Administrator

Administrator

በደራሲ ለማ ደገፋ የተፃፉት “ከመሩ አይቀር”፣ “ካደጉ አይቀር”፣ “ጂሩፍ ጂሬኛ” እና “የህይወት ውቅር” መፃሕፍት ዛሬ ረፋድ ላይ በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል እንደሚመረቁ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር አስታወቀ፡፡ “ካደጉ አይቀር” የተሰኘው ባለ 220 ገፅ መጽሐፍ የሰውን አዕምሮ በማልማት የሚገኝ ትሩፋት ላይ የሚያተኩር ሲሆን “ከመሩ አይቀር” የአመራርን ምንነት፣ የመሪን ማንነትና የመሪ ተግባራትን በማንሳት ትንታኔ ይሰጣል ተብሏል፡፡ መጽሀፉ 145 ገፆች እንዳሉትም ታውቋል፡፡ “የህይወት ውቅር” የተሰኘው የለማ ደገፋ ሶስተኛ ተመራቂ መጽሐፍ፤ 316 ገፆች ያሉት ሲሆን ስለመንፈሳዊ ህይወት የሚገደው የትኛውም ሰው የሚማርበትና መጽሐፍ ቅዱስን መሰረት በማድረግ የተሰናዳ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ “ጂሩፍ ጂሬኛ” የተሰኘው መጽሐፍ 367 ገፆች እንዳሉትም የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

በደራሲ ገስጥ ተጫኔ እና በቀድሞው የኢትዮጵያ ምድር ጦር ሰራዊት ወታደሮችና ሲቪል ማህበራት ትብብር የተዘጋጀው “የቀድሞው ጦር” የተሰኘ የታሪክ መፅሐፍ ዛሬ ይመረቃል፡፡ የመጽሀፍ ምርቃቱ ዛሬ ጠዋት በዮርዳኖስ ሆቴል የሚከናወን ሲሆን 747 ገፆች እንዳሉትና በ250 ብር ለገበያ እንደቀረበ ደራሲ ገስጥ ተጫኔ ተናግረዋል፡፡ “የቀድሞው ጦር” ለደራሲው ዘጠነኛ መፅሀፋቸው ሲሆን ከዚህ በፊት “የናቅፋው ደብዳቤ”፣ “እናት አገር”፣ “የፍቅር ቃንዛ”፣ “ነበር” ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለት፣ የማክዳ ንውዘትና ሌሎችንም ለአንባቢያን አድርሰዋል፡፡

“የሎሚ ሽታ” ፊልም ፕሮዱዩሰር የሆነው ማቭሪክ ፕሮሞሽን፤ ከኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ጋር በመሆን በኢቴቪ 3 “ማቭሪክ ፊልሞች የኢትዮጵያ” የተሰኘ የአማርኛ ፊልሞች ብቻ የሚታዩበት ፕሮግራም ጀመረ፡፡
“ፊደል አዳኝ” በሚለው ፊልም ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ የጀመረው ፕሮግራሙ፤ በየሳምንቱ ቅዳሜ ከ4፡30 እስከ 6፡30 የሚተላለፍ ሲሆን ሰኞ በተመሳሳይ ሰዓት በድጋሚ ይቀርባል፡፡ የማቭሪክ ፕሮሞሽን ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፌቨን ታደሰ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ ከዚህ ቀደም የውጭ ሃገር ፊልሞች የሚታዩበትን “ታላቁ ፊልም”ን መነሻ ያደረገው ፕሮግራማቸው፤ በሦስት ወር ጊዜ ውስጥ 10 ያህል የአማርኛ ፊልሞችን ካቀረበ በኋላ ባለሙያዎች በሚሰጡት የግምገማ ውጤት መሰረት አሸናፊው ፊልም ይሸለማል። በፕሮግራሙ የሚቀርቡ ሁሉም ፊልሞች፣ የሲኒማ ቤት የዕይታ ጊዜያቸውን ጨርሰው የወረዱ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በሸንቁጥ አየለ የተጻፈው “ህቡዕ ጣት” የተሰኘ ልቦለድ መፅሀፍ ለንባብ በቃ፡፡ ሃሳቡን በማብላላት እና የወቅቱን ሁኔታ ለማገናዘብ ረዘም ያለ ጊዜ የወሰደው መፅሀፉ፤ 206 ገፆች ያሉት ሲሆን በአህጉራዊና አገራዊ ጉዳይ ላይ የሚያጠነጥን እንደሆነና በተለይም የኢትዮጵያን ውስጣዊ ልዩነት በዙሪያዋ ያሉ ጠላቶቿ እንደ መሳሪያ በመጠቀም የራሳቸውን አላማ ሊያሳኩ የሚታትሩበትን ሁኔታ ያስቃኛል ተብሏል፡፡ በ45 ብር ለገበያ የቀረበው መፅሀፉ፤ የደራሲው ሁለተኛ ሥራ ሲሆን ከዚህ ቀደም “የተስፋ ክንፍ” የተሰኘ መፅሐፍ እና መቼቱን ባህርዳር ያደረገ “ማዕበል” የተሰኘ ፊልም በመፃፍና በመተወን ለእይታ አብቅቷል፡፡

ሚዩዚክ ሜይ ደይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ ባሳተመው “የኮሌጅ ቀን ግጥሞች” መጽሓፍ ላይ ነገ ከቀኑ 8 ሰዓት ውይይት ሊያደርግበት መሆኑን አስታወቀ፡፡ ሬድዮ ፋና አካባቢ በሚገኘው ብሔራዊ ቤተ መፃሕፍት የሚካሄደውን የሦሥት ሰዓታት ሥነጽሑፋዊ ውይይት የመኘሻ ሃሳብ በማቅረብ የሚመሩት የሥነጽሑፍ ባለሙያው አቶ ገዛኸኝ ፀጋው ናቸው፡፡

