Administrator

Administrator

Saturday, 14 June 2014 12:03

የፍቅር ጥግ

የምወድሽ ስለአንቺነትሽ ብቻ አይደለም። ካንቺ ጋር ስሆን ስለምሆነው እኔነቴም ጭምር ነው፡፡
ሮይ ክሮፍት
መፈቀርን ብቻ አይደለም የምፈልገው፤ መፈቀሬ እንዲነገረኝም እሻለሁ፡፡
ጆርጅ ኤልዮት
ሰዎችን ከፈረጅካቸው ለፍቅር ጊዜ አይኖርህም፡፡
ማዘር ቴሬዛ
አንቺ ለእኔ ጣፋጭ ስቃዬ ነሽ፡፡
                     ራልፍ ዋልዶ ኤመርሶን
ፍቅር ፈፅሞ ተፈጥሮአዊ ሞቱን ሞቶ አያውቅም፡፡ የሚሞተው ምንጩን ማደስ ስለማናውቅበት ነው፡፡ የሚሞተው በጭፍንነት፣ በስህተትና በክህደት ነው። የሚሞተው በህመምና በቁስል ነው። የሚሞተው በድካም፣ በመጠውለግና በመመረዝ ነው፡፡
አናዩስ ኒን
ቤተሰብ የሚጀምረው ከየት ነው? ጉብሉ ከኮረዳዋ ጋር በፍቅር ሲወድቅ ነው፡፡ ከዚህ የላቀ አማራጭ እስካሁን አልተገኘም፡፡
ሰር ዊንስተን ቸርችል
የተወለድነው ለብቻችን ነው፡፡ የምንኖረው ለብቻችን ነው፡፡ የምንሞተውም ለብቻችንን ነው፡፡ ብቻችንን አይደለንም የሚለውን ማስመሰል መፍጠር የምንችለው በፍቅርና በጓደኝነት አማካኝነት ብቻ ነው፡፡
ኦርሶን ዌልስ
ለእውነተኛ ፍቅር ጊዜም ሆነ ቦታ የለም። የሚከሰተው እንደ አጋጣሚ ነው፡፡ በልብ ምት፣ በአንዲት ብልጭታ፣ በትርታ ቅፅበት ነው፡፡
ሳሬ ዴሴን

