Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

ዝነኛዋ አሜሪካዊት አቀንቃኝ ቢዮንሴ ኖውልስ፤ በግል ህይወቷ ላይ ያተኮረ ልዩ ጥናታዊ ፊልም በቅርቡ እንደምትሰራ “ዘ ሆሊዉድ ሪፖርተር” አስታወቀ፡፡ እ.ኤ.አ በ2013 ዓ.ም በኤችቢኦ ጣቢያ የሚሰራጨው ፊልሙ፤ የቢዮንሴን ስብእና ግልጥልጥ አድርጎ እንደሚያሳይ ተጠቁሟል፡፡ በዚህ ጥናታዊ ፊልም ላይ ቢዮንሴ በተዋናይነት፤በዲያሬክተርነት እና በኤክዝኪዩቲቭ ፕሮዱዩሰርነት ትሰራለች ተብሏል፡፡ በታዋቂው የኤችቢኦ ጣቢያ የሚተላለፉ በርካታ ፕሮግራሞችን እንደምትከታተል የተናገረችው ቢዮንሴ፤ በዚህ ጣቢያ የሚሰራጭ ፊልም ለመስራት መብቃቷን እንደታላቅ ዕድል እንደምትቆጥረው ገልፃለች፡፡

ታዋቂዋ የላቲን አሜሪካ ድምፃዊት ሻኪራ፤ የቀድሞ ፍቅረኛዋና ማናጀሯ አንቶኒዮ ዴ ላ ሩዋ የ100 ሚሊዮን ዶላር ክስ እንደመሠረተባት ሲቢኤስ ኒውስ ዘገበ፡፡ ድምፃዊቷ በ2008 እ.ኤ.አ ላይ ላይቭ ኔሽን ከተባለ የኮንሰርት ፕሮሞተር ጋር ለ10 ዓመታት የሚቆይ የ300 ሚሊዮን ዶላር ውል እንድትፈራረም ዋናውን ሚና የተጫወትኩት እኔ ብሆንም የሚገባኝ ክፍያ አልተሰጠኝም ብሏል-ከሳሿ፡፡
አንቶኒዮ ዴ ላሩዋ በኒውዮርክ ለሚገኝ ፍርድ ቤት ባስገባው የክስ ማመልከቻ፤ ሻኪራ ከምታገኘው ትርፍ ልትከፍለኝ ቃል የገባችውን ገንዘብ ከልክላኛለች ሲል ከሷታል፡፡ በሙሉ ስሟ ሻኪራ ኢዛቤል ሜባራክ ሪፖል ተብላ የምትጠራው ኮሎምቢያዊቷ፤ የቀድሞው የአርጀንቲና ፕሬዝዳንት ልጅ ከሆነው ከዚህ ማናጀሯ ጋር ለ10 ዓመታት የዘለቀ የፍቅር ግንኙነት እንደነበራት ይታወቃል፡፡

ሰሞኑን በተካሄደው 40ኛው የአሜሪካ ሚውዚክ አዋርድ ላይ “የዓመቱ ምርጥ አርቲስት” በሚል የተሸለመው ካናዳዊው ድምፃዊ ጀስቲን ቢበር፤ በሌሎች ሁለት ዘርፎችም ለመሸለም በቅቷል፡፡ በአራት ሽልማት ዘርፎች ታጭተው የነበሩት ተፎካካሪዎቹ - ሪሃና እና ኒኪ ማናዥ ሁለት ሽልማቶችን በነፍስ ወከፍ አግኝተዋል፡፡ የዓመቱ ምርጥ አርቲስት ተብሎ ለመሸለም የበቃው የ18 አመቱ ጀስቲን ቢበር፤ ከታዋቂዎቹ ድምፃውያን ድሬክ፤ ኬቲ ፔሪ፤ ሪሃና እና ማሩን ፋይቭ ጋር ተወዳድሮ እንዳሸነፈ ታውቋል፡፡ ሌሎች ሁለት ሽልማቶቹ በ“ምርጥ ፖፕ እና ሮክ ሙዚቀኛነት” እንዲሁም “ቢልቭ” የተባለው አልበሙ “ምርጥ የሮክ እና የፖፕ አልበም” በሚል በመመረጥ ያገኛቸው ናቸው፡፡

