድሟል፡፡ እንዲህ ያለ አግዳሚ ያጋጠመው ሰውም ሆነ እንስሳ ማለፍ አይችልም፡፡ መመለስ ይገባዋል፡፡ አንድ ምድራዊ ኃይል ያንን የእገዳ ምልክት አኑሯል፡፡

አንድ የአፈ-ታሪክ ንጉሥ ህዝብ እያጉረመረመና እያደመ ሲያስቸግራቸው እንዲህ ያደርጉ ነበር አሉ፡፡
“እገደል አፋፍ ላይ ትልቅ ድንኳን ጣሉ” ይሉና ያዛሉ፡፡
“ከየት እስከ የት?” ይላቸዋል ባለሟሉ፡፡
“ህዝባችንን የሚይዘውን ያህል አስፍታችሁ ትከሉት”
“የዚያን የሚያህል ድንኳን ከየት እናገኛለን ንጉሥ ሆይ?”
“ቀጣጥላችሁም ቢሆን በሰፊው ስሩልኝ ብያለሁ፤ ብያለሁ፡፡ ይሄን ይሄንን መሥራት ካልቻላችሁ ለምን ሾምኳችሁ?!” ብለው ቱግ ብለው ይቆጣሉ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አብይ ስፖንሰር የሆነለት 12ኛው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬና ነገ በሚካሄዱ ውድድሮች በድምቀት ሊካሄድ ነው፡፡ የሩጫ ድግሱ ከአዲስ አበባ 125ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ጋር በመያያዙ ታሪካዊ ሲሆን ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ሰሞኑን ለ5 ቀናት የቆየ እና እስከ 12ሺ ጎብኝዎች ያገኘ ኤክስፖ በማዘጋጀት ውድድሩን ሲያሟሙቅ ሰንብቷል፡፡ ዛሬ በጃንሜዳ ፕላን ኢንተርናሽናል ‹ሴት በመሆኔ› በሚል መፈክር ስፖንሰር ያደረገውና 3500 ህፃናትን የሚያሳትፍ የ2 ኪ.ሜ ሩጫ ይደረጋል፡፡ ነገ ደግሞ በመስቀል አደባባይ 36ሺ ተወዳዳሪዎችን የሚያሳትፈው 12ኛው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የ10 ኪ.ሜ የጐዳና ላይ ሩጫ እንደሚደረግ ሲጠበቅ ከዚሁ ውድድር በፊት ለ9ኛ ጊዜ የሚካሄደው የአካል ጉዳተኞች የዊልቼር ሽቅድምድም እንደሚኖርም ታውቋል፡፡

Saturday, 24 November 2012 13:14

የግጥም ጥግ

መለየት
ብዙ ጊዜ አጠናሁ፤
ብዙ ጊዜ ወደቅሁ፤
ሌላ ብዙ ጊዜ፣ ሌላ ብዙ ጥናት፤
ዛሬም ነገም እዛው ተመሳሳይ ስህተት፡፡
ደግሞ ሌላ ጥናት በቃላት መራቀቅ፤
እንደገና መውደቅ፤
‘ሴት’ን እና ‘ሴክስ’ን ለይቶ አለማወቅ፡፡

ብዙ የፊልም ጽሑፎች እንዳሉሽ ሰምቻለሁ “ሰምና ወርቅ”ን በቅድሚያ ለመስራት ለምን መረጥሽ?
ስትፅፍ አንዱን ጀምረህ ሳትጨርስ ሌላውን ልትጀምር ትችላለህ፡፡ አጠገብህ ያሉት ሰዎች ስክሪፕቱን አይተውት ሊወዱት ይችላሉ፡፡ የት ደረሰ ብለው ሲጨቀጭቁህ ማለቅ አለበት ብለህ ለመጨረስ ትጣደፋለህ፡፡
ወንድሞቼና እህቶቼ እያነበቡ የሙሴ (ካሳሁን ፍስሀ የተጫወተው) እንዴት ሆነ? ሴቶቹን ገፀባህርያት ለምን እንደዚህ አደረግሻቸው ሲሉኝ ለ “ሰም እና ወርቅ” ቅድሚያ ሰጠሁ፡፡
ምን ያህል ስክሪፕቶች አሉሽ?

