Administrator

Administrator

 ከብዙ አመታት በፊት ሁለት ለአካለ ትግል የደረሱና በተቃዋሚ ፓርቲ ውስጥ ይታገሉ የነበሩ ጓዶች ነበሩ፡፡ ከተወሰነ ወቅት በኋላ የነበሩበትን ፓርቲ ትተው ዓላማቸውን ቀይረው በጊዜው ወደነበረው መንግሥት ገቡ፡፡ በዚያ መንግሥት ውስጥም እንደ አንድ ኮሚቴ ሆነው እንዲሰሩ በመወሰኑ በኮሚቴ ሃላፊነት አንድ ሻምበል ተመድቦላቸው የፖለቲካ ጥናታቸውን ቀጠሉ፡፡ ተጠመቁ፡፡ አመኑ፡፡ መልካም ኑሮ ያገኙ መሰሉ፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ከሁለቱ ወጣቶች አንደኛው ወደ ወዳጅ አገር ወደ ኩባ ለአጭር ጊዜ ስኮላርሺፕ አገኘና ሄደ፡፡
ተምሮ፣ ተመራምሮ፣ የፖለቲካ ንቃቱን አዳብሮ፣ አንቱ ተብሎ፣ በስኮላርሺፕ የሚቆይበት ጊዜ አልቆ ወደ እናት አገሩ ተመልሶ መጣ፡፡ ወደ እናት ኮሚቴው ለመግባትም አገር ውስጥ ይጠብቀው ወደነበረው ጓደኛው  ሄደና አገኘው፡፡
ሆኖም ሰብሳቢያቸው የነበረው፤ የኮሚቴያቸው መሪ ሻምበል ዛሬ የለም፡፡ ከኩባ የመጣው ወጣት እዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ የቆየውን ወጣት “ኧረ የሆነስ ሆነና ጓድ ሻምበልስ ወዴት አለ?” ሲል ጓደኛውን ጠየቀ፡፡
ጓደኛውም እያመነታ፤
“ለካ አልሰማህምና! ጓድ ሻምበል እኮ ታስሯል” ይለዋል ሲፈራ ሲቸር፡፡
ከኪዩባ የመጣው ወጣት ክው አለ፡፡ ግራ ገባው፡፡ “እንኳን አሰሩት” እንዳይል ነገ ምን ሊከተል እንደሚችል፣ ጓድ ሻምበል ይፈታ አይፈታ፣ ተፈቶም ወደ ኮሚቴው ይመለስ አይመለስ ምንም የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ በአንፃሩ “እሱን የመሰለ ጓድ እንዴት ይታሰራል?” ብሎ እንዳይሟገት ደግሞ ገና እሥሩ አላበቃም፡፡ በማን ላይ እንደሚቀጥል ስለማይታወቅ ያስፈራል፡፡ ስለዚህ ጥንቃቄ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ጓደኛው ምን ይል ይሆን እያለ እየጠበቀ አፍ-አፉን ያየዋል፡፡
ያም ከኩባ ተመላሽ ሲጨንቀው ቆይቶ እንዲህ አለ፡-
“አቤት የአብዮታችን ፍጥነት!!”
****
አለመተማመንና ጥርጣሬ የነገሰበት ወቅት የፍርሃት እናት ነው፡፡ ሰው የልቡን አያወራም፡፡ ጓደኛና ጓደኛ በጎሪጥ ይተያያል፡፡ መከዳዳት የእለት - የሰርክ ጉዳይ ይሆናል- እንደውም ይለመዳል፡፡ ጠብታዋ ነገር ሰፍታ ጎርፍ ትሆናለች፡፡ በጦርነት ከሚረታው በወሬ የሚረታው ይበልጣል፡፡ የበታች የበላዩን ይፈራል እንጂ አያከብርም፡፡ ይታዘዛል እንጂ አያምንም፡፡ የበላይ የበታቹን በትንሽ-በትልቁ ይጠራጠራል፡፡ ያሴርብኛል እንጂ ያግዘኛል የሚል እምነት የለውም፡፡ አለቅየው ቅንጣት ታህል ጥፋት ሲያይ ከምድር-ከሰማይ ጉዳይ ጋር አገናኝቶ በእኔ ላይ የተቃጣ ተንኮል ነው ሲል ይደመድማል፡፡ ሁሉ ነገር ወዴት እንደሚያመራ ስለማይታወቅ በጥንቃቄና በፍርሃት መካከል ልዩነት ይጠፋል፡፡ ሰላምታው ስድብ፣ ስድቡ ሰላምታ የሚመስልበት ሁኔታ ይፈጠራል፡፡ ፈሪው ከፍርሃቱ ብዛት ጀግና ይሆናል፡፡ እንቅፋቱ ሁሉ ለሞት ያበቃኛል ስለሚል የተከላከለ መስሎት አጥቂ ይሆናል፡፡ “የሚያባርረኝ ጣሊያን እንቅፋት መትቶት በሞተ አርበኛ ነህ አሉኝ እንጂ እኔስ አርበኛ አደለሁም!” እንዳለው የሃገራችን ሰው መሆኑ ነው፡፡ ጀግናው ደግሞ ከጥንካሬው ብዛት ፈሪ ይሆናል፡፡ ትንኟን በአቶሚክ ቦንብ ይገድላል፡፡ ለዚህም አላጨበጨባችሁልኝም ብሎ አገር ምድሩን ያኮርፋል፡፡ መጨካከን እንደ ዋዛ ይለመዳል፡፡ ስርቆትና ምዝበራ “ቢዝነስ ተሰራ” ይሰኛል፡፡ ከእያንዳንዱ ሃብት ጀርባ ያለው ወንጀል እንደ ጥበበኛነትና እንደ ጀብድ እንደሚቆጠር ሁሉ፤ በእያንዳንዱ መሸናነፍ ጀርባ ያለው ደግሞ እንደ አላማ ፅናት፣ ቆራጥነት፣ መስዋእትነት ይታያል፡፡ በዚህን አይነት ሰአት ብዙ ክስተት የድንገቴና የዱብ-እዳ እንጂ በሂደት የመጣ አልመስል ይላል፡፡ አብዛኛው ነገር የማይታይ ፍልሚያ (The invisible conflict እንዲል መፅሐፍ) አይነት ይሆናል፡፡ ህቡኡ የአደባባይ አዋጅ ፣ የአደባባይ አዋጁ ህቡእ የመምሰል ባህሪ ያመጣል፡፡ ወዴት እየሄድን ይሆን? የሚለው ጥያቄ የሁሉ ሰው ጥያቄ ይሆናል፡፡ የአለቃም የምንዝርም! አንድ ጊዜ አንድ አብዮት አደባባይ ለመሰለፍ የወጡ አሮጊት “የዛሬው ሰልፍ አላማ ምንድን ነው?” ብሎ ጋዜጠኛ ቢጠይቃቸው፤ “ቆይ እንጂ አትቸኩል ገና ሹሞቹ መጥተው መች ነገሩን!” አሉት አሉ፡፡ የሚያገባንን ጉዳይ ሁሉ መስማት መቻል አለብን፡፡ በሃገር ደረጃ የተለየ ችግር የሚፈጥር ካልሆነ በቀር፡፡
ህዝብ በየጊዜው የሚካሄደውን ነገር ማወቅ ይፈልጋል፡፡ በየወቅቱ የሚደረገውን ሃገራዊም ሆነ ከሃገር ጋር የተያያዘ አለም-አቀፍ እንቅስቃሴ እንዲገባው ይፈልጋል፡፡ አፍንጫው-ስር የሚከናወን ድርጊት ላይ አፍጦ አርቆ ማስተዋል እንዳያቅተው፣ ሩቅ ሩቅ እያየ የቆመበት ምንጣፍ ከእግሩ ስር ተስቦ እንዳይወሰድ፤ ማንኛውም ኢንፎርሜሽን ሊነገረው ይገባል፡፡ አለበለዚያ ስለነገ ያለው ተስፋና ግምት በፍርሃትና ጥርጣሬ የተሞላ ይሆንና “አቤት የአብዮታችን ፍጥነት!” ሲል የሚገኝ የራሱ አቋም የሌለውና “ዛሬን እንደምንም ልደር ብቻ” የሚል ዜጋ መፈልፈል ይሆናል እጣችን፡፡ ታመመ ሲሉ ሞተ ፣ ወደቀ ሲሉ ተሰበረ ማለት ቅርብ በሆነበት ዘመን፣ ህዝብ ላለማመን ቅርብ ቢሆን አይገርምም፡፡ አጋጣሚን መሾሚያ መሸለሚያ የሚያደርግ የሚበዛበት ጊዜ ቢፈጠርም አይገርምም፡፡ ሔልሙት ክሪስት የተባለ አንድ ደራሲ፤ The rottener the time the easier it is to get promoted  እንዳለው ነው፡፡ (ጊዜው የበለጠ እየነተበ በመጣ ቁጥር በቀላሉ መሾምና እድገት ማግኘት እየበዛ ይሄዳል እንደማለት ነው፡፡) የቢሮክራሲ ንቅዘት፣ የአመለካከት ክስረት፣ የአዛዥነት አስተሳሰብ፣ የእሺ-ባይነት ኩራት፣ ከሁሉ-በላይ ነኝ የሚል ስሜት፣ የጌታና የሎሌ ግንኙነት፣ የመቻቻል ድህነት፣ የሙስና ጌትነት ወዘተ ሁሉም የተሳሰሩና የተሳሰረ ፖለቲካዊና ማህበራዊ እንዲሁም ታሪካዊ ምንጮች ያሏቸው ጉዳዮች ናቸው፡፡ የህዝብ ጥርጣሬና ፍርሃት ሲከሰትና ነገ ምን ይፈጠር ይሆን? እያለ መስጋትና መጠየቅ ሲበዛ፣ እነዚህን ምንጮች በጥሞና መመርመር ያሻል፡፡ እንደ ሲዳማ ህዝባዊ አባባል “አይጧ ከሌለች ጉድጓዱ ከየት መጣ?” ማለት አለብን፡፡     