         “ሉሲ እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች” የሚለው መፅሀፍ ላይ የሚከተለው ታሪክ ይገኛል፡፡
በድሮ ዘመን በጣም ደስተኛ የሆነ ሰው ከሚወዳት ሚስቱና ከአራት ወንዶች ልጆቹ ጋር ይኖር ነበር። የአንጋፋው ልጅ ስም ጥልቅ ዓይን ይባላል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ቆቁ ተባለ፡፡ ሶስተኛው ልጅ ጡንቸኛው የሚል ስም ተሰጠው፡፡ የመጨረሻው ትንሹ ልጅ ህፃን ስለነበር ስም አልተሰጠውም፡፡
አንድ ቀን በማለዳ እናታቸውና ልጆቹ ከመኝታቸው ሲነሱ አባታቸውን ከቤት አጡት፡፡ በሚቀጥለው ምሽትም ሳይመለስ ቀረ፡፡ በማግስቱም የአባታቸው ዱካ ጠፋ፡፡ ልጆቹ ከእናታቸው ጋር ብዙ ተወያዩ፡፡ ወዴት እንደሄደ ማንም የሚያውቅ የለም፡፡
እናታቸው ራሷን በሁለት እጆቿ ደግፋ ለቅሶና ጩኸቷን ለቀቀችው፡፡ ጥልቅ ዓይን “ምናልባት አጎታችንን ሊጠይቅ ሄዶ ይሆናል፡፡” አለ፡፡ “ድግስ ተጠርቶ ወደ ጎረቤት ሄዶ ይሆናል” ሲል ቆቁ የራሱን ግምት ሰጠ፡፡ “ምናልባትም ወደ ተራራ ወጥቶ ነፋስ እየተቀበለ ይሆናል” በማለት ጡንቸኛው የበኩሉን ግምት ተናገረ፡፡
ይሁንና አባታቸው እንደጠፋ ሳምንታት ተቆጠሩ፡፡ አልፎ አልፎ ልጆቹ ወደ ጫካና ወደ ተራራ ሄደው ከፍ ባለ ድምፅ አባታቸውን ይጣራሉ፡፡ መልስ ሳያገኙ ወደቤታቸው ይመለሳሉ፡፡ በሁኔታቸው እየተሰላቹ ስለሄዱ መፈለጉን አቆሙ፡፡
ሕፃን ወንድማቸው ግን እንደነሱ ተስፋ አልቆረጠም፡፡ አንድ ቀን ጧት እናቱ አቅፋው ሳለ፣ ህፃኑ ልጅ “አባቴ የት አለ? አባቴን እፈልጋለሁ፡፡” በማለት ለመጀመሪያ ጊዜ ተናገረ፡፡ ታላቅ ወንድሙ ጥልቅ ዐይን “እውነት ነው፡፡ አባባ የት አለ?” በማለት ሕፃኑን እየተመለከተ እርሱም ጠየቀ፡፡ “አሁኑኑ ተነስተን አጥብቀን ብንፈልገው ይሻላል” ሲል ጡንቸኛው አምርሮ ተናገረ፡፡
መፈለግ ቀጠሉ“ቆይ-ቆይ ከሩቅ ቦታ የለቅሶ ድምጽ ይሰማኛል፡፡ በዚህ በኩል… ጪኸት እየሰማሁ ነው! ተከተሉኝ!” በማለት ቆቁ አስገነዘበ፡፡ እንደ ጩኸቱ ቅርበትና ርቀት ቆቁ በተሰማው አቅጣጫ ተያይዘው ተጓዙ፡፡ በመጨረሻም ወደ አንድ ወንዝ ተቃረቡ፡፡ አባታቸው በወንዙ ዳርቻ በጦሩ ከወጋው አነር ጋር ተፋጦ አዩት፡፡ አነሩ የአባታቸውን እግር አቁስሎታል፡፡ “አባባን ማዳን ይገባናል!” በማለት ጡንቸኛው ጮኸ፡፡ በቅጽበት በጠንካራ ጡንቾቹ አነሩን አነቀው፡፡ የታነቀው አነር አየር አጥቶ ተዝለፍልፎ ወደቀ፡፡
“እጅግ አስፈላጊ በሆነ ሰዓት ደረሳችሁልኝ! ዘነጣጥሎ ይበላኝ ነበር፡፡ በጦር ብወጋውም አስቀድሞ አቁስሎኝ ስለነበር ደከመኝ፡፡ እህል ውሃም ስላልቀመስኩ ድካሜ ተባባሰብኝ፡፡ አመጣጤ የሚታደን ነገር ለማግኘትና ለእናንተ ለማምጣት ነበር” እያለ አባታቸው አስረዳ፡፡ ሁሉም ሰው “ጀግኖች ናቸው፡፡” በማለት አደነቃቸው፡፡
ወንድማማቾቹ ይህንኑ የሕዝብ አድናቆት ሰሙ፡፡ በመካከላቸው ታላቅና ኃይለኛ ጭቅጭቅ ተነሳ፡፡ አባታቸውን በማዳን ማን ዋነኛውን ተግባር (ሥራ) እንደሰራ ለማወቅ ይነታረኩ ጀመር፡፡ ጥልቅ ዐይን “እኔ ዱካውን (ኮቴውን) ባላየው ኖሮ አባታችን የሄደበትን አናውቀውም ነበር” አለ፡፡ ቆቁ በበኩሉ “ዱካው አንድ ቦታ ስንደርስ ጠፍቷል፡፡ እኔ የለቅሶውን ጩኸት ሰምቼ ባልመራችሁ ኖሮ አባታችንን ማግኘት አንችልም ነበር” ሲል ተከራከረ፡፡
“ሁለታችሁም ተሳስታችኋል፡፡ አባታችንን ብናገኘው ምን ዋጋ አለው፡፡ እኔ አነሩን ባልገልለት ኖሮ አባታችን እኮ በአነሩ ይበላ ነበር፡፡ ዋናው ክብር ለእኔ ይገባኛል!” እያለ ጡንቸኛው ደነፋ፡፡ ወደ አባታቸው ሄዱ፡፡ እርሱን በማዳን ረገድ ክብር የሚሰጠው ማን እንደሆነ እንዲነግራቸውም ጠየቁት፡፡
