Administrator

Administrator

የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ መሪና የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊ ሁኔታ መጀመሩን ገልጸዋል።

በምርጫ ጣቢያዎች የተመለከቱት ነገር መልካም እንደነበር የጠቀሱት ኬንያታ፤ ይህ በሰላምና በሥርዓት የመምረጥ ሂደት ቀኑን ሙሉ እንዲቀጥል ተመኝተዋል።

“ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋና ከተማ ናት፤ በዚህች ሀገር የሚመዘገብ ስኬት ለመላው አህጉር ብርሃን ነው” በማለት ለኢትዮጵያ ሕዝብ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመዲናዋ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ድምጽ ሰጥተዋል።

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።

የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍፃሜ ተፋላሚ የነበረው አርሰናል ባሁኑ ሰአት በእንግሊዝ ሰሜን ለንደን ከሁሉም ተጫዋቾቹና ደጋፊዎቹ ጋር በመሆን የፕሪምየር የሊጉ አሸናፊነታቸውን በጎዳና ላይ ትርዒት እያወጁ ይገኛል።

1) እኛ ሰላም ያጣነው እንዲሁ በድንገት አይደለም፤ ሆን ብለን ሰርተንበት (ለፍተንበት) እንጂ። ዛሬም ለመሳሪያ ይዘፈናል። ዛሬም የገዳይ ልጅ ነኝ ይባላል። ፉከራ አለ። እኛ ከእንትና የበለጥን ጀግኖች ነን ይባላል። ዛሬም ልጆች በጦርነት ድምፅ መሃል ያድጋሉ።
ከዛ፣ ምን መዓት መጣብን?
2) በቅርብ ታሪካችን ውስጥ ሰዎች የሰሩት ትልቁ ስህተት መንግስትን እንደ ጓደኛ ማሰባቸው ነበር። መንግስት መቼም ቢሆን ያንተ ጓደኛ አይደለም። መንግስትን መግራት አትችልም። መንግስት የምትጠላቸውን ሰዎች ሲያጠቃ አንተም አብረኸው ልታጠቃ ትችላለህ፤ ነገር ግን መንግስት አድኖ በልቶ ሲጨርስ፣ ወደ እሱ በጣም ተቃርቦ የሚገኘው ማን እንደሆነ ገምት?
#NoMore ብለህ ጮኸህ፣ ድምፅህ ሰልሎ ወደ ቤትህ ልትገባ ስትል፣ A little more ብሎ ለእራት ያውልሃል። መንግስት ውለታ አይቆጥርም። እነዚህ ደግሞ የባሱት ናቸው ስንል፣ አብረን ያጠናከርናትና በር የከፈትንላት (Enable ያደረግናት) ዓመፅ እንዳለችም ማስታወስ ደግ ነው። ለነገ ይጠቅም ይሆናል።
3) ወላጆቻቸው ሕይወታቸውን ኦርጋናይዝ ሊያደርጉ ሲሞክሩ የሚበሳጩ (ነፃነት የሚፈልጉ) ሰዎች፣ ለምን የጓደኞቻቸው ሕይወት ላይ 60 በመቶ አክሲዮን እንዳላቸው ይሰማቸዋል?
ተቃርኖ የዓለም ገፅ ስለሆነ ወይስ ኑሯችንን በተለየ መልኩ እየደገምን የምንኖር ሆነን?
4) "እያንዳንዱ በራሱ መንገድ ይኑር" (To each their own) ጥሩ አባባል ነው።
የሕይወት ትርጉም በእጃችን የለም። እንደ እቃ ሸመታ የተመቸንን ነው የምንመርጠው። በዛ ውስጥ የዳኝነት ወንበርን ተሻምተው የሚገዙ ብዙ አሉ። አትፍረድ የሚለውን ትዕዛዝ ለአማኞች ትተን፣ ስለሕይወት ውስብስብነት፣ ስለሰዎችም መልከ ብዙነት፣ እሱንም ስለመቀበል፣ "ራስህ ሁን፣ ሌሎችንም እንዲሆኑ ፍቀድ" (Be and let others be) ለሚለው ሐረግም አሜን ብንል!
5) ድል ለአርሰናል! እና ለሰፊው ሕዝብ ፡)
Agegeheu Asegid-