አስቀድሜ የተከሳሽነት ድምፄን ላሰማ!
እነሆ በዛሬ ሳምንቱ የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በቁጣ ገንፍለው ድንገተኛ ክስ የመሰረቱብኝ የኬሚካል ኢንጅነሪንግ ባለሙያው ጌታሁን ሄራሞ፤ የክስ ጭብጣቸውን ለማጠናከር 130 የእንግሊዘኛ ቃላትን በመጠቀም፤ አምስት የውጪ አገራት መፃህፍትን በማጣቀስ፤ የአራት ታዋቂ ናቸው ያሉትን የውጪ ደራሲዎች ስም ጠቅሰውና የሁለት ፈላስፋዎችን ስም መርቀው ሙግትህ ትክክል አይደለም የሚል ክስ አቅርበውብኛልና የተከሰስኩበትን ምክንያት ሙሉ በሙሉ ጠንቅቄ እረዳው ዘንድ፣ የክሱ ቻርጁ ሙሉ በሙሉ በአማርኛ ተተርጉሞ እንዲቀርብልኝ አቤት እላለሁ፡፡ በመቀጠል ወደ ፍሬ ነገሩ ልመለስ፡፡

ብዙ ሴቶችን አይቻለሁ፡፡ አንዷ ከአንዷ በቁመት፣ በመልክ፣ በሰውነት ቅርጽ ቢለያዩ እንጂ በተረፈ አንድ ናቸው፡፡ ለፍቅር ስሱ ነኝ፡፡ ቶሎ እወዳለሁ፡፡ ፍቅሬን የምታበረክት ሴት ግን ማግኘት አልቻልኩም፡፡ወድጃት፣ ወዳኝ…ሙዳችን፣ ኮከባችንና ከንፈራችን ገጥሞ ባለንበት ሰዓት፣ መሳሳማችንን አቋርጣ፣ አይኗን በአይኔ ላይ እያንከባለለች “ትወደኛለህ?” ትላለች፡፡ይኸኔ ደሜ ይፈላል፡፡ አንዲት ሴት እንዲህ ካለችኝ በቃ እጠላታለሁ፡፡ አብረን መቆየት አንችልም፡፡ ወይ እኔ እሄዳለሁ፣ ወይ እሷ ትሄዳለች፡፡ እድሌ ሆኖ ይሁን አላውቅም የማገኛቸው ሴቶች ሁሉ ሄደው ሄደው “ትወደኛለህ?” ማለታቸው አይቀርም፡፡

የግራሚ ተሸላሚዋ አሜሪካዊት ዘፋኝ ፊዮና አፕል፣ ውሻዬ በሞት አፋፍ ላይ ነች በማለት የኮንሰርት ዝግጅቶቿን ሰረዘች።
በብራዚል ሊካሄድ የታሰበውን የ12 ቀን ኮንሰርት የሰረዘችው ሳምንት ብቻ ሲቀረው ነው። በፌስቡክ ለአድናቂዎቿ ባስተላለፈችው የሚያስተዛዝን መልዕክት፣ በውሻዋ የመሞቻ ሰዓት ከአጠገቧ መራቅ እንደማትፈልግ ገልፃለች። ጃኔት ብላ የሰየመቻትን ውሻ ከ10 አመት በፊት በሎሳንጀለስ እንዳገኘቻት ፊዮና ስትተርክ፣ በሌሎች ውሾች ተነካክሳና ተጎሳቁላ ነበር ብላለች።

የቫንፓየር አፈታሪክን ከዘመናችን ጋር ያስተሳሰረ፣ የፍቅርና የጀብድ ታሪክ ላይ የሚያተኩረው “ትዋይላይት”፣ በፊልም ተሰርቶ የቀረበው ከአራት አመት በፊት ነው - በመላው አለምም 390 ሚ. ዶላር ገቢ አስገኝቷል። በየአመቱ በፊልም ለእይታ የበቁት የታሪኩ ቀጣይ ክፍሎችም፤ ይበልጥ ተወዳጅነታቸው ጨመረ እንጂ አልቀነሰም። ዘንድሮም የታሪኩ አምስተኛና የመጨረሻ ክፍል ባለፈው ሳምንት አርብ በተለያዩ አገራት ሲኒማ ቤቶችን አጥለቅልቋል። በመክፈቻው እለት ገብተው ለማየት የጓጉ በርካታ ፊልም አፍቃሪዎች ሌሊቱን ወረፋ ሲጠብቁ አድረዋል።

የካቶሊክ ሀይማኖት ተከታየ በመሆናቸው በሕዝብ ተቃውሞ ከስልጣን የወረዱት አፄ ሱስንዮስ ዜና መዋእል ወደ አማርኛ ተተረጐመ፡፡ መፅሐፉን ከግእዝ ወደ አማርኛ የተረጐሙት አቶ አለሙ ኃይሌ ናቸው፡፡
በመፅሐፉ የጀርባ ሽፋን ላይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው ፕሮፌሰር ሽፈራው በቀለ እና ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም አስተያየት የሰጡ ሲሆን ፕሮፌሰር መስፍን “ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያን ገንዘብ አዋጥተው ከሚያሳትሟቸው መፃህፍት ይህ የመጀመርያው ነው” ብለዋል፡፡

Page 12 of 163