የ“ትራንስፎርመርስ 4” ፊልም ዋና ዋና ትእይንቶች ቀረፃ በቻይና ለማከናወን እንደሚፈልግ ዲያሬክተሩ ማይክል ቤይ መግለፁን “ዘ ቢዝነስ ኢንሳይደር” አስታወቀ፡፡ ዲያሬክተር ማይክል ቤይ ፊልሙን ከታዋቂ የቻይና ፊልም ኩባንያ ጋር በመተባበር ለመስራት ፍላጎት እንዳለው ሲገልፅ የፊልሙ አከፋፋይ “ፐርማውንት ፒክቸርስ” ፊልሙ በቻይና መቀረፁ ለገበያው መሟሟቅ ከፍተኛ ድርሻ አለው በሚል ደግፎታል፡፡
“ሞሽን ፒክቸርስ አሶሴሽን ኦፍ አሜሪካ” ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው መረጃ፤ በሆሊዉድ የተሰሩ ፊልሞች የዓመት ገቢ ከፍተኛውን በማስገባት 2.3 ቢሊዮን ዶላር የሚገኝባት ጃፓን አንደኛ ስትሆን፣ ቻይና በ2 ቢሊዮን ዶላር ፤ፈረንሳይ በ2 ቢሊዮን ዶላር፣ ዩናይትድ ኪንግደም 1.77 ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም ህንድ 1.4 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በማስገኘት እስከ 5ኛ ያለውን ደረጃ ወስደዋል፡፡

Saturday, 01 December 2012 13:47

የጠንቋዩ ትዕዛዝ

“ልጅ መውለዱ ባልከፋ፤ ግን በሁለት ዓመት ውስጥ ስድስት ልጅ እንዴት ነው ልወልድ የምችለው?” አለ መሀመድ ሰይድ እንባ እየተናነቀው፡፡ የቀዬው ቃልቻ ስድስት ልጅ በሁለት ዓመት ውስጥ ወልዶ በአውልያው ካላስመረቀ ከፍ ያለ እርግማን በእሱና በቤተሰቡ ላይ እንደሚወርድበት ፈርዷል፡፡ በድፍን ሀርቡ፣ በድፍን ወሎ ተሰምቶ የማይታወቅ ፍርድ ነው ጠንቋዩ የሰጠው፡፡ እንዴት በሁለት ዓመት ውስጥ ስድስት ልጅ? ያለችው አንድ ሚስት! መሀመድ ከጓደኛው እንድሪስ ጋር ከተቀመጡበት ጉብታ ስር ወደተንጣለለችው ሀርቡ ከተማ እያየ በሀሳብ ሰጠመ፡፡ በሀርቡ ሰማይ ላይ የምታቆለቁለውን ጀንበር መጥለቅ ተከትሎ ወደየማደሪያቸው የሚያመሩት የግመል ቅጥልጥሎችን የመሰለ ሀሳብ በአእምሮው ውስጥ በሰልፍ ያልፍ ጀመር፡፡

Saturday, 01 December 2012 13:04

የጐጆ ባለሙያው!

“የሚያምር እንጨት ካየሁ አላልፍም”
ከሙያህ እንጀምራ… እስቲ የምትሰራቸውን በዝርዝር ንገረኝ…
የሀገር ባህል ቤቶች የእንጨት ስራና የኮንስትራክሽን ሰራተኛ ነኝ፡፡ የሀገር ባህል ስራ ስልሽ ጐጆ ቤቶች ሳር የሚለብሱ፣ በሳር ብቻ አይደለም በፊላ፣ በቀርከሃ እሠራለሁ፡፡ የእንጨት ስራ ስልሽ ከተለመደው ውጪ በተለይም ከባህር ዛፍ፣ ከግራር እንጨት፣ ከዋንዛና ከዝግባ የተለያየ እና ማራኪ በተለይም እስከ እነ ተፈጥሮዋቸው ሳይፈለጡ፣ ሳይጋጋጡ፣ ሳይነካኩ ቅርፃቸውን በጠበቀ መልኩ እስከ እነ ውበታቸው ዕይታ ውስጥ እንዲገቡ ማድረግ ነው የእኔ ሞያ፡፡ የራሳቸውን የተፈጥሮ ውበት በጠበቀ መልኩ ስልሽ እንጨቶቹ ለምሳሌ የሰው፣ እንስሳ፣ ዋርካ የመሳሰሉ የእንጨቶች በሃሪ የየራሳቸውን ውበትና ዲዛይን ይዘው ነው፡፡

አንድ የአሜሪካ ፖለቲከኛ በምርጫ ተወዳድሮ ውጤት እየተጠባበቀ ነው - የምርጫ ዘመቻ ዋና ማዘዣ ቢሮው ውስጥ ተቀምጦ፡፡ በዚህች ቅፅበት የሚያስበው አንድ ጉዳይ ብቻ ነበር -ምርጫውን አሸንፍ ይሆን ወይስ በተፎካካሪዬ እረታ ይሆን ? በቃ ለጊዜው እቺው ብቻ ነበረች ሃሳቡ (ከስልጣን ሌላ ምን ያስብ?) በዚህ የሃሳብ ማዕበል እየተናጠ ሳለ ነው ድንገት የቢሮው ስልክ ያንቃጨለው፡፡ ፖለቲከኛው በፍርሃት እየራደ ስልኩን አነሳና “ሃሎ” አለ፡፡ (እንዴ … ለምን አይርድ?) ምርጫውን “ተሸንፈሃል” ከተባለ እኮ አለቀለት- ሥልጣን ሱሚ ናት፡፡ ደግነቱ ግን ቀናው(ቺርስ!) ስልኩን ዘግቶ ብቻውን እንደ ህፃን ልጅ ቦረቀ (ስልጣን እኮ ዳግም መወለድ ነው!) ለአፍታ ያህል ደስታውን ለብቻው ካጣጣመ በኋላ እንደገና ወደ ስልኩ አመራ፡፡