          የዋልያዎቹን  ዋና አሰልጣኝ ለመቅጠር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የተከተለው የአሰራር ሂደት ከዓለም አቀፍ ልምዶች አንፃር እንደዘገየ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በብዙ የዓለም አገራት የብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኞች ቅጥር ቢያንስ በ4 ቢበዛ በ5 ሳምንታት ውስጥ የሚፈፀም ቢሆንም ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የሚሆን ዋና አሰልጣኝ አፈላልጎ ለመቅጠር እስካሁን 8 ሳምንታት ቢያልፉም ሂደቱ አልተጠናቀቀም፡፡ የእግር ኳስ ፌደሬሽኑ ለዋና አሰልጣኙ ቅጥር  ካወጣው ማስታወቂያ  በኋላ ለሁለት ሳምንት   ምዝገባ ተካሂዶ ከመላው ዓለም 27 አሰልጣኞች ያመለከቱ ሲሆን የስም ዝርዝራቸውና ዜግነታቸው ከሳምንት በፊት ታውቋል፡፡ የእግር ኳስ ፌደሬሽኑ በመስፈርቶቹ 27ቱን አሰልጣኞች በማወዳደር ሲሰራ 1 ሳምንት ያለፈው ሲሆን የመጨረሻ እጩዎችን  ማንነትና ብዛታቸውን አልገለፀም፡፡  የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን የሚረከበው አዲሱ አሰልጣኝ መቼ  እንደሚታወቅ ፤  የቅጥሩ  ውል እንዴት እና መቼ እንደሚፈፀም፤ ለምን ያህል ግዜ በሃላፊነቱ እንደሚቆይ፤ ምን ያህል ወርሃዊ ደሞዝ እንደሚከፈለውና ፌደሬሽኑ ክፍያውን እንዴት ሊከፍል እንዳሰበም በይፋ የታወቀ ነገር የለም፡፡
የፌደሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት ከሳምንት በፊት ለመገናኛ ብዙሃናት በላከው መረጃ ለማወቅ እንደተቻለው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ለማሰልጠን ፍላጎት ያሳዩ አሰልጣኞች ከመላው ዓለም ከሚገኙ 15 አገራት የተሰባሰቡ ናቸው ፡፡  ከፈረንሳይ፣ ከጀርመን፣ ከቤልጅዬም፣ከቱርክ፣ ከቦስኒያ፣ ከስፔን እና ከቡልጋርያ ከእያንዳንዳቸው አንድ አሰልጣኝ፤ ከጣሊያን፣ከኢትዮጵያ፣ ከስዊድን፣ ከሆላንድ፣ ከሰርቢያ፣ ከፖርቱጋል፣ ከብራዚል እና ከሮማኒያ ከእያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት አሰልጣኞች እንዲሁም ከአርጀንቲና ሶስት አሰልጣኞች አመልክተዋል፡፡ እነዚህ አመልካች 27  አሰልጣኞች  በቅጥሩ ለመወዳደር ለፌደሬሽኑ ያስገቡት የስራ ልምድ እና ብቃትን በዝርዝር ባይገለፅም በእግር ኳስ ዙርያ መረጃ በሚገኝባቸው ድረገፆች ስለ ስራ ታሪካቸው ብዙ እውቅና ያላቸው ገሚሱ ናቸው፡፡  ስለ አሰልጣኞቹ መረጃ ማግኘት የተቻለው አንዳንዶቹ በኢትዮጵያ ከመስራታቸው በተያያዘ፤ አንዳንዶቹ በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በክለብ እና በብሄራዊ ቡድን ደረጃ ስላላቸው የስራ ልምድ በተለያዩ ድረገፆች ግለታሪካቸው ተፅፎ በመገኘቱ ነው፡፡  ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ክለቦችን በማሰልጠን ልምድ ኖሯቸው ለዋናው ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝነት ማመልከቻ ያስገቡት የደደደቢት አሰልጣኝ የነበሩት የቱርኩ ሜሜት ታይፉን እና አሁን የመብራት ኃይል ክለብ አሰልጣኝ ሆነው የሚሰሩት የቡልጋርያው ሎርዳን ስቶይኮች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን አሰልጥነው የሚያውቁት እና በድጋሚ ቡድኑን ለመረከብ ያመለከቱት ደግሞ የጣሊያኑ ዲያጎ ጋርዚያቶ እና የቤልጅዬሙ ቶም ሴንትፌይት ናቸው፡፡ ቤልጅማዊው ቶም ሴንትፌይት ከአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በፊት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ቅጥር ሳይፈፀምላቸው ለሙከራ እንዳሰለጠኑ የሚታወስ ሲሆን አሁን ብሄራዊ ቡድኑን ለመረከብ ከሁሉም ቀድመው ፍላጎታቸውን በሱፕር ስፖርት በመግለፅ የሚጠቀሱ ሆነዋል፡፡
የፌዴሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት መግለጫ  እንዳመለከተው የቅጥር ማመልከቻቸውን ካቀረቡት 27 እጩ አሰልጣኞች መካከል ኢትዮጵያዊያን የሆኑት ሁለት ብቻ ናቸው፡፡ የመጀመርያው ከ3 የውድድር ዘመናት  በፊት በኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ አሰልጣኝነት  የፕሪሚዬር ሊግ ሻምፒዮን ለመሆን የበቃው እና አሁን በሱዳኑ ክለብ አልሃሊ ሼንዲ በረዳት አሰልጣኝነት በመስራት ላይ የሚገኘው ውበቱ አባተ ነው፡፡ ሌላኛው ደግሞ አስቀድሞ በስኮትላንዳዊው ኢፌም ኦኑራ የዋና አሰልጣኝነት ዘመን  የእግር ኳስ ፌደሬሽኑ የፉትቦል ዲያሬክተር ሆኖ የሰራውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የአሰልጣኝነት ትምህርት የተከታተለው ዮሃንስ ተሰማ ናቸው፡፡  በአውሮፓ ታዋቂ ክለቦች ተሰልፈው ውጤታማ ከመሆን አልፈው በአውሮፓ፣ በአፍሪካና፣ በእስያ የሚገኙ ብሔራዊና ወጣት ቡድኖችን እንዲሁም ክለቦችን በማሰልጠን ለሻምፒዮንነት ክብር የበቁ ሙያተኞች  እንዳመለከቱ የገለፀው የፌደሬሽኑ ህዝብ ግንኙነት ክፍል ፤ ብሄራዊ ቡድኑን ተረክቦ ለውጤት ለማብቃት ያላቸውን ፍላጎት በተለያያ መንገድ መግለፃቸው የሚያበረታታ ነው ብሏል፡፡ ከእጩ አሰልጣኞቹ መካከል ከ30 ዓመታት በላይ የማሰልጠን ልምድ ያላቸው፤ በዓለም አቀፍ ውድድሮች አመርቂ ውጤት ያስመዘገቡ እንደሚገኙበት የተገለፀ ሲሆን የጥቂቶቹ የትምህርት ዝግጅት በዲፕሎማ ከመወሰኑ በስተቀር አብዛኞቹ ከመጀመሪያ ዲግሪ በላይ ያላቸው፤ በአውሮፓው እግር ኳስ ማህበር የመጀመሪያ ደረጃ የአሰልጣኝነት ብቃት ማረጋገጫ የያዙና የፕሮፌሰርና የኢንስትራክተርነት ማዕረግ የተሰጣቸው ሙያተኞች መሆናቸው ተመልክቷል፡፡  
የእግር ኳስ ፌደሬሽን ብሄራዊ ቡድኑን  ባለፈው 2 ዓመት ከ6 ወር በዋና አሰልጣኝነት የመሩትን ሰውነት ቢሻው  በተሻለ ለመተካትና ለውጥ ለመፍጠር በሚል ካሰናበተ ሁለት ወር ቢሆነውም በምትክነት ለመቀጠር ማመልከቻ ካስገቡት 27 አሰልጣኞች በስራ ልምዳቸው አለመሻላቸውን ለመረዳት አያዳግትም፡፡ በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ይመራ የነበረው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን  ከ31 ዓመታት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ለአፍሪካ ዋንጫ ያለፈ፤ ለ20ኛው ዓለም ዋንጫ ለማለፍ ለሚደረገው የመጨረሻ ማጣርያ ምእራፍ ለመገባት ከበቁ 10 የአፍሪካ ብሄራዊ ቡድኖች አንዱ ለመሆን የበቃ፤ በአፍሪካ አገራት ሻምፒዮንሺፕ ወይም ቻን ውድድር በታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ የተሳተፈ፤ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን ከዓመቱ ምርጥ ሶስት ብሄራዊ ቡድኖች አንዱ እንደሆነ ይታወቃል፡፡  
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን በሃላፊነት ለመረከብ ካመለከቱት 27ቱ አሰልጣኞች መካከል ስፖርት አድማስ የተወሰኑትን ለማስተዋወቅ ከዚህ በታች ያለውን አጭር መግለጫ አቅርቧል፡፡ እነዚህን አስር 10 አሰልጣኞች ለስፖርት አፍቃሪው ማስተዋወቅ የተቻለው ስለባለሙያዎቹ የሚገልፁ በቂ መረጃዎችን በተለያዩ ድረገፆች  በማፈላለግ ማግኘት ስለተቻለ ነው፡፡


ፋቢዮ ሎፔዝ የ50 ዓመት ጣሊያናዊ ናቸው። በትልልቆቹ የጣሊያን ሴሪኤ ክለቦች አትላንታና ፌዬሬንቲና በአማካሪነት አገልግለዋል፡፡ ከ2007 እ.ኤ.አ ጀምሮ ለ6 የውድድር ዘመናት ከ6 በላይ የዝቅተኛ ሊግ ክለቦችን ያሰለጠኑ ሲሆን በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ብዙም ልምድ የላቸውም፡፡


ሃንስ ሚሸል እድሜያቸው 49  ሲሆን በዜግነታቸው ጀርመናዊ ናቸው፡፡ በተጨዋችነት ዘመናቸው ግብ ጠባቂ ነበሩ፡፡ ከ2001 እ.ኤ.አ ጀምሮ ወደ ማሰልጠን ስራ ገብተዋል፡፡ በአሰልጣኝነት ስራ ዘመናቸው በቻይና ሀ-20 ቡድን ረዳት አሰልጣኝ፣ ከ2007 እ.ኤ.አ ጀምሮ ለ3 ዓመት በሩዋንዳ  እግር ኳስ ፌደሬሽን የቴክኒክ ዲያሬክተር፣ በ2011 የፊልፒንስ ሀ-25 ብሔራዊ ቡድን ረዳት አሰልጣኝ ሆነው ከተቀጠሩ በኋላ አድገው ባለፉት 3 ዓመታት ደግሞ የዋናው ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ነበሩ፡፡ በስፖርት ሳይንስና በማኔጅመንት ባችለር ዲግሪ ያላቸው ሲሆን በታላላቆቹ የዓለማችን ክለቦች ሪያል ማድሪድ፣ አርሰናል፣ ካይዘስላውተርን፤ ሪቨር ፕሌት ሌሎችም  በአሰልጣኝነት የስራ ልምምድ በመስራት አስደናቂ ልምድ አላቸው፡፡



ዲያጐ ጋርዚያቶ በትውልድ ፈረንሳዊ ቢሆኑም በዜግነት ጣሊያናዊ ናቸው፡፡ አሁን የ64 ዓመት አዛውንት የሆኑት እኝህ አሰልጣኝ በተጨዋችነት ዘመናቸው የተከላካይ መስመር ተሰላፊ ነበሩ፡፡ ከ1984 እ.ኤ.አ ጀምሮ በአሰልጣኝነት ማገልገል ሲጀምሩ የፈረንሳይ ዝቅተኛ ሊግ ክለቦችን ሲያሰለጥኑ ቆይተው ትልቁን ኃላፊነት የተረከቡት በ2001 እ.ኤ.አ ላይ የኢትዮጵያ ሀ 20 ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው ሲመደቡ ነበር። በዚሁ ጊዜም የኢትዮጵያን ወጣት ቡድን በአርጀንቲና ለተደረገው 14ኛው የዓለም ወጣቶች ዋንጫ እንዲሳተፍ አብቅተዋል። የኢትዮጵያ ሀ-20 ቡድን ዋና አሰልጣኝነት ከለቀቁ በኋላ በተለያዩ የአፍሪካ አገራት በክለብ ደረጃ ሲሰሩ ቆይተው በ2007 እ.ኤ.አ ላይ የቶጐ ብሔራዊ ቡድን ተረክበው ነበር፡፡ በቶጎ አሰልጣኝነት የቆዩት ግን ለ2 ወራት የስራ ጊዜ ነበር፡፡ በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ ትልቅ ውጤት በማስመዝገብ የተደነቁ ሲሆን ለሁለት ጊዜያት ያሰለጠኑትን የዲ ሪፖብሊክ ኮንጎውን ቲፒ ማዜምቤ  በ2009 እ.ኤ.አ የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ እንዲያሸንፍ አድርገዋል፡፡ በ2012 እ.ኤ.አ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ኢትዮትጵያ ተመልሰው በነበረ ጊዜ ዋና ብሔራዊ ቡድኑን በሃላፊነት ቢይዙም በአወዛጋቢ ሁኔታዎች ቢይዙም ከ2 ወራት በኋላ ተሰናብተዋል፡፡



ኤርኒስት ብራንድተስ የ58 ዓመቱ ሆላንዳዊ በተጨዋችነት ዘመናቸው የተከላካይ መስመር ተሰላፊ ነበሩ፡፡ በሆላንድ ብሔራዊ ቡድን ከ1977 -85 እኤአ በመጫወት ልምድ ከማግኘታቸውም በላይ በ1978 እ.ኤ.አ ላይ አርጀንቲና ባስተናገደችው ዓለም ዋንጫ ለመጫወት የበቁ ናቸው፡፡ ከ1993 እ.ኤ.አ ወዲህ በአሰልጣኝነት ማገልገል የጀመሩ ሲሆን በተለይ በትልቁ የሆላንድ ክለብ ፒኤስቪ አይንድሆቨን በረዳት አሰልጣኝነት ለ9 ዓመታት ሰርተዋል፡፡ በአፍሪካ ደረጃ የተወሰነ የስራ ልምድ ያላቸው ሲሆን ለ2 ዓመታት የሩዋንዳውን ክለብ ኤፒአር ካሰለጠኑ በኋላ ባለፈው ዓመት ደግሞ የታንዛኒያው ክለብ ያንግ አፍሪካንስ አሰልጥነው ነበር፡፡


