Administrator

Administrator

እስላማዊ መንግስትን የማስፋፋት አላማ ይዞ የሚንቀሳቀሰው አይሲስ በቅርቡ በምዕራባውያን አገራት ዜጎች ላይ የፈጸማቸውን አሰቃቂ ግድያዎች በሚያሳዩ የቪዲዮ ምስሎች ውስጥ ጭምብል አጥልቆ አሰቃቂ ግድያዎችን ሲፈጽም የሚታየውና ጂሃዲ ጆን በሚል ሃሰተኛ መጠሪያ የሚታወቀው ግለሰብ ትክክለኛ ማንነት መታወቁን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
ግለሰቡ፣ ሞሃመድ ኢምዋዚ እንደሚባልና በትውልድ ኩዌታዊ፣ በዜግነት ደግሞ እንግሊዛዊ እንደሆነ ተረጋግጧል ያለው ዘገባው፣ ቀደም ሲል በእንግሊዝ የደህንነት አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበርም ጠቁሟል፡፡
 ግለሰቡ ባለፈው ነሐሴ ወር  በተለቀቀው የአይሲስ ቪዲዮ፣ አሜሪካዊውን ጋዜጠኛ ጄምስ ፎሌን አንገት  ሲቀላ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደታየ ያስታወሰው ዘገባው፣ በማስከተልም አሜሪካውያንና እንግሊዛውያንን በጭካኔ ሲገድል መታየቱን አስታውቋል፡፡ በዚህ ወር መጀመሪያ በተለቀቀውና ጃፓናዊው ጋዜጠኛ ኬንጂ ጎቶ ሲገደል በሚያሳየው የአይሲስ ቪዲዮ ውስጥም፣ ይሄው ግለሰብ ግድያውን ሲፈጽም እንደታየ ዘገባው አስታውቋል፡፡
ግለሰቡ የግድያ ተግባሩን ሲፈጽም ሙሉ ለሙሉ ጥቁር ልብስ ለብሶ፣ ፊቱን በጭንብል ጋርዶ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፤ አንገት ከመቅላቱ በፊትም በእንግሊዛውያን የአነጋገር ቅላጼ ምዕራባውያን መንግስታትን ያወግዝ እንደነበር ጠቁሟል፡፡
በአይሲስ ቁጥጥር ስር ቆይተው በቅርቡ የተለቀቁ የአይን እማኞች፣ ግለሰቡ በሶሪያ ከሚንቀሳቀሱ የቡድኑ እንግሊዛውያን ጂሃዲስት መሪዎች አንዱ እንደሆነ መመስከራቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡እስላማዊ መንግስትን የማስፋፋት አላማ ይዞ የሚንቀሳቀሰው አይሲስ በቅርቡ በምዕራባውያን አገራት ዜጎች ላይ የፈጸማቸውን አሰቃቂ ግድያዎች በሚያሳዩ የቪዲዮ ምስሎች ውስጥ ጭምብል አጥልቆ አሰቃቂ ግድያዎችን ሲፈጽም የሚታየውና ጂሃዲ ጆን በሚል ሃሰተኛ መጠሪያ የሚታወቀው ግለሰብ ትክክለኛ ማንነት መታወቁን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
ግለሰቡ፣ ሞሃመድ ኢምዋዚ እንደሚባልና በትውልድ ኩዌታዊ፣ በዜግነት ደግሞ እንግሊዛዊ እንደሆነ ተረጋግጧል ያለው ዘገባው፣ ቀደም ሲል በእንግሊዝ የደህንነት አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበርም ጠቁሟል፡፡
 ግለሰቡ ባለፈው ነሐሴ ወር  በተለቀቀው የአይሲስ ቪዲዮ፣ አሜሪካዊውን ጋዜጠኛ ጄምስ ፎሌን አንገት  ሲቀላ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደታየ ያስታወሰው ዘገባው፣ በማስከተልም አሜሪካውያንና እንግሊዛውያንን በጭካኔ ሲገድል መታየቱን አስታውቋል፡፡ በዚህ ወር መጀመሪያ በተለቀቀውና ጃፓናዊው ጋዜጠኛ ኬንጂ ጎቶ ሲገደል በሚያሳየው የአይሲስ ቪዲዮ ውስጥም፣ ይሄው ግለሰብ ግድያውን ሲፈጽም እንደታየ ዘገባው አስታውቋል፡፡
ግለሰቡ የግድያ ተግባሩን ሲፈጽም ሙሉ ለሙሉ ጥቁር ልብስ ለብሶ፣ ፊቱን በጭንብል ጋርዶ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፤ አንገት ከመቅላቱ በፊትም በእንግሊዛውያን የአነጋገር ቅላጼ ምዕራባውያን መንግስታትን ያወግዝ እንደነበር ጠቁሟል፡፡
በአይሲስ ቁጥጥር ስር ቆይተው በቅርቡ የተለቀቁ የአይን እማኞች፣ ግለሰቡ በሶሪያ ከሚንቀሳቀሱ የቡድኑ እንግሊዛውያን ጂሃዲስት መሪዎች አንዱ እንደሆነ መመስከራቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡

- አልቃይዳ በዋይት ሃውስ ላይ ጥቃት የመፈጸም ዕቅድ ነበረው


ኦሳማ ቢላደን በህይወት በነበሩበት ጊዜ በምዕራባውያን  አገራት የሽብር ጥቃቶችን ለመሰንዘር በተያዙ ዕቅዶች ዙሪያ ከአልቃይዳ መሪዎች ጋር የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች መገኘታቸውን  ስካይ ኒውስ ዘገበ፡፡
ከአልቃይዳ ጋር በመተባበር በእንግሊዝ የሽብር ጥቃቶችን ለመሰንዘር አሲሯል በሚል ክስ የተመሰረተበትን አቢድ ናስር የተባለ ፓኪስታናዊ ተማሪ ጉዳይ በመመርመር ላይ የሚገኘው የኒው ዮርክ ፍርድ ቤት ባለፈው ረቡዕ በዋለው ችሎት፣ ቢላደን ከቡድኑ መሪዎች ጋር የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በማስረጃነት ቀርበዋል፡፡ ደብዳቤዎቹ ቢላደን በሩስያ፣ በአሜሪካ፣ በእንግሊዝና በሌሎች የምእራቡ አለም አገራት ላይ የሽብር ጥቃቶችን ለመሰንዘር ዝግጅት ሲያደርጉ እንደነበር ያጋለጡ ሲሆን በአቦታባድ ተደብቀውበት በነበረው ግቢ ውስጥ በአሜሪካ ወታደሮች እስከተገደሉበት ጊዜ ድረስ በተለያዩ የአለም ክፍሎች ከሚኖሩ የቡድኑ የጥቃት መሪዎች ጋር የሽብር ሴራ መልዕክቶችን ይለዋወጡ እንደነበር ያረጋገጡ ናቸው ተብሏል፡፡ አልቃይዳ በዋይት ሃውስ ላይ የሽብር ጥቃት የመሰንዘር ትልቅ እቅድ እንደነበረው የሚገልጽ ደብዳቤ ከመገኘቱ በተጨማሪ፣ ቢላደን አዳዲስ የጥቃት መፈጸሚያ መንገዶችን መቀየስ እንደሚገባ ከጥቃት መሪዎቹ  ጋር ያደረጉትን ውይይት የሚጠቁሙ  ደብዳቤዎችም ተገኝተዋል፡፡