አባታቸውም “ሰማችሁ ልጆቼ እኔን በመታደጋችሁ ባለውለታዬ ናችሁ፡፡ ከሦስታችሁም እኔን አድኖ ለቤት ለማብቃት ትልቁን ክብር የሚያገኝ የለም፡፡ አንዳችሁም ትልቁን ክብር የሚያሰጥ ውለታ አልሰራችሁም፡፡ ለትልቁ ክብር የሚበቃ ሥራ የሰራው ይህ ህፃን ወንድማችሁ ነው፡፡  ክብር ለሕፃኑ ትንሽ ወንድማችሁ ይገባዋል፡፡ ጀግናችሁ ነው” በማለት አባታቸው ነገራቸው፡፡ ትንሹን ሕፃንም ታቀፈው፡፡
*         *        *
ትክክለኛው ክብርና ምሥጋና ለሚገባው ተገቢውን ክብር እንስጥ፡፡ የሌሎችን ዋጋ ለመውሰድ ጥቅማቸውንም ለመንጠቅ አንሞክር፡፡
በጨው ደንደስ በርበሬ ተወደስን አንመኝ! ዛሬ ሁለ-መናችንን ጠንቅቀን ለማየት ጥልቅ-ዐይን ያስፈልገናል፡፡ የምናየውንና የሚገጥመንን ሁሉ ያላግባብ እንዳንመዝንና የተሳሳተ ምላሽ እንዳንሰጥ ቆቅነት ያስፈልገናል፡፡ ይሄ ሁሉ ኖሮን ግን አቅም ማዳበር ካልቻልን ከንቱ ነው! በመጨረሻም እንደህፃን የዋህ የሆነ ልቡና ያሻናል - የምንፈልገውን ሁሉ በንፅህና ለመጠየቅ! ተስፋ የማይቆርጥ የህፃን መንፈስ ሁልጊዜም ያስፈልገናል፡፡ መሸለም ያለበትና ዘላቂው ተሸላሚ ይሄ ተስፋ የማይቆርጥ የነገ ተስፋ ነው!
ቻይናዎች ሁለት የፊደል ባህሪያትን አገጣጥመው ነው ድቀትን (Crisis)፣ የችግር ጊዜን፤ የሚተረጉሙት። ሁለቱ ባህሪያት ጣጣ (Risk) እና አጋጣሚ (Opportunity) ናቸው፡፡ አንድን ጉዳይ፣ (የችግር ጊዜ) ለማሸነፍ የሚያመጣውን ጣጣ ልንችል፣ ያሉንን አጋጣሚዎች ልንጠቀም ዝግጁ መሆን አለብን እንደማለት ነው፡፡ የሀገራችንን አያሌ ችግሮች እንዲህ ቆርጠን እንፍታቸው ካ›ልንና ዝግጁነት ካላሳየን፣ የውሃ ላይ ኩበት ነው የምንሆነው፡፡ ጣጣውን ችሎ አጋጣሚን ለመጠቀም መነጋገር,፣ መመካከር ፣ አዕምሮን ከአዕምሮ ማወዳደርና መደራጀት ያስፈልጋል፡፡ ዓለም ያለፈቻቸው አምስት ዘመናት አሉ፡፡ አንደኛው “ዓለም እኔን የምትሰማኝን ያህል ናት” ያልንበት ነው፡፡ ሁለተኛው “ዓለም እኔ ነች ብዬ የማስባት ናት” የምንልበት ነው፡፡ ሶስተኛው ዓለም እልቆ መሣፍርት የሌላት ማሽን ናት፡፡ እንዴት እንደምትሠራ እደርስባታለሁ” የምንልበት የሳይንስ ዘመን ነው፡፡ አራተኛው “ዓለም እኔ በፈጠርኳቸው ልዩ ልዩ ምናልባቶች የተሞላች ስትሆን ይምህ የእኔ አመለካከት ያመጣው ነው” የተባለበት ነው፡፡ በመጨረሻም፤ “የእኔ ዓለም ማናቸውም ቀመር (formulation) የማይወስነው መዋቅር ያላት ናት፡፡ እኔ ዓለምን የማያት ከሷ ጋር እንዳለኝ ጅምላ ልምድ ነው። እናም በራሴ ምልክት ስሪቶች (Symbolic constructs) ራሱን ነፃ በማውጣት መንፈስ እየተጫወትኩ፣ እየተንቀሳቀስኩ ነው” የምንልበት ዘመን ነው፡፡ የዓለምን ታሪክ ወደራሳችን ተርጉመን ፋይዳ ሰጥተን ካስተዋልነው፤ ለውጥ የማምጣትና የማሸነፍ ዕድል አለን፡፡
ቴድ ሲልቬይ የተባለ ፀሀፊ ይሄን ይላል “... ለደጋ ፍየሎች መረማመጃ የድንጋይ ደረጃ እንሰራለን። ለእንስሶች ማረፊያ ቤት እንሰራለን፡፡ ሌላው ቀርቶ ለእባብም የሚያስደስተውን የአየር ማረጋጊያ (Air conditioning) እናደርጋለን! ለሰው ልጅ ግን ተገቢውን መጠለያ፣ ለህፃናትም በቂ መኖሪያ ሥፍራ፣ አንሰጥም” ይላል፡፡ ለዜጎቻችን ቢያንስ መሰረታዊውን የቤት ችግር ማስወገድ - በተለይ ይሄ ሁሉ የቤት ሙስና ባለበት አገር - እጅግ ወሳኝ ነው፡፡ አናንቀላፋ፡፡ በግሪክኛ Hypnos - እንቅልፍ ማለት ነው፡፡ Hypnos የሚለው ቃል ሥረ ቃሉ hypnosis ነው፡፡ ይህኛው ግን በመንቃትና በመተኛት መካከል ያለ ሰመመናዊ ስሜት ነው፤ ይለናል ሚካኤል ፓወል፡፡
ሁኔታዎች አጥፊያችን ሆነው ስናገኛቸው በቆቅ ዐይን ማየት እንጂ ሰመመን ውስጥ (Hypnosis) ውስጥ መግባት የለብንም፡፡ መንቃት፣ ጆሮአችንን ማንቃት፣ አቅማችንን ማወቅና መስፈንጠር፤ እመርታ ማሳየት አለብን፡፡ አለበለዚያ እንደ አፈ-ታሪኩ፤ “ዕባብ ያፍዝ ያደንግዝ ያደረገባት ወፍ፤ ክንፍ እንዳላት ትረሳለች” መባል አይቀርልንም፡፡  



በጥቅምት 2006 ይጠናቀቃል የተባለው የስኳር ፋብሪካ ግንባታ ገና አልተጀመረም

የፋብሪካ ግንባታ በመጓተቱ፤ የ100 ሚሊዮን ብር ሸንኮራ አገዳ ያለ ጥቅም ተወግዷል

የፕሮጀክቶቹ የገንዘብ ወጪ በውል አይታወቅም፤ ያለ ጥናትና ዲዛይን የተጀመሩ ናቸው

           መንግስት በመቶ ቢሊዮን ብር ወጪ የስኳር ምርትን 23 ሚሊዮን ኩንታል ለማድረስ የሚያካሂዳቸው ከአስር በላይ አዳዲስና ነባር የስኳር ፕሮጀክቶች ያለ ውጤት ለአመታት የተጓተቱ ሲሆን፤ የመስኖና የፋብሪካ ግንባታዎቹ ለተቋራጭ ድርጅቶች የተሰጡት በህገወጥ መንገድ ያለጨረታ እንደሆነ የፌደራል ኦዲተር ገለፁ፡፡ አስር የስኳር ፋብሪካዎች ግንባታ ህግን ባልተከተለ መልኩ ያለ ጨረታ ሙሉ ለሙሉ ለብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን መሰጠቱን ኦዲተሩ ጠቅሶ፤ የፋብሪካዎቿ ግንባታ እንደተጓተተ ገልጿል፡፡ ያለ ጨረታ የመስኖና የአገዳ ልማት ፕሮጀክቶችን ወስደው ስራ ያጓተቱ ተቋራጮች፤ በአዲስ አበባና በየክልሉ የሚገኙ የውሃ ስራ ድርጅቶች እንዲሁም የብረታብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ናቸው፡፡ ፕሮጀክቶቹ የመንግስትን የግዢ መመሪያ ባልተከተለ መልኩ ያለ ጨረታ ለተቋራጮች መሰጠታቸው፣ በታቀደላቸው ጊዜና ወጪ እንዳይጠናቀቁ ያደርጋል ብሏል - የኦዲተሩ የምርመራ ሪፖርት፡፡