ከዝግጅት ክፍሉ፡- ከላይ የቀረበው ጽሁፍ መጠነኛ አርትኦት ተደርጎበታል፡፡ ኦሪጂናል ጽሁፉን እንደወረደ ከጸሃፊው ፌስቡክ ገጽ ላይ ታገኙታላችሁ፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ደኔሮ በአዲስ አበባ የሚገኘውን የጣልያን ኤምባሲ ምክትል አምባሳደር ሚ/ር ሉካ ካርፔንትዬሪን በቢሮአቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በሁለቱ አካላት መካከል በተደረገው የትውውቅና የውይይት መድረክ ላይ በቀጣይ ጊዜያት በጋራ ሊከናወኑ በሚችሉ የፖሊስና የፀጥታ ተግባራት ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።
በውይይቱ ወቅት ምክትል አምባሳደሩ ሚ/ር ሉካ ካርፔንትዬሪ፣ የኢትዮጵያና የጣልያንን የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት በማንሳት፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ በከተማዋ እያከናወነ ያለውን የፀጥታና የህግ ማስከበር ስራ አድንቀዋል። ኤምባሲያቸው ቀደም ሲል ለትራፊክ ሞተረኞች የሰጠውን ስልጠና ያስታወሱት ምክትል አምባሳደሩ፣ በቀጣይም ከፖሊስ ተቋሙ በሚቀርብ ፍላጎት ላይ ተመስርቶ ማንኛውንም ዓይነት ድጋፍና ትብብር ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ሌተናል ጀነራል አስራት ደኔሮ በበኩላቸው፣ አዲስ አበባ የበርካታ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶችና የኤምባሲዎች መገኛ መሆኗን ጠቅሰው፣ የመዲናዋን ሰላምና ደህንነት አስተማማኝ ለማድረግ ዋና ጠቅላይ መምሪያው ከተለያዩ የፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል። ምክትል አምባሳደሩ ላደረጉት ጉብኝት በማመስገን፣ በቀጣይም ከኤምባሲው ጋር በተለይም በከተማ ፀጥታና ደህንነት ዙሪያ ይበልጥ በጋራ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
በአፍሪካ አህጉር ውስጥ ሚሊየነሮች እንዴት እንደተሰራጩ አስበው ያውቃሉ? የቅርብ ጊዜው የ"Henley & Partners" መረጃ እንደሚያመለክተው ደቡብ አፍሪካ ከአህጉሪቱ ባለጸጎች መካከል ሲሶ የሚሆነውን በመያዝ ቀዳሚውን ስፍራ ስትይዝ፣ ግብፅና ሞሮኮ በደረጃው በቅርብ ርቀት ይከተላሉ።
የአፍሪካ አገራት በሚሊየነሮች ብዛት (በሺዎች) እንደሚከተለው ተቀምጠዋል፦
ደቡብ አፍሪካ: 41.1ሺህ (33.6%)
ግብፅ: 14.8ሺህ (12.1%)
ሞሮኮ: 7.5ሺህ (6.1%)
ናይጄሪያ: 7.2ሺህ (5.9%)
ኬንያ: 6.8ሺህ (5.6%)
ሞሪሸስ: 4.8ሺህ (3.9%)
አልጄሪያ: 2.7ሺህ (2.2%)
ጋና: 2.6ሺህ (2.1%)
ናሚቢያ: 2.5ሺህ (2.0%)
ኢትዮጵያ: 2.4ሺህ (2.0%)
እነዚህ አኃዞች በበርካታ የአህጉሪቱ አገሮች ውስጥ እየታየ ያለውን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገትና በአፍሪካ ያለውን ተለዋዋጭ የኢንቨስትመንት ገጽታ በግልጽ ያሳያሉ።
Great Africa-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