ዞራን ፍሊፖቪች የ69 ዓመቱ ፖርቱጋላዊ አሰልጣኝ ናቸው፡፡ በተጨዋችነት ዘመናቸው ከሚጠቀስ ታሪካቸው ከ1970-78 በዩጎዝላቪያ ብሄራዊ ቡድን የአጥቂ መስመር ተሰላፊ ሆነው ማሳለፋቸው ነው። በአሰልጣኝነት ስራ የጀመሩት በ1988 እ.ኤ.አ ጀምሮ ሲሆን ለ2 ዓመት የፖርቱጋሊ ትልቅ ክለብ ቤነፊካ አሰልጣኝ ሆነው ከመስራታቸው በላይ በ1999 እኤአ በጣሊያኑ ክለብ ሳምፕዶርያም አገልግለዋል።  ከዚያም ተጫውተው ወዳሳለፉበት ታዋቂው ክለብ ስታር ቤልግሬድ በመመለስ ለ3 ዓመት በአሰልጣኝነት አገልግለው በ2007 እ.ኤ.አ  የሞንቴኔግሮ ቡድንን በመምራት  ለ2 ዓመት አገልገለው ከዚያ ወዲህ  ስራፈት ናቸው፡፡

ጐራን ስቴቫኖቪች የ47 ዓመቱ ሰርቢያዊ በተጨዋችነት ዘመናቸው የአማካይ መስመር ተሰላፊ ነበሩ፡፡ ከ1983 ጀምሮ ለስምንት አታመት ለፓርቴዝያን ቤልግሬድ የተጫወቱ ሲሆን በ1985 እ.ኤ.አ የዩጐዝላቪያ ብሔራዊ ቡድን አባል ነበሩ፡፡ ከ2001 እ.ኤ.አ ወዲህ በአሰልጣኝነት መስራት ጀምረው ከ2003-2006 እ.ኤ.አ የሰርቢያና ሞንቴኔግሮ ብሔራዊ ቡድን ረዳት አሰልጣኝ ሆነው ካገለገሉ በኋላ በ2009 እ.ኤ.አ ላይ በቀድሞ ክለባቸው ፓርቴዝያን ቤልግሬድ ረዳት አሰልጣኝ ሆነው ተቀጥረዋል፡፡ በ2013 ደግሞ በዚሁ ክለብ ዋና አሰልጣኝ ሆነው አገልግለዋል፡፡ በአፍሪካ ልምድ ያላቸው ሲሆን በ2011 እ.ኤ.አ ላይ የጋና ብሔራዊ ቡድንን ለማሰልጠን በደቡብ አፍሪካ በተደረገው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፈዋል፡፡ ባለፈው የውድድር ዘመን የቻይና ሱፕር ሊግ ክለብ በሃላፊነት ተረከበው የነበረ ቢሆንም ክለቡ ወደ ዝቅተኛ ሊግ በመውረዱ ተሰናብተው ያለፉትን ወራት ያለ ስራ ቆይተዋል፡፡


ስቴፈን ኮንስታንቲን የ51 ዓመቱ አርጀንቲናዊ ከ1994 እ.ኤ.አ ጀምሮ ለአሰልጣኝነት እየሰሩ ናቸው፡፡ 4 ብሔራዊ ቡድኖችን ለማሰልጠን ከሌሎቹ አመልካቾች የላቀ ልምድ ያላቸው ሲሆን  በ1999 እ.ኤ.አ ለሁለት ዓመት ኔፓልን፣ ከ2003 ጀምሮ ለ3 ዓመታት ህንድን፣ ከ2007 ጀምሮ ለአንድ ዓመት ማላዊን እንዲሁም በ2011 የሱዳን ብሔራዊ ቡድን በዋና አሰልጣኝነት መርተዋል፡፡ በአሰልጣኝነት የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ፕሮፌሽናል ፍቃድ ያላቸው ሲሆን በስነልቦና እና በአካል ብቃት ስልጠና ምርጥ ተብለው ሁለት ጊዜ የተሸለሙ፤ በምግብ ሳይንስ ዲፕሎማ ያላቸው እና የአሰልጣኞች አሰልጣኝ ተብለው በፊፋ እውቅና ያላቸው ኢንስትራክተር ናቸው፡፡

        የዓለም አትሌቶች በጎዳና ላይ ሩጫዎችና በተለያዩ የአትሌቲክስ ውድድሮች ባገኙት የሽልማት ገቢ  ከ1 እስከ 50  በወጣው ደረጃ ኢትዮጵያ  በሁለቱም ፆታዎች  በ23 አትሌቶች እንደተወከለች ለማወቅ ተቻለ፡፡ ከኢትዮጵያ አትሌቶች በሽልማት ገቢያቸው ኃይሌ ገብረስላሴ እና ጌጤ ዋሚ ይመራሉ፡፡ ባለፉት 15 ዓመታት  በዓለም ዙርያ በተካሄዱ የጎዳና ላይ ሩጫዎች እና ሌሎች የአትሌቲክስ ውድድሮች አትሌቶች ያገኙአቸውን በግልፅ የሚታወቁ  የገንዘብ ሽልማቶች በመደመር ደረጃውን ከሳምንት በፊት  በድረገፁ ይፋ ያደረገው የጎዳና ላይ ሩጫዎች የስታትስቲክስ ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ ማህበር (ARRS/ Associations of Road racing statisticians )  ነው፡፡ ይህን ዓለም አቀፍ ደረጃ  በወንዶች ምድብ  የሚመራው በ52 የተለያዩ ጊዜያት 3 ሚሊዬን 548 ሺህ 398 ዶላር ያፈሰው ኃይሌ ገብረስላሴ ሲሆን በሴቶች ምድብ ደግሞ በ56 የተለያዩ ጊዜያት 2 ሚሊዬን 236 ሺህ 415 ዶላር ያገኘችው የእንግሊዟ ፓውላ ራድክሊፍ ናት፡፡  በወንዶች ምድብ በደረጃው ሰንጠረዥ መግባት ከቻሉት  50 አትሌቶች 10 ኢትዮጵያውያን ሲገኙበት በድምሩ 10 ሚሊዬን 345 ሺህ 423 ዶላር በሽልማት ገቢ አድርገዋል፡፡ በሴቶች ምድብ ደግሞ  ከ50ዎቹ አትሌቶች 13 ያህሉ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ድምር የሽልማት ገቢያቸው 9 ሚሊዬን 575 ሺህ 957 ዶላር ነው፡፡
የጎዳና ላይ ሩጫዎች የስታትስቲክስ ባለሙያዎች ማህበር www.arrs.net በተባለው ድረገፁ በዓለም አቀፍ
የአትሌቲክስ  ከ3ሺ ሜትር አንስቶ ያሉትን የጎዳና ላይ ሩጫዎች እና ሌሎች ውድድሮች በትኩረት በመከታተል የአትሌቶችን የውጤታማነት ደረጃ፤ ሰዓትና ድምር ስኬት ከፋፍሎ በማስላት ወርሃዊ እና ዓመታዊ መረጃዎችን ይፋ ያደርጋል፡፡ በዚሁ ድረገፅ የዓለም አትሌቶች በጎዳና ላይ ሩጫዎች እና በሌሎች የአትሌቲክስ ውድድሮች በሰበሰቡት የሽልማት ገንዘብ ላይ ደረጃውን በማውጣት የሚያስታውቅበት አሰራርም አለው፡፡ ኤአርአርኤስ በሽልማት ገቢ  ለሚሰራው ደረጃ እና ሌሎች መረጃዎችን በድረገፁ ለማስፈር የሚጠቀምበትን ዳታቤዝ ለማዘጋጀት   በመላው ዓለም የሚደረጉን ከ160 ሺህ በላይ የጎዳና ላይ የሩጫ እና ሌሎች ውድድሮችን በመከታተል መረጃዎችን ከማሰባሰቡም በላይ በየውድድሩ  35 ሺህ አትሌቶች ያስመዘገቧቸውን 900 ሺህ በላይ ውጤቶች አገናዝቧል፡፡ እነዚህን መረጃዎች በማሰባሰብ እና በማቀናበር ከስታትስቲክስ ባለሙያዎች ማህበር ጋር በመላው ዓለም ያሉ ከ100 በላይ ባለሙያዎች የሚሰሩት ሲሆን  በሺዎች የሚቆጠሩ የአትሌቲክስ በጎ ፍቃደኞችም በተለያዩ ተግባራት ተሳታፊ ይሆኑበታል፡፡ ኤአርአርኤስ የዓለም አትሌቶች በጎዳና ላይ ሩጫ እና ሌሎች የአትሌቲክስ ውድደሮች ያገኟቸውን የሽልማት ገቢዎች ያሰባሰበው በግል በሚመዘገብ ውጤት በግልፅ የሚወስዷቸውን የሽልማት ድርሻዎችና  በቡድን ውጤት የሚያገኙትን ገቢ በመደማመር ነው፡፡ በሽልማት ገቢው የተሰራው ደረጃ አትሌቶች በተለያዩ ዓለምአቀፍ ውድድሮች በግላቸው ተደራድረው የሚያገኟቸውን የተሳትፎ ክፍያዎች፤  ልዩ ልዩ ጥቅማጥቅሞች፤ የቦነስ ሽልማቶች፤ የስፖንሰር ገቢዎች፤ እንደመኪና አይነት የተለያዩ ስጦታዎችን ያካተተ አይደለም፡፡ ከዚህ በታች የቀረበው በኤአርአርኤስ ድረገፅ በዓለም አትሌቶች የሽልማት ገቢ ደረጃ ላይ በሁለቱም ፆታዎች ከ50ዎቹ ተርታ የገቡት የኢትዮጵያ አትሌቶች ባገኟቸው የሽልማት ገቢዎች በአገር እና በዓለምአቀፍ የሚኖራቸው ደረጃ ነው፡፡
=======================
በወንዶች
$3,548,398  (52)  ኃይሌ ገ/ስላሴ
                                                 - ከዓለም 1ኛ
1,559,828   (47) ቀነኒሳ በቀለ - 2ኛ
1,544,520   (18) ፀጋዬ ከበደ - 4ኛ
648,500   (10) አዲስ አበበ   - 15ኛ
$573,445   (24) ሌሊሳ ዴሲሳ  - 21ኛ
568,947   (38)  ገብሬ ገ/ማርያም - 22ኛ
533,700   (32) ድሪባ መርጋ - 26ኛ
475,850   (31) ታደሰ ቶላ- 35ኛ
475,465   (26) ጥላሁን ረጋሣ  -36ኛ
416,770   (11) ደሬሳ ኤዴ - 47ኛ