ፕሮጀክቶቹ ለተቋራጮቹ የተሰጡበትን አሰራር በተመለከተ ማብራሪያ እንዲሰጡ የተጠየቁት የኮርፖሬሽኑ የስራ ሃላፊዎች፣ በግዢ ክፍሉ በኩል የምናውቀው ነገር የለም የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። የኮርፖሬሽኑን የአምስት አመታት እቅድ አፈጻጸም በተመለከተ የቀረበው መረጃ እንደሚያሳየው፣ በጣና በለስ እና በኦሞ-ኩራዝ ፕሮጀክቶች፣ የ3 ፋብሪካዎች ግንባታ እስከ ጥቅምት 2005 ዓ.ም እንዲጠናቀቅ እቅድ ወጥቶ እንደነበር የገለፀው የፌደራል ኦዲተር፤ እስከ አመቱ መጨረሻ የተከናወነው ስራ ግን ከ45 በመቶ እንደማይበልጥ ገልጿል፡፡ በጥቅምት ወር 2006 ዓ.ም ይጠናቀቃል የተባለው የወልቃይት የስኳር ፋብሪካ ግንባታም፣ ገና ግንባታው ሳይጀመር የእቅዱ ጊዜ ማለፉ ተገልጧል፡፡

በአገዳ ተክል ልማት፣ በመስኖ ስራና በፋብሪካ ግንባታ በኩል ኮርፖሬሽኑ የሚያዘጋጃቸው የስኳር ፕሮጀክት እቅዶች የሰው ሃይልንና የገንዘብ ምንጭን ያላገናዘቡ፣ ተግባሪ አካላትን ያላሳተፉና በበቂ ጥናት ላይ ያልተመሰረቱ መሆናቸውን በምርመራ እንደደረሰበት ኦዲተሩ ገልፆ፤ በዚህም ምክንያት የኮርፖሬሽኑ ዓመታዊ እቅዶች በአመት ከሶስት ጊዜ በላይ ይከለሳሉ ብሏል፡፡ ይህም ፕሮጀክቶቹ እንዲጓተቱ ማድረጉንና መንግስትን ተገቢ ላልሆነ ወጪ እየዳረገው እንደሚገኝ የኦዲተሩ ሪፖርት ገልጿል፡፡ የተንዳሆ ስኳር ፕሮጀክት የፋብሪካ ግንባታ ስራ በታቀደለት ጊዜ መጠናቀቅ ባለመቻሉ ምክንያት፣ በ5ሺህ164 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የሸንኮራ አገዳ ምርት ጥቅም ላይ ሳይውል እንዲወገድ መደረጉን ኦዲተሩ ጠቅሶ፤ በዚህም ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ እንደደረሰ አመልክቷል፡፡

ፕሮጀክቶቹ በትክክል ምን ያህል ገንዘብ ወጪ እንደተደረገባቸው በውል ለመለየት አለመቻሉን የገለጸው የኦዲተሩ ሪፖርት፤ ከአገዳ ልማት፣ ከመስኖ ግንባታና ከፋብሪካ ግንባታ ክፍል ጋር የተቀናጀና የተጠናከረ የፕሮጀክት ክትትልና ቁጥጥር አሰራር ባለመኖሩ ምክንያት በየአመቱ ተደጋጋሚ የዕቅድ ክለሳ በማድረግ የዕቅድ አፈጻጸም መጓተትን፣ የወጪ መጨመርን፣ የጊዜ መራዘምንና የሃብት ብክነትን አስከትሏል ብሏል፡፡ ፕሮጀክቶቹ ለአመታት መጓተታቸው፤ የሃብት ብክነትን ከመፍጠር በተጨማሪ በአምስት አመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ላይ የተቀመጠው ግብ እንዳይሳካ ማድረጋቸውን ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡ የአገሪቱ የስኳር ምርት በየአመቱ እንደሚጨምር ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፤ ከ2003 ዓ.ም ወዲህ የስኳር ምርት እየቀነሰ እንደነበር ይታወቃል፡፡ በአምስት አመት ውስጥ የስኳር አመታዊ ምርት ከ3 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 22 ሚሊዮን ኩንታል እንዲያድግ ታቅዶ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን፤ እስካሁን አራት ሚሊዮን ኩንታል አለመድረሱ ተዘግቧል፡፡