ዘመን ባንክ፤ አዲሱን የዋና መሥሪያ ቤቱን ህንጻ ዛሬ ያስመርቃል

         የዛሬ 15 ዓመት፣ በ87.2 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል፣ የባንክ ኢንዱስትሪውን  የተቀላቀለው ዘመን ባንክ፣ አዲሱንና ዘመናዊውን ባለ 36 ወለሎች የዋና መሥሪያ ቤቱን ህንጻ በዛሬው ዕለት  ያስመርቃል፡፡
የዘመን ባንክ  አመራሮች  ከትናንት በስቲያ ሐሙስ፣ በአዲሱ የዋና መሥሪያ ቤት ህንጻ  መግለጫ የሰጡ ሲሆን፣ የባንኩን ያለፉ ዓመታት የሥራ አፈጻጸምና የአዲሱን ህንጻ መጠናቀቅ አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በአዲስ አበባ የፋይናንስ ማዕከል ተብሎ በሚታወቀው ሰንጋ ተራ አካባቢ የተገነባው

የዘመን ባንክ  የዋና መሥሪያ ቤት ህንጻ አምስት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን፤የግንባታው አጠቃላይ ወጪ ወደ 1.5 ቢሊዮን ብር እንደሚደርስ ተነግሯል፡፡
የዋና መ/ቤቱ ህንጻ መጠናቀቅ ተበታትነው የቆዩትን የባንኩን የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ወደ አንድ ህንጻ በመሰብሰብ ለደንበኞቹም ሆነ ለራሱ ወጪ ቆጣቢ፣ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችለው ተገልጧል፡፡
አዲሱ ህንፃ ባንኩ በየዓመቱ ለህንጻ ኪራይ ሲያወጣው የነበረውን ከ40 ሚ. ብር በላይ እንደሚያስቀርለት የተናገሩት የዘመን ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደረጀ ዘበነ ፤” አዲሱ ህንጻ ለባለአክሲዮኖቻችን ሃብት፣ ለደንበኞቻችን ደግሞ ዋስትና ነው” ብለዋል፡፡የባንኩ ዘመናዊ ህንጻ ሁሉንም የግንኙነት አማራጮችን በቴክኖሎጂ ያቀፈ፣ የመረጃ መሰብሰቢያና ማደራጃ እንዲሁም መተንተኛ ማዕከላት ያሉት ነው ተብሏል፡፡
በ2300 ካሬ ሜትር ስፋት ላይ ያረፈው ህንጻው፤ እስከ 200 የሚደርሱ ተሳታፊዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው የስብሰባ አዳራሾች፣ እያንዳንዳቸው 13 ተሳፋሪዎችን የሚያጓጉዙ አሳንሰሮች፣ 200 ተሽከርካሪዎችን ማቆየት  የሚያስችሉ የምድር ቤትና ፎቅ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎችን ይዟል፡፡


ግንባታውን ያከናወነው China W

u Yi CO. LTD የተሰኘ የቻይና መንግሥት ተቋራጭ ኩባንያ መሆኑ ታውቋል፡፡


ባለፈው 2021/22 በጀት ዓመት የባንኩ ትርፍ ከታክስ በፊት 2.1 ቢሊዮን ብር እንደነበር ያስታወሱት የባንኩ አመራሮች፤ ይህም ባንኩ ከተመሰረተ ጀምሮ ካስመዘገበው ትርፍ ከፍተኛው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ያለፉት አምስት ዓመታት የትርፍ ድርሻ በአማካይ 40 በመቶ መድረሱንም አክለው ገልጸዋል፡፡
የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ በአሁኑ ሰዓት ከ35 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱ የተገለጸ ሲሆን፤የባንኩ አጠቃላይ ካፒታል ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱና የተከፈለው ካፒታል መጠን 4.7 ቢሊዮን ብር መሆኑ ተመልክቷል፡፡ 100 የሚደርሱ ቅርንጫፎች ያሉት ዘመን ባንክ፤ ከ40 ቢሊዮን ብር በላይ ጠቅላላ ሃብት እንዳለው  ታውቋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ መረጃው ያልተጣራና ከአንድ ወገን ብቻ የተገኘ ነው ብሏል

        በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ እየተካሄደ ያለው ዜጎችን በግዳጅ የማስነሳትና ቤቶችን የማፍረስ ሂደት 100ሺ ቅሬታዎች እንደቀረቡበት ተገለፀ፡፡ የከተማ አስተዳደሩ መረጃው ያልተጣራና ከአንድ ወገን ብቻ የተገኘ ነው ሲል አስተባብሏል፡፡የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ በሸገር ከተማ “ህገወጥ ግንባታ” በሚል እየተካሄደ ካለው የቤት ፈረሳ ጋር በተያያዘ ከአንድ መቶ ሺ በላይ አቤቱታዎች እንደቀረቡለት ገልጿል፡፡
ተቋሙ በተያዘው በጀት አመት ከ133ሺ በላይ አቤቱታዎችን መቀበሉን ገልፆ፤ ከዚህ ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ያለው በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ውስጥ እየተካሄደ ካለው የቤት ፈረሳ ጋር የተያያዙ አቤቱታዎች እንደሆኑም አመልክቷል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ “ህገወጥ ግንባታ” ናቸው እያለ ለሚያፈርሳቸው የመኖሪያ ቤቶች ለነዋሪዎች ምትክ ቦታ እንደማይሰጥና ለተፈናቃዮችም ጊዜያዊ መጠለያ እንዳልተዘጋጀላቸው የገለፀው የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ይህ ሁኔታም ተቋሙን እጅግ እንዳሳሰበውና መንግስት አስቸኳይ መፍትሄ ሊሰጠው እንደሚገባ አመልክቷል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ በከተማው እየፈረሱ ያሉት ቤቶች በህገወጥ መንገድ የተገነቡና የግንባታ ፈቃድ የሌላቸው ቤቶች መሆኑን ጠቁሞ፤ እርምጃው የህግ የበላይነትን ከማስከበር ጋር የተያያዘ ነው ብሏል፡፡
በህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የተገለፀውና 100ሺ ቅሬታዎች ቀረቡበት የተባለው ጉዳይም ከእውነት የራቀ፣ ውይይት ያልተደረገበትና፣በአግባቡ ያልተጣራ እንዲሁም ከአንድ ወገን ብቻ በተገኘ መረጃ ላይ የተመሰረተ ነው ሲል አስተዳደሩ አስተባብሏል፡፡