በሴቶች
$1,438,280   (44) ጌጤ ዋሚ   - ከዓለም 6ኛ
1,254,395   (67) ብርሃኔ አደሬ  - 9ኛ
970,893   (56)  መሠረት ደፋር  - 16ኛ
904,836   (43) ጥሩነሽ ዲባባ   - 17ኛ
835,605   (45)  ማሚቱ ደሳካ  - 19ኛ
772,189   (19) አሰለፈች መርጊያ  -  22ኛ
647,873   (46) ደራርቱ ቱሉ  - 28ኛ
622,053   (36) ድሬ ቱኔ አሪሲ  - 29ኛ
621,508   (25)  ብዙነሽ በቀለ  - 30ኛ
517,380   (40)  መሰለች መልካሙ   - 36ኛ
517,220   (18)  ትርፌ በየነ  - 37ኛ
515,185   (27) አፀደ ባይሳ  - 40ኛ
475,920  (29)  ሙሉ ሰቦቃ -  45ኛ
ማስታወሻ - በቅንፍ የተቀመጠው አኃዝ የተሸለሙበት ብዛት ነው፡፡
አንድ ዶላር በወቅታዊ የምንዛሬ ዋጋ 19.80 ብር ነው፡፡

“በህይወቴ እንደ ፎቅና ሊፍት የምጠላው ነገር የለኝም”