የ5ጂ ፍጥነት ከ4ጂ በ65ሺህ እጥፍ ይበልጣል
 - 100 ፊልሞችን በሶስት ሰከንድ ማውረድ ያስችላል

   የሱሬ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች በታሪክ እጅግ ፈጣኑ የተባለለትን የ5G (የአምስተኛው ትውልድ) የኢንተርኔት መረጃ ልውውጥ ቴክኖሎጂ በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ ማድረጋቸውን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
በአሁኑ ሰዓት በጥቅም ላይ ከሚውሉት የመረጃ ልውውጦች ፍጥነት በብዙ ሺህዎች እጥፍ የላቀ ነው የተባለለት የ5ጂ ፈጠራ፣ በሰከንድ አንድ ቴራ ባይት መጠን ያለው መረጃ የማስተላለፍ አቅም ያለው ነው፡፡
የዩኒቨርሲቲው የ5ጂ ፈጠራ ማዕከል ሃላፊ፤ አዲሱ ቴክኖሎጂ ከሶስት አመታት በኋላ በይፋ ተጠናቅቆ ለህዝብ እይታ እንደሚበቃ የተናገሩ ሲሆን ምርምሩን የሚመራው ኦፍኮም የተባለ ኩባንያም፤ ፈጠራው እስከ 2020 ድረስ በእንግሊዝ ተጠቃሚዎች እጅ ይገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁሟል፡፡
የቴክኖሎጂው ፍጥነት እጅግ የላቀ እንደሆነ የጠቆመው ቢቢሲ፤ የአንድ ሙሉ ፊልም መቶ እጥፍ ያህል መረጃ ያለውን ፋይል በሶስት ሰከንድ ብቻ ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) እንደሚያስችል  አስረድቷል፡፡ የ5ጂ ፍጥነት፣ በአሁኑ ሰአት ጥቅም ላይ እየዋለ ከሚገኘው 4ጂ አንጻር ሲወዳደር ከ65 ሺህ እጥፍ በላይ እንደሚበልጥም አመልክቷል፡፡

ስልጣን ከያዝን ቦኮ ሃራም በናይጀሪያ አይኖርም ብለዋል

በመጪው ወር በሚካሄደው የናይጀሪያ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ኦል ፕሮግሬሲቭስ ኮንግረስ የተባለውን  የአገሪቱ ተቃዋሚ ፓርቲ በመወከል የሚወዳደሩት የፓርቲው መሪ ሙሃሙዱ ቡሃሪ፣ ፓርቲያቸው ስልጣን ቢይዝ ቦኮ ሃራም ከተባለው አሸባሪ ቡድን ጋር ሰላማዊ ድርድር እንደማያደርግ አስታወቁ፡፡ ጽንፈኛውን ቡድን ለማጥፋት ብቸኛው አማራጭ የሃይል ጥቃት መሰንዘር ነው ያሉት ቡሃሪ፤ በስልጣን ላይ ያለው የአገሪቱ መንግስት በቡድኑ ላይ የሚያሳየውን መለሳለስ ክፉኛ ነቅፈውታል፡፡
“ቦኮ ሃራም የሰላም ፍላጎት የሌለው የጥፋት ቡድን ነው፤የሰላም ፍላጎት ቢኖረው ኖሮ 13 ሺ ናይጀሪያውያንን አይገድልም ነበር” ያሉት የቀድሞው የአገሪቱ የጦር አዛዥ ሙሃሙዱ ቡሃሪ፣ ፓርቲያቸው በምርጫው አሸንፎ ስልጣን ከያዘ፣ ቦኮ ሃራም በናይጀሪያ ግዛት ውስጥ ስንዝር መሬት እንደማይኖረው አስታውቀዋል፡፡
በሌላ በኩል የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ጉድላክ ጆናታን መንግስት፣ ሰሞኑን በአሸባሪ  ቡድኑ ላይ የተጠናከረ ዘመቻ ማወጁን ያስታወቀ  ሲሆን የተቃዋሚ ፓርቲው መሪ ግን  “ፍሬ ቢስ” ሲሉ አጣጥለውታል፡፡