ጅቡቲ ድንበር ልንደርስ ስንል በውሃ ጥም ምላሴ ተጣብቆ፣ እኔም እንዳልሞት ብዬ የሚቀመስ ጠብታ ውሃ ስናጣ ግዜ ሁለት ቀን ሙሉ የገዛ ሽንቴን ጠጥቻለሁ፡፡ ይሄውልህ በእጄ እንዲህ እያደረኩ! ሌሎቹም ወንዶቹም ሴቶቹም እኮ የገዛ ሽንታቸውን እንደኔው ጠጥተዋል!----
የየመን የገሃነም ጉዞ
የእኛ ሰዎች ተሰደው የሚኖሩባቸውን የተለያዩ የአለማችንን ሀገራት አንድ ሁለት እያልን ብንቆጥር የተሳካና የከሸፈ የስደኝነት ህይወት መሳ ለመሳ ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ ስኬትና ሽንፈት መሳ ለመሳ ሆነው የማይገኙባት ብቸኛይቱ ሀገር ብትኖር የመን ናት፡፡ በድሮዋ የመን የተሳካ የስደተኝነት ህይወት የመሰረቱ ኢትዮጵያውያን ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ የአሁኗ የመን ግን ከቀድሞዋ የመን በእጅጉ የተለየች ናት፡፡ የአሁኗ የመን ለስደተኞች የሚራራ አንጀት የላትም፡፡ የምድር ላይ ገሃነመ እሳት ናት፡፡

Saturday, 01 December 2012 12:36

አሣሣቢው የቲቢ በሽታ

በ2003 ዓ.ም ብቻ 154ሺ አዳዲስ የቲቢ ህሙማን ተመዝግበዋል
መድሃኒቱን የተለመደ ቲቢ ስርጭት አሣሣቢ ደረጃ ላይ ደርሷል
በዓለም እጅግ ከፍተኛ የቲቢ በሽታ ስርጭት ካለባቸው 22 አገራት ኢትዮጵያ አንዷ ስትሆን በዘጠነኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡
የቲቢ በሽታ በዓለማችን ከተከሰተ በርካታ ዓመታትን ያስቆጠረ ቢሆንም ምርመራውም ሆነ ህክምናው የተጀመረው ብዙዎችን ለህልፈተ ህይወት ከዳረገና በዓለም ዙሪያ ስርጭቱ ከተስፋፋ በኋላ እ.ኤ.አ በ1960ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ ነው፡፡ በሽታው ማይክሮ ባክቴሪየም ቲዩበርክሎስስ በሚባል ባክቴሪያ አማካኝነት የሚከሰት ሲሆን ይህ ባክቴሪያ በጋራ የምንጠቀመውን አየር መድረክ አድርጐ ወደሰው አካል ውስጥ ከገባ በኋላ ራሱን ያራባል፡፡

በወሊሶ ከተማ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እስከ 11ኛ ክፍል በቆዩበት ዘመን ለትራንስፖርት የሚጠቀሙበት ቢስክሌት ነበራቸው፡፡ ወደ አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ቢስክሌት በማከራየት ሲሰሩ ከ30 ዓመት በላይ አስቆጥረዋል፡፡ “የሥራዬ ልዩ ገጠመኝ ቢስኪሌት በተደጋጋሚ መሰረቄና ያንን ለማስመለስ ያደረግሁት ትግል ነው” የሚሉት አቶ መቻል ቦሪ፤ በህይወታቸው፣ በሥራቸውና በገጠመኞቻቸው ዙሪያ ከብርሃኑ ሰሙ ጋር አውግተዋል፡፡
ትምህርትዎትን ከ11ኛ ክፍል ለምን አቋረጡ? 
ጥላሁን ግዛው ከተገደለ ጊዜ ጀምሮ በወሊሶ፣ እንድብርና አምቦ በየዓመቱ በየትምህርት ቤቱ ሙት ዓመቱን ለማስታወስ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እናደርግ ነበር፡፡ የወጣትነት እንቅስቃሴያችን በተለይ ከኢህአፓ በኋላ ለሕይወታችን አስጊ ስለነበር ወደ አዲስ አበባ መጣሁ፡፡ በጭነት ማመላለሻ ድርጅት (ጭማድ) ውስጥ የሚሰራ ወንድም ነበረኝ፡፡ እንደመጣሁ በሱ ቤት መኖር ጀመርኩ፡፡
የሥራ ታሪክዎ ምን ይመስላል?

Page 11 of 163