ከአለም ህዝብ ከ10 በመቶ በላይ የፎቢያ ተጠቂ ነው
ሴቶች ከወንዶች ሁለት እጥፍ ያህል በፎቢያ ይጠቃሉ

          ከፍ ያሉ ሥፍራዎችን የመፍራት ችግር (ፎቢያ) እንዳለበት ያወቀው የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ በነበረበት ወቅት ነው፡፡ የመማሪያ ክፍላቸው ወደሚገኝበት 3ኛ ፎቅ ለመሄድ ገና ደረጃዎችን መውጣት ሲጀምር ሰውነቱ ይንቀጠቀጣል፣ ልቡ በሃይል ይመታል፣ ፍርሃት ፍርሃት ይለዋል። ይህ ነገር በጊዜ ሒደት ሊተወው እንደሚችል ቤተሰቦቹም ሆኑ ጓደኞቹ ቢነግሩትም እሱ ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ ችግሩ እየባሰበትና ለከፍታ ቦታዎች ያለው ፍራቻ እየጨመረ ሄደ፡፡
እጅግ በበዛ ችግርና ፈተና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን አጠናቆ ለከፍተኛ ትምህርት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገባ፡፡ የዩኒቨርሲቲ ቆይታውም በበርካታ ፈታኝ ሁኔታዎች የተሞላ ነበር፡፡ የመማሪያ ክፍሎቹ በህንፃዎች ፎቅ ላይ መሆናቸው በየዕለቱ በትምህርት ገበታው ላይ እንዳይገኝና ትምህርቱን በአግባቡ እንዳይከታተል  እንቅፋት ሆነውበታል፡፡ ፍርሃቱ እጅግ የበዛ ቀን ሲቀር፣ ከመምህራኖቹ የሚደርስበት ተከታታይ ማስጠንቀቂያ ሲያደፋፍረውና እንደምንም አይኑን ጨፍኖ ወደ ክፍሉ ሲገባ የአራት አመታት የዩኒቨሲቲው ትምህርት አልቆ ወጣ፡፡
በኢትዮ ቴሌኮም የአይቲ ዲፓርትመንት ክፍል የተቀጠረው ከዩኒቨርሲቲው ከወጣ ከጥቂት ወራት በኋላ ነበር፡፡ በተማረው ሙያና በሚወደው የሥራ መስክ መሰማራቱ እጅግ ቢያስደስተውም ያ ከልጅነቱ ጀምሮ  ፈተና የሆነበት ልክ ያጣ የከፍታ ፍራቻ እዚህም ተከትሎት መጣ፡፡ ወደ ቢሮው ለመሄድ ገና ከቤቱ ሲወጣ ሃሣብ የሚሆንበት ባለስምንት ደረጃዎቹን ፎቅ መውጣት ነበር፡፡
ቢሮው የሚገኘው እጅግ ዘመናዊ አሳንሰር ከተገጠመላቸው የከተማዋ አዳዲስ ህንፃናዎች በአንዱ ላይ በመሆኑ ሊፍት የመጠቀም ዕድል ቢኖረውም ለአንዲትም ቀን ሞክሮት አያውቅም። “ሊፍት ውስጥ ገብቼ በህይወት የምወጣ አይመስለኝም፡፡ የሊፍቱ በር ጭርሱኑ የሚከፈት ሁሉ አይመስለኝም፡፡ በደረጃ ስወጣ እንኳን ዘወር ብዬ የመጣሁበትን ደረጃ ወደኋላ ማየት አልችልም፡፡ ህንፃው መስታወት በመስታወት ሆኖ ደረጃ እየወጣሁ መሬቱን ቁልቁል የማየው ከሆነ አዙሮኝ ልወድቅ ሁሉ እችላለሁ፡፡ በህይወቴ እንደፎቅና ሊፍት የምጠላው ነገር የለኝም፡፡ ይህ የፎቅና የደረጃ ፍራቻዬ ለትምህርቴም ለሥራዬም መሰናከል ሆኖብኛል፡፡ ትምህርቴን ለመቀጠል ወይም ደግሞ ሥራዬን ለመቀየር ፍላጐቱ ቢኖረኝም ይኸው ችግሬ እንደሚከተለኝ ስለማወቅ መድፈር አቅቶኛል፡፡ ይህንን ችግሬን ለማስወገድ የተለያዩ ሙከራዎችን ባደርግም አልተሳካልኝም፡፡ ሁሉም ቀስ እያለ ይተውሃል ይሉኛል፡፡ ይሄው 36 ዓመቴን አጠናቅቄአለሁ፡፡ መቼ እንደሚተወኝ አይገባኝ። በአውሮፕላን መብረር ስለማልችል በርካታ ስልጠናዎችና ልዩ ልዩ የውጭ አገር ዕድሎችን አጥቻለሁ፡፡ ችግሩ ካለበት ሰው ሌላ ማንም ስሜትሽን በቅጡ ሊረዳሽ አይችልም፣ ነገሩ ችግር ብቻ ሳይሆን በሽታም ነው፡፡ ሐኪም የማያድንሽ፣ ሰው የማያዝንልሽ በሽታ!”
 ይህንን ያለኝ በኢትዮ ቴሌኮም የአይቲ ዲፓርትመንት ክፍል በኃላፊነት ደረጃ ላይ ተመድቦ የሚሰራ አንድ ወጣት ነው፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ የተጠናወተው ከፍታ ቦታዎችን የመፍራት አባዜ (አክሮ ፎቢያ) ዕድሜው የወጣትነትን ድንበር እስኪሻገር ድረስም አልተወውም፡፡
ከልክ ያለፈ፣የተጋነነና ተጨባጭ የሆነ ምክንያት በሌለው ጉዳይ የሚፈጠር ስር የሰደደ ፍርሃት ፎቢያ ይባላል፡፡ ከወንዶች ይልቅ ሴቶች በዚህ ችግር የመጠቃት ዕድላቸው በሁለት እጥፍ እንደሚጨምር በእንግሊዝ ተመራማሪዎች የተደረጉ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ ከዓለማችን ህዝቦች 10 በመቶ ያህሉ በአንድ የፎቢያ ዓይነት የመያዝ ዕድል እንደሚያጋጥማቸው የሚጠቁመው እ.ኤ.አ በ2012 የተደረገው ይኸው ጥናት፤ በተለይም ባደጉት አገራት ህዝቦች ላይ ጎልቶ እንደሚታይ አመልክቷል፡፡
ፍርሃት ሰዎች ራሳቸውን ከተለያዩ አደጋዎች እንዲጠብቁና ከችግሩ ለመከላከል የሚያስችላቸው ፈጣን ውሳኔ እንዲተገብሩ የሚያስጠነቅቅ ጤናማ ስሜት ሲሆን ከሰው ሰው በተለያዩ ሁኔታዎችና ደረጃዎች ሊገለፅ ይችላል፡፡ ይሄ ስሜት ጠንቃቃ እንድንሆንም ያግዘናል፡፡ ፎቢያ የሚሆነው ከጤናማው የፍርሃት መገለጫ በተለየ ያለአንዳች ምክንያት የሚከሰትና ቅጥ ያጣ ጭንቀትና መረበሽን የሚያስከትል ሲሆን ነው፡፡
ልዩ ልዩ ነገሮችን ያለምክንያት ከልክ በላይ የመፍራት አባዜ (ፎቢያ) በአራት ዋና ዋና ክፍሎች እንደሚከፈል የገለፀው ጥናቱ፤እነዚህም የደም ፍራቻ፣ የተፈጥሮ ሁኔታዎች ፍራቻ፣ የእንስሳት ፍራቻና የማህበራዊ እንቅስቃሴዎች ፍራቻ እንደሚባሉም ጠቅሷል፡፡
ፎቢያ መነሻው ይህ ነው ተብሎ ሊጠቀስ የሚችል ምክንያት እንደሌለው ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ የሥነ ልቦና ባለሙያው ዶ/ር ተከተል ካሳሁን ይህንኑ አስመልክተው ሲናገሩ፤ “የፎቢያ መነሻና ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ ተብለው በግልፅ የሚቀመጡ ነገሮች የሉም፡፡ ይሁን እንጂ ችግሩ ወደ ፎቢያነት ደረጃ ከመድረሱ በፊት የሚኖር ተራ ፍርሃት አለ፡፡ ለዚህ ፍርሃት መነሻ ሊሆኑ የሚችሉ ምክንያቶች ደግሞ ይኖራሉ፡፡ ለምሳሌ - አንድ በልጅነቱ ሰው ከከፍታ ላይ ወይም ከፎቅ ላይ ተወርውሮ ሲወድቅ ያየ ሰው፣ ዕድሜው እየጨመረ ሲሄድ ለከፍታ ቦታዎች የሚኖረው ፍራቻ እያደገ ይሄድና ወደ ፎቢያ በመለወጥ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴውን አደጋ ላይ ሊጥልበት ይችላል፡፡ እዚህ ደረጃ ላይ የደረሰ ፎቢያ ደግሞ ያለምንም ጥርጥር የህክምና እርዳታ ያስፈልገዋል” ብለዋል፡፡
በጣም የተለመዱና የበርካታ ሰዎች ችግር ከሆኑት ፎቢያዎች መካከል የከፍታ፣ የጨለማና የውሃ፣ ድልድይ የመሻገር፣ ፎቅ ላይ የመውጣት፣ በአውሮፕላን የመሳፈር፣ መኪና የመንዳት፣ ዳገታማ ቦታዎች ላይ (ፎቅ) ላይ የመውጣት፣ በሊፍት (በአሳንስር) የመሳፈር፣ መሰላል ላይ የመውጣትና ሰዎች በተሰበሰቡባቸው ቦታዎች ላይ የመገኘት  ፎቢያዎች ከብዙዎቹ ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
ከፍታን የመፍራት ፎቢያ (አክሮፎቢያ)
ይህ አይነቱ ፎቢያ ያለባቸው ሰዎች ዳገታማ ቦታዎች ላይ፣ ፎቅና መሰላል ላይ እንዲሁም ደረጃዎች ላይ መውጣትን አጥብቀው ይፈራሉ፡፡ በሊፍት (በአሳንሰር) መውጣትና መውረድ ለእነዚህ አይነት ሰዎች የሞት ያህል አስፈሪ ነው፡፡ የከፍታ ፍራቻ ያለባቸው ሰዎች፣ በአውሮፕላን መሳፈርን አጥብቀው ይፈራሉ፡፡ የዚህ ፎቢ ተጠቂ የሆኑ ሰዎች ድልድይ መሻገርንና መኪና ማሽከርከርንም ይፈራሉ፡፡ ፍራቻው  በአብዛኛው የፎቢያ ችግር ባለባቸው ሰዎች ላይ ጎልቶ የሚታይ ሲሆን ችግሩ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴን  በማወክ በተጠቂው ላይ ስነልቦናዊ ቀውስን ሊያስከትል ይችላል፡፡
የደም ፍራቻ (ሄማቶፎቢያ)
የዚህ ዓይነት ፎቢያ ያለባቸው ሰዎች ደምን ጨምሮ ማናቸውንም ከደም ጋር ንኪኪ ያላቸውን ነገሮች የማየት ከፍተኛ ፍራቻ አለባቸው፡፡ መርፌ፣ ምላጭና የተለያዩ የህክምና መሳሪያዎች ለእነዚህ ሰዎች ፍራቻ መነሻ ሊሆኗቸው ይችላሉ፡፡ ደም ባልሆነና ደም ሊሆን ይችላል ባሉት ነገር ሁሉ ፍርሃትና ድንጋጤ ይፈጠርባቸዋል፡፡
የማህበራዊ እንቅስቃሴ ፍራቻ (ሶሻልፎቢያ)
ይህ አይነቱ ፎቢያ ያለባቸው ሰዎች፣ ማህበራዊ እንቅስቃሴ በሚደረግባቸው ሥፍራዎች ላይ መገኘትን አጥብቀው ይፈራሉ። በሰዎች ፊት መብላት፣ መጠጣትና መናገርን ፈጽመው አይደፍሩም።  ምክንያታቸው ደግሞ በሥፍራው የተሰበሰቡት ሰዎች ስለነሱ የሚያወሩ ስለሚመስላቸው ነው። ይህ አይነቱ ጥልቅ ፍርሃት የሰዎችን ማህበራዊ እንቅስቃሴ የሚገድብና ከፍተኛ የሥነልቡና ችግር የሚያስከትል እንደሆነ የሥነ-ልቡና ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡ የዚህ ችግር ተጠቂዎች እንደሠርግ፣ ለቅሶ፣ ግብዣ፣ ሃይማኖታዊ በአላት በሚከበሩባቸው ሥፍራዎችና ሰዎች በሚሰበሰቡባቸው ቦታዎች ላይ ጨርሶ መገኘት አይፈልጉም፡፡ ደህንነት የሚሰማቸው በፀጥታ ሥፍራ ብቻቸውን ሲሆኑ ነው፡፡
የእንስሳት ፎቢያ
በሰው ልጅ ላይ ምንም ጉዳት የማያደርሱ ወይንም የሚያደርሱት ጉዳት እጅግ አነስተኛ የሆኑ እንስሳትን ጨምሮ ለማንኛውም እንስሳ ጥልቅ ፍራቻ ያድርባቸዋል - የዚህ ችግር ተጠቂዎች። ውሻ፣ ድመት፣ አይጥ፣ ሸረሪትና ጉንዳን እጅግ የሚያስፈሯቸው ሲሆን እነዚህን እንስሳት በተመለከቱ ጊዜ ወይንም በሌሉበት ሥፍራ ስማቸው ሲነሳ ከፍተኛ ፍርሃት ይሰማቸዋል፡፡ ይህ ፎቢያ ያለባቸው ሰዎች በአብዛኛው ለችግሩ መነሻ የሆኑ ምክንያቶች ይኖሯቸዋል፡፡ በልጅነታቸው በእንስሳ የመነከስ ወይም ሌሎች ጉዳቶችን የሚያደርስ አደጋ ከገጠማቸው እስከ ዕድሜያቸው ፍፃሜ ድረስ እነዚህን እንስሳት ሲፈሩና ሲሸሹ ይኖራሉ፡፡  
የጨለማና የውሃ ፎቢያ
የዚህ ፎቢያ ተጠቂዎች ለጨለማ ወይንም ለውሃ ያላቸው ፍራቻ እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ ብርሃን በሌለባቸው ቦታዎች ላይ መንቀሳቀስም ሆነ ጨለማ በሆኑ ሥፍራዎች ላይ መገኘትን ፈፅመው ይፈራሉ። የጨለማ ፎቢያ ያለባቸው ሰዎች፣ በአብዛኛው የከባድ ራስ ምታት ተጠቂዎች ናቸው፡፡ የውሃ ፎቢያ ተጠቂዎችም በተለይ ብቻቸውን ሆነው ውሃ ባሉባቸው አካባቢዎች መዘዋወርን አጥብቀው ይፈራሉ፡፡ አነስተኛ ኩሬዎች ወይንም የውሃ መውረጃዎች ለእነዚህ ሰዎች ፍርሀት መነሻዎች ናቸው፡፡ ችግሩ ባስ ያለባቸው ሰዎች ደግሞ ለብቻቸው ሰውነታቸውን መታጠብም ሆነ ዋና መዋኘት ፈፅመው አይደፍሩም፡፡
የፎቢያ ተጠቂነት በምን ይገለፃል?
አንድ ሰው የፎቢያ ተጠቂ መሆኑን በቀላሉ መረዳት ይቻላል፡፡ ሰውየው ለነገሮች እጅግ የተጋነነ እና ቅጥ ያጣ የፍርሀት ስሜትን የሚያሳይ፣ ስሜቱ በእጅጉ የሚረበሽ፣ ውጥረት የሚያጠቃው፣ እንዲሁም ከሥፍራው ለመራቅ ወይም ለመሸሽ ጥረት የሚያደርግ ከሆነ የፎቢያ ተጠቂ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
የፎቢያ ችግር በህክምና ሊድን ይችላል?
የፎቢያ ችግር በህክምና እርዳታ ሊድን እንደሚችል ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ግን ራሱ የፎቢያ ተጠቂው  ከፍተኛ ጥረት ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡
አንድ የፎቢያ ተጠቂ የሆነ ሰው ችግሩን የሚፈጥርበትን ነገር እንዲጋፈጠውና ውስጣዊ የፍርሃት ስሜቱን በማስወገድ፣ ፍርሀቱ ምክንያታዊ መሆን አለመሆኑን አጥብቆ መጠየቅና ማወቅ ይኖርበታል፡፡ ለምሳሌ የከፍታ ፍራቻ ያለበት ሰው፣ ሌሎች በደረጃዎችም ሆነ በአሳንሰር (ሊፍት) በመጓዛቸው ምክንያት የገጠማቸው ችግር አለመኖሩን በማየት፣ አዕምሮው ለፍርሃቱ ምላሽ እንዲሰጥና ጉዳዩ ምንም ችግር እንደማያስከትልበት እንዲነግረው ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ይህ ደግሞ የችግሩ ተጠቂ ከነገሮች ጋር ቀስ በቀስ እንዲላመድና በውስጡ ያለው የፍርሃት ስሜት በሂደት እንዲወገድ ለማድረግ ያስችለዋል፡፡ ስር የሰደደና በራሱ በችግሩ ተጠቂ ጥረት ሊወገድ ያልቻለውን የፎቢያ አይነት ለማስወገድ የሚረዳ “ኮግኒቲቭ ቢሔቨየራል ቴራፒ” የሚባል የህክምና ዘዴ ያለ ሲሆን ህክምናው የሚሰጠው በስነ-ልቦና ባለሙያዎች ነው፡፡

============

የፍራቻ (ፎቢያ) ዓይነቶች

የመብረቅ ፍራቻ - አስትራፎቢያ
የማስመለስ ፍራቻ - ኢሜቶፎቢያ
የወሲብ ፍራቻ - ጂኖፎቢያ
የብቸኝነት ፍራቻ - ሞኖፎቢያ
የአይጥ ፍራቻ - ሙሶፎቢያ
የጭለማ ፍራቻ - ኒክቶፎቢያ
የቁጥር ፍራቻ - ኒውሮፎቢያ
የእባብ ፍራቻ - ኦፊዲዮፎቢያ
የእሳት ፍራቻ - ፓይሮፎቢያ
የሞት ፍራቻ- ታናቶፎቢያ
የባቡር ፍራቻ - ሲዴሮድሮሞፎቢያ
የፀጉር ፍራቻ - ትሪቾፎቢያ
የመርፌ መወጋት ፍራቻ  - ትራይፓኖፎቢያ