የሰዓሊ ቴዎድሮስ መስፍን (ቴዲ ማን) ከ30 በላይ የካርቱን ስዕሎች የቀረቡበት “ስዕላዊ ምፀት እና ስዕላዊ ስላቅ” የተሰኘ የስዕል ትርዒት ጥር 22 ቀን 2007 ዓ.ም በጋለሪያ ቶሞካ መከፈቱ የሚታወስ ሲሆን በነገው ዕለት ከረፋዱ 4፡00 ጀምሮ በሥራዎቹ ላይ ውይይት ይካሄዳል፡፡
የጋለሪው አርት ዳይሬክተር ሰዓሊ እሸቱ ጥሩነህን ጨምሮ ሌሎች ሰዓሊያን፣ የስዕል አፍቃሪያን፣ ጋዜጠኞችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በውይይቱ ላይ እንደሚሳተፉ የጋለሪው ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ነብዩ ግርማ ተናግሯል፡፡ ውይይቱ በሰዓሊው ስራዎች፣ በአሳሳል ፍልስፍናው፣ ስዕሎቹ ለአገራችን ስነ-ጥበብ ባላቸው ፋይዳና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥን ይሆናል ተብሏል፡፡ ጋለሪያ ቶሞካ 14ኛውን የስዕል ትርዒት ከአንድ ወር በኋላ ለመክፈት በዝግጅት ላይ እንደሆነም ታውቋል፡፡

Monday, 02 March 2015 10:26

የፍቅር ጥግ

(ዝነኛ ሴቶች ስለወንዶች)
ራስህን በሌላ ሰው መነፅር እየተመለከትክ ህይወትህን መምራት አትችልም፡፡
ፔኔሎፕ ክሩዝ (ተዋናይ)
ከ10 ዓመት በፊት ከነበረው የተለወጠው አሁን ራሱን የሚያውቅ ወንድ መፈለጌ ነው፡፡ ራሱን የሚገነዘብ፣ ከራሱ ጋር የታረቀና “ቀደም ሲል የቱ ጋ እንደተሞኘው አውቃለሁ፤ ዳግም ግን አልሞኝም” ማለት የሚችል ወንድ ነው የምፈልገው፡፡
ካሜሮን ዲያዝ (ተዋናይ)
አንድ ወንድ ስከታተል እንደነበረ አልክድም፡፡ ጥሩ ጓደኛሞች ነበርን፡፡ ለተወሰነ ጊዜ ተለያየን፡፡ አንድ ቀን የሚሰራበት ምግብ ቤት ሄድኩና እዚያ መስራቱን እንደማላውቅ አስመስዬ አንተ፤ እዚህ ነው እንዴ የምትሰራው? እኔ እኮ አላውቅም ነበር” አልኩት፡፡ ይሄ በመላ ህይወቴ ከፈፀምኩት ሁሉ የላቀ ሴራ ነው፡፡ ነገር ግን ሰርቶልኛል፤ ስለዚህም አልፀፀትም፡፡
ራሄል ማክአዳምስ (ተዋናይ)
በአሁኑ ሰዓት ከወንዶች ጋር መቅበጥ ያስደስተኛል፡፡ ሴተ-ላጤ ስለሆንኩ ነፃነነቴን እያጣጣምኩ ነው፡፡ ሆኖም ስልክ ቁጥሬን አዘውትሬ አልሰጥም፡፡ የፍቅር ግንኙነት ከጀመርኩ ግን ቀልድ አላውቅም፤ ወንዱን ከራስ ጠጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ ነው የምመረምረው፡፡
ሪሃና (ዘፋኝና ተዋናይ)
ወንዶችን በተመለከተ ማር አይጥምሽ ነኝ፡፡ ከልቤ የተማረኩለት ወንድ የሚያጋጥመኝ በየአምስት ዓመቱ አንዴ ነው፡፡
ኢቫንጄሊን ሊሊ
ፍቅረኛ መፈለጉን ትቼዋለሁ፡፡ የሚስማማኝ ወንድ ባገኝ ግን አልፈልግም ማለት  አይደለም፡፡ ሆኖም አልቸኩልም፡፡ ከጓደኞቼና ከጥሩ ፊልም ጋር ቤት ውስጥ ብቀመጥ እመርጣለሁ፡፡
ኢሚሊ ቫንካምፕ