 ከ16 አገራት የተውጣጡ 130 ኩባንያዎች ይሳተፉበታል

       5ኛው ʺአግሮፉድ ኢትዮጵያ እና ፕላስትፕሪንትፓክ ኢትዮጵያʺ ዓለማቀፍ የንግድ ትርኢት፣ ከሰኔ 1- 3 ቀን  2015 ዓ.ም ለሦስት ተከታታይ ቀናት በሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡በንግድ ትርኢቱ ላይ የግብርና፣ ምግብ ማቀነባበሪያ፣ የምግብ ግብዓት ንጥረነገሮች፣ ፕላስቲክ፣ ህትመትና ማሸጊያ ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም  መፍትሄዎች ይቀርባሉ ተብሏል፡፡
የንግድ ትርኢቱ አዘጋጆች ባለፈው ሰኞ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም  በስካይ ላይት ሆቴል ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
አዘጋጆቹ በመግለጫው ላይ እንደጠቆሙት፤ በንግድ ትርኢቱ ላይ  ከ16 አገራት የተውጣጡ  130 ድርጅቶች የሚሳተፉ ሲሆን  አገራቱም ኢትዮጵያን ጨምሮ ኦስትሪያ፣ ቡልጋሪያ፣ ቻይና፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ህንድ፣ ጣሊያን፣ ዮርዳኖስ፣ ኬንያ፣ ኮሪያ፣ ኩዌት፣ ኔዘርላንድስ፣ ታይዋን፣ ታይላንድና ቱርክ ናቸው፡፡ ትርኢቱን ከ3ሺ  በላይ ሰዎች ይጎበኙታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በንግድ ትርኢቱ ላይ ከቻይና የመጡ ከ60 በላይ ኩባንያዎች የሚሳተፉ  ሲሆን፤ ከኩዌት የመጡ  8 ድርጅቶችም ተሳታፊ  እንደሚሆኑ ታውቋል፡፡
“በኩዌት አምርቱ” የንግድ ትርኢቱ  የወርቅ ስፖንሰር  ነው ተብሏል፡፡  
5ኛው አግሮፉድ ፕላስትፕሪንትፓክ ኢትዮጵያ ዓለማቀፍ የንግድ ትርኢት የተዘጋጀው፣  በጀርመኑ የንግድ ትርዒት ስፔሽያሊስት ፌር ትሬድ መሴ እና በኢትየጵያው አጋሩ  ፕራና  ኢቨንትስ ትብብር ነው፡፡

 የዛሬ 15 ዓመት፣ በ87.2 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል፣ የባንክ ኢንዱስትሪውን  የተቀላቀለው ዘመን ባንክ፣ አዲሱንና ዘመናዊውን ባለ 36 ወለሎች የዋና መሥሪያ ቤቱን ህንጻ የፊታችን ቅዳሜ ያስመርቃል፡፡