  • ምትክ ደም መቅረቱ የደም ደላሎችን ከጨዋታ ውጭ ያደርጋል
  • ከ2500 በላይ ቋሚ በጎ ፈቃደኛ  ደም ለጋሾች አሉን
  • ታዋቂ ሰዎችን መጠቀማችን ለጋሾቻችንን እያበዛልን ነው

ዶ/ር ዳንኤል ገ/ሚካኤል ይባላሉ፡፡
በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የብሔራዊ ደም ባንክ ዳይሬክተር ናቸው፡፡ በተለይ ከሶስት ዓመት ወዲህ ብሄራዊ ደም ባንኩ ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ወጥቶ ወደ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በመዛወር በርካታ የአሰራር ለውጦችን አድርጓል፡፡ ከእነዚህም መካከል ለበሽተኞች ደም ሲሰጥ የሚጠየቀውን ምትክ ደም አስቀርቶ ዜጎች ደም በነፃ እንዲያገኙ አድርጓል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ  የደም እጥረት ቢያጋጥም ምን ሊፈጠር ይችላል የሚሉ ስጋቶች ይስተጋባሉ፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ በስጋቶቹ፣ በህገ-ወጥ የደም ደላሎች፣ በበጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾችና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከዶክተር ዳንኤል ጋር ተከታዩን ቃለምልልስ  አድርጋለች፡፡