በየቀኑ 1 ሺ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ

አምና ለስደተኞች የምግብ እህል የተገዛው ከኢትዮጵያ ነው

        ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ግማሽ ሚሊዮን ስደተኞች እያስተናገደች መሆኑን የገለፀው የዓለም ምግብ ፕሮግራም አብዛኞቹ የሶማሊያ፣ የደቡብ ሱዳንና የኤርትራ ስደተኞች መሆናቸውን አስታወቀ፡፡ ድርጅቱ ያለፈውን ዓመት (2013) የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ሰሞኑን ባቀረበበት ወቅት፤ በየቀኑ 1 ሺ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ መሆኑን ጠቅሶ ካለፈው ዓመት መስከረም ወር አንስቶ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ስደተኞች 140ሺ እንደደረሱ የድርጅቱ ተጠሪና ዳሬክተር ሚ/ር አብዱ ዴንግ ገልጸዋል፡፡ አብዛኞቹ ስደተኞች ሕፃናት፣ ሴቶችና የሚያጠቡ እናቶች መሆናቸውን ሚ/ር አብዱ ጠቅሰው፣ ለችግሩ ፖለቲካዊ መፍትሔ ካልተፈለገ በስተቀር አሁን ድርጅቱ የቀረው 70 ሚሊዮን ዶላር የሚያገለግለው እስከ መጪው ጥር ወር በመሆኑ፣ በሚቀጥለው ዓመት ለሚያስፈልጋቸው 120 ሚሊዮን ዶላር የዓለም ለጋሾች እጃቸውን እንዲዘረጉላቸው ተማፅነዋል፡፡

ከቀያቸው የተፈናቀሉት የደቡብ ሱዳን ስደተኞች የተጠለሉት በቀላሉ በማይደረስበት የጫካ አካባቢ በመሆኑ፣ በየቀኑ ከጋምቤላ አሶሳ፣ ከአሶሳ ወደ ደቡብ ሱዳን ድንበር እየበረሩ በአውሮፕላንና በጀልባ እየተጠቀሙ 15,000 ሜትሪክ ቶን የምግብ ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡ ድርጅቱ ባለፈው 2013 ዓመት፣ ለስደተኞች 330ሺ ሜትሪክ ቶን የምግብ እህል ከ15 አገሮች መግዛቱን ጠቅሶ፣ 46 ከመቶው ከኢትዮጵያ የተገዛ መሆኑን አመልክቷል፡፡ 120 ቶን እህል ከኢትዮጵያ ገበሬዎችና የህብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን በመግዛቱ፣ 67 ሚሊዮን ዶላር ገበሬዎቹ ኪስ መግባቱንና ኢትዮጵያ ብዛት ያለው የምግብ እህል ከተገዛባቸው አምስት አገሮች አንዷ መሆኗን ጠቁሟል፡፡