የዘመን ባንክ ማናጅመንት በዛሬው ዕለት ከሰዓት በኋላ በአዲሱ የዋና መሥሪያ ቤት ህንጻ  መግለጫ የሰጠ ሲሆን፣ የባንኩን ያለፉ ዓመታት የሥራ አፈጻጸምና የአዲሱን ህንጻ መጠናቀቅ አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡

በአዲስ አበባ የፋይናንስ ማዕከል ተብሎ በሚታወቀው ሰንጋ ተራ አካባቢ የተገነባው የዘመን ባንክ አዲስ የዋና መሥሪያ ቤት ህንጻ አምስት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን፤ግንባታው በ1.2 ቢሊዮን ብር ቋሚ ክፍያ የተጀመረ ቢሆንም፣በተለያዩ ምክንያቶች በተፈጠረ መዘግየትና የዲዛይን ለውጥ አሁን ላይ አጠቃላይ ወጪው ወደ 1.5 ቢሊዮን ብር እንደሚደርስ ተገምቷል፡፡

የዋና መ/ቤቱ ህንጻ መጠናቀቅ ተበታትነው የቆዩትን የባንኩን የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ወደ አንድ ህንጻ በመሰብሰብ ለደንበኞቹም ሆነ ለራሱ ወጪ ቆጣቢ፣ ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችለው ተገልጧል፡፡

አዲሱ ህንፃ ባንኩ በየዓመቱ ለህንጻ ኪራይ ሲያወጣው የነበረውን ከ40 ሚ. ብር በላይ እንደሚያስቀርለት የተናገሩት የዘመን ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደረጀ ዘበነ ፤”አዲሱ ህንጻ ለባለአክሲዮኖቻችን ሃብት፣ ለደንበኞቻችን ደግሞ ዋስትና ነው” ብለዋል፡፡

የባንኩ ዘመናዊ ህንጻ ሁሉንም የግንኙነት አማራጮችን በቴክኖሎጂ ያቀፈ፣ የመረጃ መሰብሰቢያና ማደራጃ እንዲሁም መተንተኛ ማዕከላት ያሉት ነው ተብሏል፡፡

በ2300 ካሬ ሜትር ስፋት ላይ ያረፈው ህንጻው፤ እስከ 200 ተሳታፊዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው የስብሰባ አዳራሾች፣ እያንዳንዳቸው 13 ተሳፋሪዎችን የሚያጓጉዙ አሳንሰሮች፣ 200 ተሽከርካሪዎችን ማቆየት  የሚያስችሉ የምድር ቤትና ፎቅ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎችን ይዟል፡፡

ግንባታውን ያከናወነው China Wu Yi CO. LTD የተሰኘ የቻይና መንግሥት ተቋራጭ ኩባንያ መሆኑ ታውቋል፡፡

ባለፈው 2021/22 በጀት ዓመት የባንኩ ትርፍ ከታክስ በፊት 2.1 ቢሊዮን ብር እንደነበር ያስታወሱት የባንኩ አመራሮች፤ ይህም ባንኩ ከተመሰረተ ጀምሮ ካስመዘገበው ትርፍ ከፍተኛው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ያለፉት አምስት ዓመታት የትርፍ ድርሻ በአማካይ 40 በመቶ መድረሱንም አክለው ጠቁመዋል፡፡

የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ በአሁኑ ሰዓት ከ35 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱ የተገለጸ ሲሆን፤የባንኩ አጠቃላይ ካፒታል ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱና የተከፈለው ካፒታል መጠን 4.7 ቢሊዮን ብር መሆኑ ተመልክቷል፡፡ 100 የሚደርሱ ቅርንጫፎች ያሉት ዘመን ባንክ፤ ከ40 ቢሊዮን ብር በላይ ጠቅላላ ሃብት እንዳለው  ታውቋል፡፡

•  ከ16 አገራት የተውጣጡ 130 ኩባንያዎች ይሳተፉበታል