ቀደም ሲል ብሄራዊ ደም ባንኩ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ስር ነበር የሚተዳደረው፡፡ አሁን ወደ ጤና ጥበቃ ዞሯል፡፡ ምክንያቱ ምንድነው?
ከደም ባንኩ አመሰራረት ብንነሳ በኢትዮጵያ የደም ባንክ የተመሰረተው በ1962 ዓ.ም ነው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ላለፉት 42 ዓመታት ደም ባንኩ ይተዳደር የነበረው በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ስር ነው። ደም ባንኩ ወደ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የተዛወረበት ምክንያት ሚኒስቴሩ እያስፋፋ የሄደባቸው የጤና ተቋማት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ መምጣት፣ ደም አቅርቦቱ ከፍላጎት ጋር አለመጣጣም በማስከተሉ፣ ይህንን ለማስተካከልና ካሉት የጤና ተቋማት ጋር አስተሳስሮ ለመምራት በመታሰቡ ነው፡፡  ከ2003 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ጀምሮ ነው ወደ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና ወደ ክልል ጤና ቢሮዎች አገልግሎቱ እንዲዛወር የተደረገው፡፡
የደም ባንኩ ወደ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከተዛወረ በኋላ አዳዲስ አሰራሮች እየመጡ ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ታካሚ ምትክ ደም እንዲያመጣ የሚገደድበት አሰራር ቀርቶ በነፃ የሚገኝበት አይነት አሰራር እየተከተላችሁ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ሊሰጡኝ ይችላሉ?
እንዳልሽው ቀደም ሲል አንድ ታካሚ ደም በሚያስፈልገው ከጊዜ ቤተሰቡ ወይም የቅርብ ሰው ምትክ ደም እንዲሰጥ ይደረግ ነበር፡፡ ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በተለይም በአዲስ አበባ ይህ አሰራር ቀርቶ፣ አንድ ሰው ደም በሚፈልግበት ጊዜ የህክምና ባለሙያው ለዚህ ታካሚ ደም ያስፈልጋል ብሎ፣ ወረቀት ይዞ ይቀርባል፤ በቀጥታ ደሙ ይፈቀድለታል። ሁለተኛው አሰራር እና አዲስ የተጀመረው በተለይ በመንግስት ሆስፒታሎች እዚያው ሆስፒታሉ ውስጥ ሚኒ (ትንሽ) ደም ባንክ በማዘጋጀት፣ፍሪጃቸው ውስጥ ለሳምንት የሚበቃቸውን ደም ይወስዱና በሳምንቱ ሲያልቅ መጥተው ይወስዳሉ፡፡ በቀጣይ በግል ሆስፒታሎችም አሰራሩ ይቀጥላል፡፡ ይህ አሰራር በተለይ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ውስጥ በደንብ እየተሰራበት ነው፡፡ ምክንያቱም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከሚሰበሰበው ደም አርባ በመቶውን ይጠቀማል፡፡ በቀጣይ ወደ የካቲትና ጳውሎስ ሆስፒታሎች የማስፋፋት ጥረቶች ይደረጋሉ፡፡
ይህን አሰራር የግል ሆስፒታሎች መቼ የሚጀምሩ ይመስልዎታል?
በአሁኑ ሰዓት ለግል ሆስፒታሎች እየወሰዱ ለመስጠት ከባድ ነው፣ ምክንያቱም በአዲስ አበባ ውስጥ ከመቶ በላይ ሆስፒታሎችና የጤና ተቋማት በመኖራቸው ሁሉንም ለማዳረስ ይከብዳል። እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው፣ ከደም ባንኩ ደም የሚወስዱት አዲስ አበባ ያሉት ብቻ ሳይሆኑ በአዲስ አበባ ዙሪያ ያሉ እስከ መቶ ኪሎ ሜትር ያሉና ከዚያም በላይ እንደነደብረብርሃን ያሉት ሁሉ ደም ይወስዳሉ፡፡ ለእነዚህ ሁሉ ለሳምንት የሚበቃቸውን እንዲወስዱ ማድረግ ከባድ ነው፡፡ እስከ ሻሸመኔ ድረስ ከዋናው (ከአዲስ አበባው) ደም ባንክ ይወስዳሉ፡፡ ዋናው ደም ባንክ ከፍተኛ ጫና አለበት፡፡
የክልል ጤና ቢሮዎች አሰራር ምን ይመስላል? ለምሳሌ የሻሸመኔ  ሆስፒታሎችና ጤና ተቋማት ለምን ከክልሉ ደም ባንክ አይወስዱም?
ጥሩ ጥያቄ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት በአዲስ አበባ ወደ 25 የሚጠጉ ደም ባንኮች ይገኛሉ፡፡ በዚህም በየመቶ ኪሎ ሜትር ራዲየስ የሚገኙ የግልና የመንግስት ሆስፒታሎችና ጤና ተቋማት ከአቅራቢያቸው የደም ባንኮች እንዲወስዱ የሚደረግበት አሰራር እየተዘረጋ ነው፡፡ ለምሳሌ የሻሸመኔ ጤና ተቋማት ከአዳማ ወይም ከሀዋሳ እንዲወስዱ ይደረጋል፡፡ አሁን ለጊዜው ባለው ሁኔታ ግን ከዋናው እየወሰዱ ነው፡፡ ነገር ግን እንዳልሽው አሰራሩ ተዘርግቶ ሲያልቅ ከየአቅራቢያቸው ደም ባንኮች እንዲወስዱ ይደረጋል፡፡
አሁን 25 የደም ባንኮች መኖራቸውን ነግረውኛል። አዳዲሶች እንደተከፈቱም ጠቁመዋል። ቀደም ሲል በአገራችን ምን ያህል የደም ባንኮች ነበሩ?
ቀደም ሲል የነበሩት ከ12 አይበልጡም ነበር። ደም ባንኩ ወደ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከተዛወረ በኋላ በተደረገው እንቅስቃሴ ወደ 25 አድገዋል። እነዚህም አዳዲስ ደም ባንኮች ስራ የጀመሩት ገና በቅርቡ ነው፡፡ በሙሉ አቅማቸው መስራት ሲጀምሩና በደንብ ሲጠናከሩ ቀደም ብለሽ ያነሳሽው በየአካባቢያቸው ደም የሚከፋፍሉበት አሰራር ይቀጥላል፡፡ አሁን ግን አዲስ እንደመሆናቸው የሚችሉትን ያህል እየሰሩ ነው፡፡ በተለይ በኦሮሚያ ክልል ያሉት በደንብ እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡ በኦሮሚያ በዚህ ዓመት ስድስት የደም ባንኮችን ከፍተው በደንብ እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ አዳማ፣ ነቀምት፣ መቱ፣ ጎባ፣ ወሊሶ በደንብ እየሰሩ ነው፡፡ በጭሮ (አሰበ ተፈሪም) ደም ባንኩን ለመክፈት የሰራተኛ ቅጥርና በቢሮው ላይ የማስተካከያ ስራዎች እየተሰሩ ነው፤ በቅርቡ ይጀምራል፡፡
ቀደም ሲል ሰዎች ምትክ ደም እንዲያመጡ የሚገደዱበት አሰራር ቀርቶ ሰዎች ደም በነፃ እንዲያገኙ መደረጉ ፋይዳው ምንድነው?
ይህ አሰራር እንዲቀር የተደረገበት ዋናው ምክንያት የዓለም የጤና ድርጅት (WHO)ም ሰዎች ደምና የደም ተዋፅኦዎችን በነፃ ማግኘት አለባቸው የሚል ሲሆን ደም መገኘትም ያለበት ከበጎ ፈቃደኞች ነው ይላል፡፡ ምክንያቱም አንድ ሰው ምትክ ደም በሚሰጥበት ጊዜ ግዴታ ነው። እናትህ ታማለችና ደም መስጠት አለብህ ተብሎ ይገደዳል፡፡ ይህ አሰራር በብዙ ምክንያቶች ጥሩ አይሆንም፤ ከምክንያቶቹ አንዱ ይህ ሰው የስነ-ልቦና ዝግጅት ላይኖረው ይችላል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ በጤናው ላይ ችግር ሊኖርበት ይችላል። አንዳንድ ሰዎች ለምሳሌ ኤችአይቪ በደማቸው ያለባቸው፣ ከቤተሰብ ደብቀው መድሃኒት የሚወስዱ ይሆኑና ደም ስጡ ሲባሉ ሚስጥሩ እንዳይታወቅ ደም ይሰጣሉ፡፡ ደማቸው ምትክ ሆኖ ሲቀርብ አያገለግልም፡፡ ከቤተሰብ በምትክ የሚገኝ ደም በአብዛኛው ለተለያዩ ችግሮችና በሽታዎች የተጋለጠ ነው፡፡ ይህ በመረጃ የተረጋገጠ ነው፡፡ በጎ ፍቃደኞች በየሶስት ወሩ የኤችአይቪ እና የሌሎች የጤና ምርመራዎች የሚያደርጉ ናቸው፡፡ ስለሆነም የዓለም የጤና ድርጅት በ2020 ዓ.ም ሁሉም አገሮች መቶ በመቶ ደም ከበጎ ፈቃደኞች ብቻ እንዲሰበስቡ በሚል አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ አገራችንም ይህን ተግባራዊ ለማድረግ ነው እየተንቀሳቀሰች ያለችው፡፡ በመሆኑም የፌደራል ጤና ጥበቃም ይህን አቅጣጫ በመከተል መቶ በመቶ ደም ከበጎ ፈቃደኞች ብቻ እየሰበሰበ ይገኛል፡፡
በጎ ፈቃደኞች የሚፈለገውን ያህል ደም መለገስ ባይችሉና ያለው ክምችት ቢያልቅ ምን ተማምኖ ነው ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ምትክ ደም እንዲቀር ያደረገው?
ይህንን ጉዳይ በጣም አስበንበት ነው የጀመርነው፤ ዝም ብሎ በስሜት የሚሰራም አይደለም፡፡ በደንብ አቅደንና አስልተነው ነው ወደ ትግበራ የገባነው። ከላይ ላነሳሽው ስጋት መፍትሄው በጎ ፈቃደኞች  እንዲለግሱ ግንዛቤ መፍጠርና ማስተማር ነው፡፡ ጠንክረን እስካስተማርን ድረስ እጥረት ይገጥመናል ብለን አናስብም። ሁለተኛው እጥረት በሚገጥመን ጊዜ ፈጥነው ደም የሚሰጡ ተመዝግበው የተቀመጡ ከ2500 በላይ በጎ ፈቃደኞች አሉን፡፡ እነዚህ በጎ ፈቃደኞች በማንኛውን ሰዓት እጥረት ቢገጥመን ደውለን የምንጠራቸው ቋሚ ደም ለጋሾቻችን ናቸው፡፡ ሆኖም የእነዚህን በቋሚነት ደም የሚለግሱ ሰዎች ቁጥር በ10 እጥፍ የማሳደግ እንቅስቃሴ እቅድ አለን፡፡ ስለዚህ ህብረተሰቡ ደም መለገስን ባህሉ እንዲያደርግ ከጣርን፣ እነዚህ ከ2500 በላይ ቋሚ ለጋሾቻችን በየሶስት ወሩ የሚሰጡን ደም ካለ፣ የህሙማንን ቤተሰቦች ደም በነፃ ስንሰጣቸው ማወቅ ያለባቸው ያህል ካስተማርናቸው እጥረት ሊገጥመን አይችልም፡፡ ለህሙማን ቤተሰቦች ደም በነፃ ከሰጠን በኋላ በደንብ አስተምረን፣ ወደፊት እነሱም ደም በመለገስ የሰዎችን ክብር ህይወት እንደያተርፉ ነግረን፣አድራሻቸውን ወስደን ነው የምናሰናብታቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ዛሬ እናታቸው፣ እህታቸው ወይም ወንድማቸው በሌላ ሰው ደም መዳኑን ስለሚያውቁ፣ ነገ የሌላውን ህይወት ለማትረፍ እየመጡ ደም ይሰጣሉ፡፡ ይህን በተጨባጭ እያየነው ነው፡፡ በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች የደም እጥረት ያጋጥመናል ብለን አናስብም ግን ብዙ መስራትን ይጠይቀናል፡፡፡
ደም ሻጭ ደላሎች ሰዎችን እያጭበረበሩ በአሰራሩ ላይ እንቅፋት ሆነዋል የሚሉ ቅሬታዎች አሁንም ሆስፒታሎች አካባቢ እየተደመጡ ነው፡፡ ይህን ችግር ታውቁታላችሁ?
በነገራችን ላይ ምትክ ደም አስቀርተን በነፃ መስጠት ስንጀምር አካባቢ፣ ትልቁ ራስ ምታታችን ደም ሻጭ ደላሎች ጉዳይ ነበር፡፡ አንድ ሰው በፊት ምትክ የሚሰጥለት ዘመድ ሳይኖረው ሲቀር “የሚሸጥ ደም አለ” እያሉ ደላሎች ካገናኙት በኋላ “የአጎቴ ልጅ ነው፣ የአክስቴ ልጅ ነው” እያለ ደም ገዝቶ ያመጣ ነበር፡፡ ደም ገዝቶ ያመጣ ነበር ሲባል ሻጩና ገዢው በደላላ ከተገናኙ በኋላ ተደራድረው “ዘመድ ነኝ” በማለት ደም ሰጥቶ ይሄድ ነበር፡፡ በተጠና ጥናትና ባለው መረጃ መሰረት፣ ደም ሻጮቹ ደማቸውን ሸጠው ለጫት፣ ለመጠጥ፣ ለአደንዛዥ ዕፅ መግዣ ነው የሚጠቀሙበት፡፡
እነዚህ ዕጾች ደግሞ ጤናማ ደም እንዳይኖራቸው ያደርጓቸዋል?
በትክክል! ለምሳሌ ከአደንዛዥ እፅ ጋር በተገናኘ ሱስ ያለባቸው ጠጥተው የሚሰክሩ ሰዎች ራሳቸውን ለኤችአይቪ ኤድስና መሰል በሽታዎች ሊያጋልጡ ይችላሉ፡፡ ይህን ደግሞ ራሳችን የምናጠናበት መንገድ አለ፣የታተሙ ጥናቶችም አሉ፡፡ በነገራችን ላይ እነዚህ ደም በገንዘብ የሚሸጡ ሰዎች “Paid donors” ይባላሉ፡፡ በእኛ አገር ደም አይሸጥም አይለወጥም፣ ይህ ወንጀል ነው፡፡ በሌሎች አገሮች የደም ባንካቸው ገንዘብ እየከፈለ ደም የሚሸጡ አሉ። ይህ በስትራቴጂና በሌሎች ችግሮች ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡ እኛ አገር እንደ ስትራቴጂ የምንከተለው የበጎ ፈቃደኝነት ደም ልገሳን ነው፡፡ አሁን በዓለም ጤና ድርጅት ውስጥ አባል የሆነ አገር ደም መግዛትና መሸጥ ይከለክላል፡፡ ወደ ደም ሻጮች እና አደንዛዥ ዕፅ ተጠቃሚዎች ደም ስንመጣ፣ከሚለግሱት ደም 50 በመቶው ጤናማ ባለመሆኑ ከጥቅም ውጭ ይሆናል፡፡
ስለዚህ እኛም አገር እነዚህ ደም ሻጮች በቤተሰብ ምትክ ውስጥ ተሸሽገው ሊኖሩ ይችላሉ። ቤተሰብ ነኝ እያሉ ይመጣሉ፡፡ ያኔ ታዲያ ባለሞያዎቻችን ቤተሰብ ነው አይደለም የሚለውን ለማየት መታወቂያ መጠየቅና መሰል ስራዎች አስቸግረዋቸው ነበር። ምትክ ደም መቅረቱ ደም ሻጮችንና ደላሎችን ከጨዋታ ውጭ የሚያደርግ ነው፡፡
ግን እኮ አሁንም ሆስፒታሎች አካባቢ ይህ ማጭበርበር አልቀረም እየተባለ ነው?
እርግጥ አሁንም በተለይ ከገጠር የሚመጡ ወገኖች እስከ ሁለት ሺህ ብር ድረስ አውጥተው ደም ይገዛሉ የሚባል ነገር ይሰማል፡፡ ይህ ግን ከደም ባንኩ ጋር የተያያዘ አይደለም፡፡ በፊትም ሆነ አሁን የደም ባንክ ደም ሲሰጥ ሽራፊ ሳንቲም አይቀበልም። ወደፊትም አይቀበልም፡፡ ማንኛውም ዜጋ ደም በነፃ ነው የሚያገኘው፡፡ የሰራተኞች ደሞዝ፣ የደም ከረጢትና የመመርመሪያ መሳሪያዎችን ወጪ መንግስት ነው የሚሸፍነው፡፡ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾችም ከማንም ሽራፊ ሳንቲም ሳይፈልጉ በነፃ ይሰጣሉ፡፡ ነገር ግን በመሀል ቢሮክራሲ በመፍጠርና ሲስተሙን በማዛባት ገንዘብ ለማግኘት የሚጥሩ አንዳንድ ግለሰቦች አይኖሩም ማለት አይደለም። ሆስፒታሎች አካባቢ ከደም ጋር የተያያዘ ስራ የሚሰሩ ባለሙያዎች፣ደም ለመስጠት ወይ ምትክ ደም አለበለዚያ ገንዘብ አምጡ እያሉ እንደሚያጭበረብሩ ሰምተን፣ ጉዳዩን እጅ ከፍንጅ ለመያዝ በድብቅ ክትትል አድርገን ነበር፣ እስካሁን ግን ያጋጠመን ነገር የለም፡፡ ይህ በግለሰብ ደረጃ ነው የሚደረገው፡፡ ሆስፒታሎችም አካባቢ የስነ-ምግባር ችግር ያለባቸው ግለሰቦች አይጠፉም። ዋናው ነገር ህብረተሰቡ ደም በነፃ የማግኘት መብት እንዳለው አውቆና ተገንዝቦ፣ “ምትክ አምጣ ገንዘብ፣ ክፈል” የሚሉ አጭበርባሪዎችን ማጋለጥና ለህግ ማቅረብ አለበት፡፡
ደም ባንኩ ወደ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከተዛወረ በኋላ ያለው የደም ክምችት በምን ያህል ፐርሰንት ጨምሯል?
በዓመት ውስጥ የሚሰበሰበው የደም ክምችት ምን ያህል ነው የሚለውን ብንመለከት፣ ከሶስት አመት ወዲህ፣በፊት ከነበረው እጥፍ በሚባል መልኩ እየተሰበሰበ ነው፡፡ ከዚያ በፊት ግን በአመት የሚሰበሰበው የደም መጠን ከ40 ሺህ ከረጢት በታች ነበር፡፡ አሁን ወደ ሚኒስቴሩ ከተዛወረ በኋላ ለሁለት አመቱ አፈፃፀም በዓመት ወደ 63ሺህ ዩኒት ደም መሰብሰብ ተችሏል፡፡ ሌላው ቀርቶ በ2006 ዓ.ም በስድስት ወር ውስጥ 40 ሺህ ከረጢት ደም ተሰብስቧል፡፡ ይህ መጠን ከሶስት ዓመት በፊት በዓመት የሚሰበሰብ የደም መጠን ነበረ። ስለዚህ በእጥፍ መጨመሩን ያመለክታል፡፡ ይህ ለውጥ በሁለት መንገድ ነው የመጣው፡፡ አንደኛው የሰራነው የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ነው። ትምህርቱ በቂ ነው ብለን ደረታችንን ባንነፋም በተቻለ መጠን ህብረተሰቡ ደም ልገሳ ላይ ያለው አመለካከት እንዲሰፋ እያደረግን ነው፡፡ ግን በጣም ይቀረናል፡፡ ሁለተኛው የደም ባንኮችን ቁጥር በእጥፍ ማሳደግ በመቻላችን ለውጥ አምጥቷል፡፡ በፊት  የደም ባንኮች አዲስ አበባን ጨምሮ በሀገሪቱ ትልልቅ ከተሞች ብቻ ነበር የሚገኙት፡፡ ለምሳሌ ደሴ፣ ባህርዳር፣ ጎንደር፣ አዳማና ሌሎች ከተሞች ነበሩ፡፡ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ደም ባንኩን በስሩ ካደረገ በኋላ በሁሉም የክልል ከተሞች እንዲኖሩ አድርጓል፡፡ በተለይ በማደግ ላይ ያሉት እንደ አፋር፣ ሱማሌ፣ ቤኒሻንጉል እና ጋምቤላ ባሉትም ክልሎች የደም ባንክ እንዲኖር ተደርጓል፡፡ ወደፊትም የበለጡ ቅርንጫፎች እንዲኖሩ ይደረጋል፡፡
በአዲስ አበባ ከ2500 በላይ ቋሚ ደም ለጋሾች እንዳሏችሁ ነግረውኛል፡፡ ከነዚህ በጎ ፍቃደኞች ጋር ያላችሁ ግንኙነት ምን ይመስላል?
በጣም ከፍተኛ ግንኙነት አለን፡፡ አንደኛ በየአመቱ ሰኔ ሰባት ቀን የአለም ደም ለጋሾች ቀን በመሆኑ በዓሉን በደመቀ ሁኔታ እናከብራለን፡፡ ሁለተኛ ከደም ለጋሽ አስተባባሪዎች ጋር በየስድስት ወሩ ውይይት  አለን፡፡ ሶስተኛው መንገድ ዓመት በዓላት በሚኖሩ ጊዜ እየደወልን “እንኳን አደረሳችሁ” እንላለን፡፡ እንደ ቤተሰብ ነው የምናያቸው፣ የምንሳሳላቸው፣ እነሱም በየሶስት ወሩ ለደም ልገሳ ሲመጡ እንገናኛለን፡፡ የጤና ምርመራ፣ የምክር አገልግሎት ያገኛሉ፡፡ በዚህ በዚህ መልኩ መልኩ የጠበቀ ግንኙነት አለን፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ታዋቂ ግለሰቦችና ባለስልጣናት ደም እየለገሱ ነው፡፡ ይህ ምን ያህል ረድቷችኋል?
ጥሩ! አንደኛ እነዚህ ትልልቅ ሰዎች በተለይም የፌዴሬሽንና የህዝብ ተወካዮች ም/ቤቶች አፈ ጉባኤዎች አቶ አባዱላ ገመዳና አቶ ካሳ ተክለብርሃን ደም ሲሰጡ ድርብ ኃላፊነት እየተወጡ መሆናቸውን ያሳያል፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ባለስልጣናት በህዝብ የተመረጡ ናቸው። ስለዚህ የመረጣቸውን ህዝብ ለማስተማር እነሱ በተግባር ማሳየታቸው ህብረተሰቡ ላይ መነሳሳትን ፈጥሯል። አርአያ በመሆን ለሌሎች ለጋሾች ብርታትን ሰጥተዋል፡፡ እነ አትሌት ሀይሌ ገ/ሥላሴ፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ እነ ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ፣ እነ አርቲስት አብርሀም ወልዴ እና መሰል ታዋቂ ሰዎች መጠቀማችን ለጋሾቻችንን እያበዛልን ነው፡፡
በእቅድ ደረጃ በዚህ ዓመት ይህን ያህል ደም እንሰበስባለን የሚል ግብ አስቀምጣችኋል?
አዎ! ለምሳሌ በ2006 ዓ.ም መጨረሻ 150ሺህ ከረጢት ደም ለመሰብሰብ እቅድ ተይዟል። በየዓመቱ የጤና ተቋማት በጨመሩ ቁጥር የሚፈለገው የደም መጠንም እየጨመረ ይሄዳል። በየክልሉ እና በየወረዳው አዳዲስ ሆስፒታሎች ጤና ተቋማት እየተስፋፉ ነው፡፡ የረጅም ጊዜ እቅዳችን የደም ባንኩ ተወዳዳሪና ለሁሉም ዜጋ በቂ የሆነ የደም አቅርቦት እንዲኖረው ማድረግ ነው። ወደፊት የግልም የመንግስትም ጤና ተቋማት ፈቃድ ያላቸው ደረጃቸውን የጠበቁ እስከሆኑ ድረስ ደም እኩል የማግኘት መብት አላቸው፡፡ ላስገነዝብ የምወደውም ከደም ባንክ በነፃ የሚያገኙትን ደም ለህሙማኖቻቸው በነፃ  መስጠት እንዳለባቸው ነው፡፡  
ሆስፒታሎችና ጤና ተቋማት ከደም ባንክ የወሰዱትን ደም በአግባቡ ስራ ላይ ማዋል አለማዋላቸውን የምታረጋግጡበት መንገድ ምንድነው?
አሁን በቀጣይ ትኩረት ሰጥተን የምንሰራው እዚህ ጉዳይ ላይ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ስለሚኖረን ግንኙነት ከሆስፒታሎች ጋር ቁጭ ብለን ተወያይተናል፡፡ ከሆስፒታሎች ጋር የምንዋዋለው ምንድነው? እነሱ በየሳምንቱ ለሳምንት የሚበቃ ደም ይወስዳሉ። ከዚያ በኋላ በየወሩ ያላቸውን አፈፃፀም ሪፖርት እንዲያደርጉ ይጠበቃል፡፡ እስካሁን ሪፖርት አላደረጉም፡፡ ወደፊት ግን ምን ያህል ደም ወሰዱ፣ ምን ያህሉ ጥቅም ላይ ዋለ---የሚለውን ሪፖርት እንዲያደርጉ ይገደዳሉ፡፡ በዚህ መልኩ ነው የምንከታተለው። ይህን ሲስተም ከሁለትና ከሶስት ሳምንት በኋላ ደረጃውን ከሚያሟሉ ሆስፒታሎችና ጤና ተቋማት ጋር እንፈራረማለን፡፡ ከዚያም ለሚወስዱት ለእያንዳንዱ ከረጢት ደም ተጠያቂ ይሆናሉ፡፡  