“አዲስ አድማስ” ጋዜጣ የዜጐችን የመኖሪያ ቤት እጥረት ችግር ለመፍታት በመንግስት በኩል እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትንና ውጤታቸውን እንዲሁም የአፈጻጸም ክፍተቶችን አስመልክቶ ለህዝቡ ትክክለኛና ሚዛናዊነቱን የጠበቀ መረጃ በመስጠት ኃላፊነቱን ይወጣል ብለን እናምናለን፡፡ እየተወጣም ነው፡፡ ሆኖም በአዲስ አበባ ቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ የሚካሄደውን የ40/60 ቁጠባ ቤቶች ልማት ፕሮግራም አፈፃፀም በተመለከተ በጋዜጣው እትሞች የወጡት መረጃዎች የተሳሳቱ ናቸው፡፡ በተለይም በቅፅ 13 ቁጥር 748 እና 750 ላይ ኢንተርፕራይዙን አስመልክቶ የወጡ ዘገባዎች በትክክለኛ የመረጃ ምንጭ ላይ የተመሰረቱ አይደሉም፡፡ ዘገባዎቹ የተመዝጋቢዎች ቁጥር፣ የሚገነቡት ቤቶች ብዛትና ዓይነት፣ የግንባታ ማነቆዎችን በተመለከተና በመሳሰሉ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ ናቸው፡፡ በርዕሰ ጉዳዮቹ ዙሪያ ዘገባዎች መሰራታቸው ተገቢና ትክክል መሆኑን የምንቀበለው ቢሆንም በዘገባችሁ የቀረቡ አንዳንድ መረጃዎች ትክክለኛ ስላልሆኑ ተከታዩን ማስተካከያ እንድታወጡ እንጠይቃለን፡፡
በቅፅ 13 ቀጥር 750 እትም፤ የ40/60 ቤቶች ግንባታና የተመዝጋቢዎች ፍላጐት አይጣጣምም የሚል ዘገባ ወጥቷል፡፡ የኢንተርፕራይዙ እቅድ ባለ 2 እና ባለ 3 መኝታ ቤት የሚፈልጉ ተመዝጋቢዎችን ማስተናገድ አይችልም ይላል ዘገባው፡፡ ይሄ ፍፁም የተሳሳተና ትክክለኛ ባልሆነ መረጃ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ኢንተርፕራይዙ በ9 የግንባታ ሳይቶች የ13,881 ቤቶች ግንባታ እያካሄደ ሲሆን በእያንዳንዱ ሕንፃ ባለ 1፣ በላይ 2 እና ባለ 3 መኝታ ቤቶችን እያመጣጠነ በመገንባት ላይ ነው፡፡
በዚሁ እትም፤ በ40/60 ለሚገነቡ የንግድ ቤቶች አንድም ተመዝጋቢ አልተገኘም ተብሎ ተዘግቧል፡፡ ሆኖም ኢንተርፕራይዙም ሆነ የከተማ አስተዳደሩ የንግድ ቤቶችን የምትፈልጉ ተመዝገቡ ብሎ ያወጣው ማስታወቂያ የለም፡፡ ከነሐሴ 3-17 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ  የተካሄደው ምዝገባ ዓላማው የመኖሪያ ቤት ችግር ላለባቸው ዜጐች ቁጠባን መሰረት አድርጐ ቤት ለመገንባት ነው፡፡ የንግድ ቤቶች ምዝገባ ሳይኖር በ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም የንግድ ቤት ተመዝጋቢዎች አልተገኙም የሚል ዘገባ ለመስራት የተፈለገበት ምክንያት ግልፅ አይደለም፡፡
35 በመቶ በባለ 1 መኝታ፣ 25 በመቶ በባለ 2 መኝታና 20 በመቶ ደግሞ በባለ 3 መኝታ ይመዘገባል ተብሎ ቢጠበቅም የተጠበቀው ሳይሆን ቀርቷል በሚል የቀረበውም ዘገባ በመረጃ ላይ የተመሰረተ አይደለም፡፡ መንግስት በ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም፣ ቤት ፈላጊዎችን ሲመዘግብ በባለ 1 መኝታ፣ በባለ 2 መኝታና በባለ 3 መኝታ ላይ ይሄን ያህል በመቶ ዜጐች ይመዘገባሉ ብሎ አቅዶ አልተነሳም፡፡ ሊነሳም አይችልም፡፡ የሚያመለክቱት በአንድ ሕንፃ ላይ የሚኖረውን የቤት ብዛት ምጣኔ እንጂ ከተመዝጋቢው ቁጥር ማነስና መብዛት ጋር የሚያያዝ አይደለም፡፡ መንግስት በአንድ ህንፃ የሚኖረው የማህበረሰብ ስብጥር የተመጣጣነ እንዲሆን ለማድረግ የተከተለው አቅጣጫ መሆኑን ልናስገነዝብ እንወዳለን፡፡
ኢንተርፕራይዙ ከተመዝጋቢዎች ቁጥር ጋር በተያያዘ ምክንያት ወደ ግንባታ የገቡ ቴፖሎጂዎችን እንደሚቀይር ተደርጎ የተዘገበውም ስህተት ነው፡፡ በአሁኑ ሰአት ባለ 12፣ ባለ 9 እና ባለ 7 ፎቅ 13,881 ቤቶችን (219 ብሎኮችን) በመገንባት ላይ ሲሆን በቀጣይነትም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ ከተገለፁት የሕንፃ ከፍታዎች በተጨማሪ በተወሰነ ቦታ በርካታ ሰው ለማስተናገድና ከተማዋን ከፍ ወዳለ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ሕንፃዎችን ለመገንባት፣ ኢንተርፕራይዙ በራሱ ተነሳሽነት ባለ 18 እና ባለ 24 ፎቅ ከፍታ ያላቸው ህንፃዎች ዲዛይን አሰርቶ የሚመለከተው አካል እንዲያፀድቀው ልኳል፡፡
በመጨረሻም በሰንጋተራ እየተገነቡ ባሉ ቤቶች የሜትር ስኩየር የስፋት ልዩነት መከሰቱን በተመለከተ የቀረበው ዝርዝር መረጃ፣ ከኢንተርፕራይዙ እውቅና ውጭ የሆነና በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ አለመሆኑን እንገልፃለን፡፡