በኩዌት አዲስ ተጋቢዎች የጋብቻ ቃል ኪዳን ካሰሩ ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ በመፋታታቸው በማህበራዊ ሚዲያ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል። በሀገሪቱ ታሪክ አጭሩ ጋብቻ ተብሎ የሚገመተው ይህ እንግዳ ክስተት ሙሉ በሙሉ የተፈጸመው በአካባቢው በሚገኝ የአውራጃ ፍርድ ቤት ውስጥ ነበር። ጥንዶቹ በዳኛ ፊት ይፋዊ የጋብቻ ውላቸውን ፈርመው ከአዳራሹ ለመውጣት ሲዞሩ፣ ሙሽራዋ በድንገት እግሯ ተጠልፎ ወደቀች። በዚህ ጊዜ ሙሽራው እሷን ከማንሳት ወይም ከማጽናናት ይልቅ፣ "ደደብ" በማለት ዘለፋት።
የሙሽራው ስድብ ሙሽራዋን ያስቆጣት ሲሆን፣ ይህ የክብር ማጣት ወደፊት አብረው ለሚኖራቸው ህይወት የማስጠንቀቂያ ምልክት እንደሆነ ተረዳች። በሰርግ ቀኗ በህዝብ ፊት የተሰማትን ውርደት ለመታገስ ፈቃደኛ ያልሆነችው ሙሽራ፣ በቀጥታ ወደ ዳኛው ዘወር በማለት ጋብቻው በዚያው ቅጽበት እንዲፈርስ ጠየቀች። ዳኛውም በሁኔታው ላይ ያላትን ህጋዊ መብት በመገንዘብ ጥያቄዋን ተቀብሎ ጋብቻውን ወዲያውኑ ውድቅ አደረገው።
ይህ ታሪክ በበይነመረብ ላይ ከፍተኛ የድጋፍ ማዕበል ያስከተለ ሲሆን፣ በርካታ ሰዎች ለሴትየዋ ፈጣን ውሳኔ አድናቆታቸውን ገልጸዋል። መሰረታዊ መከባበርና መተሳሰብ የሌለው ግንኙነት ገና ከመጀመሪያው የፈረሰ መሆኑን በመጥቀስ፣ የወሰደችው እርምጃ ትክክል መሆኑን ብዙዎች አረጋግጠዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
የደቡብ ሱዳን መንግሥት፣ ግብፅ በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው የላይኛው ናይል ግዛት ፓጋክ አካባቢ ያቋቋመችውን ወታደራዊ ጦር ሠፈር በአስቸኳይ እንድትዘጋ ማዘዙን የዓረብኛ የዜና ምንጮች በሰፊው ዘግበዋል። ይህ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ የተገነባውና ወታደራዊ ሥልጠና የመስጠት እንዲሁም የናይል ወንዝ ፍሰትን የመቆጣጠር ስውር ዓላማ የነበረው ጦር ሠፈር፣ የሥልጠና ባለሙያዎችን ጨምሮ 260 የሚያህል የሰው ኃይል አሰማርቶ የነበረ መሆኑ ታውቋል።
የደቡብ ሱዳን ውሳኔ በምሥራቅ አፍሪካ ያለውን የኃይል ሚዛን የሚቀይር ሲሆን፣ ታዛቢዎች እርምጃውን አገሪቱ በቅርቡ ከፈረመችው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት ጋር በቀጥታ ያያይዙታል። ጁባ የወሰደችው ይህ ቁርጠኛ አቋም፣ በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ዙሪያ በግብፅና በኢትዮጵያ መካከል ላለው ውጥረት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ከመሆኑም በላይ፣ ካይሮ በታችኛው ናይል ተፋሰስ አገራት ላይ የነበራትን የቆየ ተጽዕኖ በእጅጉ የሚፈታተን ሆኗል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
 
 
በኬንያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው ውድድር ብሔራዊ ቡድኑ በወንዶች ከ75 ኪሎ ግራም በታች እና ከ53 ኪሎ ግራም በታች፣ እንዲሁም በሴቶች ካታ እና በቡድን ኩሚቴ ባሳየው ድንቅ ብቃት አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን አሸንፏል።
በተጨማሪም በወንዶች ከ67 ኪሎ ግራም በታች እና በቡድን ካታ ውድድር ሁለት የብር ሜዳሊያዎች ተገኝተዋል።
Page 4 of 808