Monday, 02 March 2015 10:20

የግጥም ጥግ

በሁለት ድንጋይ
ልሰህ እንዳትጨርሰኝ -
እጅግ አልጣፈጥኩም
አንቅረህ እንዳትተፋኝ -
እሬት ብቻ አልሆንኩም
ሁሌም እባብ ሆኜ -
በልቤ አልተሳብኩም
እንደእርግብ ታምኜም -
ከታዛ አልበረርኩም
በሁለት ድንጋዮች -
አንዲት ወፍ ልመታ
አነጣጥሬያለሁ -
እየኝ በለዘብታ፡፡

ንገረኝ ሳኩራ
እንደ አገሬ አደይ ቀለመ ደማቁ
እንደ መስኩ ንጣፍ ህብረ ፍልቅልቁ
ደመናው ማለፉን ጉሙ መገፈፉን
የጨቀየው ቀዬ በብራ መግፈፉን
ትተህ ክፉ ክፉን
አውጋኝ ደግ ደጉን፡፡
ይቺ ምስኪን ነፍሴ የምስራች ናፍቃ
በ-ብ ---ዙ ተጨንቃ
ትለምንሃለች ልቧ እየደወለ
ርዳ ተርበድብዳ ሰው እንደገደለ፡፡
ጣቷ ተቆላልፎ
ሆዷ ተንሰፍስፎ
አይኗም የብሶቱን የጨው ውሃ አርግፎ
ት-ማ-ጠ-ን-ሐ-ለ-ች
እያሽቆጠቆጣት የጃፓን ክረምቱ
አል-ገፋ ብሏት ጠንቶባት በብርቱ፡፡
የአገራችን አደይ ክረምትና በጋ
እርቃለችና አትሔድም ፍለጋ
ምላሽ አትንፈጋት እባክህ ሳኩራ
እንደ ቅርንጫፍህ እሷም ተንጨባራ
ክርችው! እንዳትለው በቁሟ በድና
መቼ ነው ንገራት ጥጡስ የሚያባራው የጃፓን ክረምቱ
እንኳንስ ለመጤው ለራሱም አልሳሳ አልተፈታ ፊቱ፡፡
ወይም አስተምራት እንዳንተ ጽናቱን
አረንጓዴ ቅጠል፤ ቅርንጫፍ አርግፎ፤ ሞቶ መነሳቱን፡፡
በራሔል አሸናፊ
“እንካችሁ አደራ” ከተሰኘው የግጥም መድበሏ - የካቲት 2007 ዓ.ም)