Saturday, 22 March 2014 12:19

የቀልድ - ጥግ

አንዷ ሴት ለአንድ የወንድ ጓደኛዋ፡-
“የማገባው ሰው”
ወንድ - “እሺ?”
ሴት -  “በጣም የሚያዝናናኝ መሆን አለበት”
ወንድ -“እሺ?”
ሴት     “ሙዚቃዊ ድምፅ ሊኖረው ይገባል
ወንድ  “እሺ?”
ሴት     “ጆክ ሊያወራልኝ ይገባል”
ወንድ  “እሺ?”
ሴት     “መዝፈን መቻል አለበት”
ወንድ  “እ..ሺ?”
ሴት     “መደነስ መቻል አለበት”
ወንድ  “እ..ሺ?”
ሴት     “ሁሌ እቤት ውስጥ መገኘት አለበት”
ወንድ  “እ..ሺ?”
ሴት     “መረበሽ የለበትም በፈለኩ ጊዜ ዝም በል ስለው ዝም ማለት አለበት”
ወንድ    “አይ የኔ እህት አንቺ ባል አይደለም የፈለግሽው”
ሴት     “ታዲያ ምንድን ነው የምፈልገው?”
ወንድ  “ቴሌቪዥን!”
*   *   *
ልጅቷ ከአንድ ፕሮፌሰሯ ጋር አድራ መጥታለች፡፡ ጓደኛዋን አግኝታት፤
“ማታ ያወጣሁት ፕሮፌሰር የመጨረሻ ዝንጉና ማስታወስ የማይችል ሰው ነው”
ጓደኛዋ - “በምን አወቅሽ?”
ልጅቷ - “ዛሬ ጠዋት ክላስ ውስጥ ማርካችንን ሲሰጠን ዜሮ ነው ለእኔ የሰጠኝ!”
ትርጓሜ
የገርል ፍሬንድና ቦይ ፍሬንድ ጠበሳ ታሪክ በሊፕ-ስቲክና በሞፕ-ስቲክ (የቤት መጥረጊያ እንጨት) መካከል ያለ ታሪክ ነው፡፡
*   *   *
አንድ የገነገነ በሬ ወደሱ ሲመጣ ያየ ወንድ ፈጥኖ ወደ ኋላ ሸሸ፡፡ ይሄኔ ገርል-ፍሬንዱ፤
“ምነው ፍቅሬ! እንደዚህ ፈሪ ነህ እንዴ? ሞት ቢመጣ እጋፈጥልሻለሁ ስትለኝ አልነበረም እንዴ?”
ቦይፍሬንዷም፤
“አዎ የኔ ቆንጆ ብዬ ነበር፡፡ ይሄ በሬ ግን ከነነብሱ ነው የመጣብን!”