Monday, 02 March 2015 10:03

የስኬት ጥግ

ዕድል ከሰማይ እንደ መና አይወርድም፡፡ አንተ ትፈጥረዋለህ እንጂ፡፡
ክሪስ ግሮሰሪ
በየቀኑ አንድ የሚያስፈራህን ነገር አከናውን፡
ያልታወቀ ሰው
ሁሉም ዕድገቶች እውን የሚሆኑት ከምቾት ቀጠና ውጭ ነው፡፡
ማይክል ጆን ቦባክ
ነጋችንን እውን እንዳናደርግ የሚገድበን ብቸኛው ነገር ዛሬአችን ላይ ያለን ጥርጣሬ ነው፡፡
ፍራንክሊን ዲ.ሩዥቤልት
የስኬት ምስጢር የለውም፡፡ የዝግጅት፣ ተግቶ የመስራትና ከውድቀት የመማር ውጤት ነው፡፡
ኮሊን ፖል
የስኬትን ቀመር ልሰጥህ አልችልም፡፡ የውድቀትን ቀመር ልሰጥህ ግን እችላለሁ፡- ሁሉን ሰው ለማስደሰት መሞከር ነው፡፡
ኸርበርት ባያርድ ሰዎኝ
ሰባት ጊዜ ወድቀህ በስምንተኛው ቁም፡፡
የጃፓኖች አባባል
ማለም ከቻልክ ታደርገዋለህ፡፡
ዋልት ዲዝኒ
ስኬታማ ለመሆን የስኬት ፍላጎትህ ከውድቀት ፍርሃትህ መብለጥ አለበት፡፡
ቢል ኪዝቢ
የስኬት ምስጢር ማንም የማያውቀውን አንድ ነገር ማወቅ ነው፡፡
አሪስቶትል አናሲስ
“አይሆንም” ያሉኝን ሰዎች አመሰግናቸዋለሁ። በእነሱ የተነሳ ነው ራሴ የገባሁበት፡፡
አልበርት አንስታይን
ህልሞችህን አንፅ፤ ያለዚያ ተቀጥረህ የሌሎችን ህልም ታንፃለህ፡፡
ፍራህ ግሬይ
የስኬት ጎዳና እና የውድቀት ጎዳና ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ናቸው፡፡
ኮሉን አር.ዴቪስ

Monday, 02 March 2015 09:30

የጀግንነት ጥግ

ድልን ጠብቅ፤ ድልም ታደርጋለህ፡፡
ፕሪስተን ብራድሊ
(አሜሪካዊ ቄስ)
አሸንፋለሁ ብለህ ካሰብክ ታሸንፋለህ፡፡ ድል ለማድረግ እምነት ወሳኝ ነው፡፡
ዊሊያም ሃዝሊት
(እንግሊዛዊ ወግ ፀሐፊና ሃያሲ)
በምርጫው ለተሸነፉት ሁሉ አዝናለሁ፡፡ ይሄ እኔ የማውቀው ተመክሮ አይደለም፡፡
ማርጋሬት ታቸር
(የቀድሞ የእንግሊዝ ጠ/ሚኒስትር)
 ድል ሺ አባቶች አሉት፤ ሽንፈት ግን ወላጅ አልባ ምስኪን ነው፡፡
ጆን ፊትዝገራልድ ኬኔዲ
(የአሜሪካ ፕሬዚዳንት)
የሰው ልጅ ትልቁ ድል ራሱን ድል ማድረግ ነው፡፡
ጆሃን ሔይንሪክ ፔስታሎዚ
ተመልከቱ፤ ድል አድራጊው ጀግና መጣ!
       ጡሩንባው ይነፋ፤ ከበሮው ይመታ!
ቶማስ ሞሬል
(እንግሊዛዊ የመደብ ልዩነት አቀንቃኝ)
መደበኛ ጦር ካላሸነፈ ይሸነፋል፡፡ ሽምቅ ተዋጊ ካልተሸነፈ ያሸንፋል፡፡
ሔነሪ ኪሲንጀር
(አሜሪካዊ ፖለቲከኛና ዲፕሎማት)
ሽንፈትን መቀበል የሚችል አንጀት ካለህ አታሸንፍም፡፡
ቪንስ ሎምባርዲ
(አሜሪካዊ የእግር ኳስ አሰልጣኝ)
አስቤው የሆነ አይደለም፡፡ ጀልባዬን አስጠሙብኝ፡፡
ጆን ፊትዝገራልድ ኬኒዲ
(እንዴት ጀግና ሊሆን እንደበቃ ሲጠየቅ የመለሰው)
ዓለም በደስታ ብቻ የተሞላች ብትሆን ኖሮ ጀግንነትንና ትዕግስተኛነትን አንማርም ነበር፡፡
ሔለን ከለር
(አሜሪካዊ ፀሐፊና መምህር)
ድፍረት የተስፋ ፍሬ ነው፡፡
የፊሊፒኖች አባባል
ለሰው ልጅ አንዳች ድል እስክታመጣ ድረስ ሞትን ተጠየፍ፡፡
ሆራስ ማን
(አሜሪካዊ የትምህርት ባለሙያ)

Monday, 02 March 2015 09:23

የፀሃፍት ጥግ

ኃይለኛ መፅሃፍ ለመፃፍ ኃይለኛ ጭብጥ መምረጥ አለብህ፡፡
ሔርማን ማልቪሌ
ግሩም አድርገህ እስካረምከውና እስካሻሻልከው ድረስ ትርክምርኪ ብትፅፍ ችግር የለውም፡፡
ሲ.ጄ.ቼሪ
ታሪኩ ረዥም መሆን ስላለበት አይደለም፡፡ አጭር ለማድረግ ረዥም ጊዜ ስለሚወስድ ነው፡፡
ሔነሪ ዴቪድ ቶርዩ
በህይወትህ ውስጥ ሌሎች ነገሮች ካሉህ - ቤተሰብ፣ ጓደኞች፣ ውጤታማ የሥራ ቀን - እኒህ ሁሉ ከምትፅፈው ጋር መስተጋብር በመፍጠር ድምር ውጤቱ እጅግ የበለፀገ ይሆናል፡፡
ዴቪድ ብሪን
በእኔ ልምድ እንዳየሁት፣ ታሪኩን አንዴ ከፃፉ በኋላ መግቢያውንና መጨረሻውን ሰርዞ ማውጣት ያስፈልጋል፡፡ እኛ ደራሲያን አብዛኞቹን ውሸቶችቻችንን የምንጨምረው መግቢያውና መዝጊያው ላይ ነው፡፡
አንቶን ቼኾቭ
እስካሁን ስኬታማ የሆንኩት ምናልባት ሁልጊዜም ስለድርሰት አፃፃፍ ምንም እንደማላውቅ በመገንዘቤና ማራኪ ታሪክን በሚያዝናና መንገድ ለመተረክ በመሞከሬ ብቻ ነው፡፡
ኢድጋር ራይስ ቡሮውስ
መጀመሪያ መሪ ገፀባሪህ ምን እንደሚፈልግ እወቅ፤ ከዚያ ዝም ብለህ እሱን ተከተለው!
ሬይ ብራድበሪ
ፀሐፊ የሚሰራበት አብዛኛው መሰረታዊ ጥሬ ነገር የሚገኘው ከ15 ዓመት ዕድሜ በፊት ነው፡፡
ዊላ ካተር
አዝናለሁ፤ የሳይንስ ልብወለድ ፀሃፊዎች ከምር ምንም ነገር አያውቁም፡፡
ፊሊፕ ኬ.ዲክ
በግጥም ውስጥ ገንዘብ የለም፤ በገንዘብም ውስጥ ግን ግጥም የለም፡፡
ሮበርት ግሬቭስ
ሰዎች ጥሩ ፅሁፍ ማግኘት አይገባቸውም፤ በመጥፎው ሲበዛ ደስተኞች ናቸው፡፡
ራልፍ ዋልዶ ኢመርሰን
ለዓመታት ምንም ሥራ ሳልጨርስ ነው የቆየሁት፡፡ ምክንያቱም አንድ ነገር ጨርሰህ ስታወጣ ትችት አይቀርልህም፡፡
ኢሪካ ጆንግ
ሌሎች ካንተ መስማት ስለሚፈልጉት ነገር ለማሰብ አትሞክር፤ አንተ ማለት ስላለብህ ጉዳይ ብቻ አስብ፡፡ እሱ ነው አንተ መስጠት ያለብህ አንድና ብቸኛ ነገር፡፡
ባርባራ ኪንግሶልቨር