ሁለት የህክምና ባለሙያዎችን ጋብዣለሁ፡፡ አንድ የፅንስና ማህፀን ሃኪም ሌላ ደግሞ የህፃናት ሃኪም ሁለቱም የሚሰሩት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሲሆን ባነሳሁት ርዕስ ጉዳይ ላይ በዚህ ገፅ (አምድ) ቢታይና ቢነበቡ የእናንተን የአንባብያንን ደረጃ ይመጥኑ ይሆናል ብዬ የገመትኳቸውን ጥያቄዎች ብቻ ለማንሳት ሞክሬአለሁ፡፡
ዶ/ር ሶፋኒት ኃይሌ በአዲስ አበባ ዪኒቨርሲቲ ህክምና ፋክሊቲ የማህፀንና ፅንስ ህክምና ትምህርት ክፍል መምህርት እንዲሁም ሁለተኛ አመት የስፔሻላይዜሽን ትምህርት ፕሮግራም ተማሪ ነች፡፡
ዶ/ር ትንሳኤ አለማዬሁ በጥቁር አንበሳ ሆ/ል በህፃናት የትምህርትና የህክምና ክፍል በመስራት ላይ የሚገኝ ሃኪምና የሶስተኛ አመት የህፃናት ህክምና የስፔሻላይዜሽን ትምህርት ፕሮግራም ተማሪ ነው፡፡

ጥያቄ፡- መደበኛ ከሚባው የእርግዝና ጊዜ (ከዘጠኝ ወራት በፊት)፣ ቀድሞ በሰባተኛው ወር ላይ አንዲት እናት የእርግዝናው ጊዜ በቃኝ፣ ከዚህ በኋላ ጽንሱን ለመሸከም በአካልም በስነ ልቦናም ብቁ አይደለሁም፣ ብትል ማዋለድ ይቻላል?
ዶ/ር ሶፋኒት፡- በመጀመሪያ በሰባተኛው ወርም ሆነ ከዚያ በፊት ባለው ጊዜ ያለ በቂ ምክንያት ፅንስን ማቋረጥ በህግ አይፈቀድም፤ በህክምናው ደግሞ ፅንስ በማህፀን ውስጥ ተገቢውን ጊዜ ባለማቆየቱ የሚገባውን የሳንባ፣ አንጀትና የአእምሮ እድገት አያገኝም ማለት ነው፡፡ በእኛ ሃገር ደግሞ ህፃናትን የምናቆይበት ማሞቂያ ክፍል በበቂ ሁኔታ የተደራጀ ስላልሆነ እክል ሊያጋጥማቸው ይችላል፡፡ ይኽም እስከ ማት ሁሉ ሊደርስ የሚችልበት አጋጣሚ ይኖራል። በእናትም ላይ ድህረ ወሊድ የጤና እክል ሊያጋጥም ይችላል፡፡
ጥያቄ፡- ከሚጠበቀው ጊዜ በፊት የሚወለዱ ልጆች ከጤናና ከአካላዊ እድገት ጋር በተያያዘ የሚያጋጥማቸው ችግር ምንድን ነው?
ዶ/ር ትንሳኤ፡- ከሚጠበቀው ጊዜ በፊት ሲባል ብዙ ጊዜ ከ37ኛው ሳምንት በፊት የሚወለዱ ልጆች ናቸው፡፡ ብዙ ጊዜ ከሚጠበቀው ክብደት በታች ሆነው ይወለዳሉ፡፡ ይኸውም አዲስ የሚወለዱ ልጆች ቢያንስ ክብደታቸው ሁለት ነጥብ አምስት ኪሎ ግራም (2.5ኪሎ ግራም) እና ከዚያ በላይ መሆን ሲገባቸው ከዚህ በታች ይሆናሉ፡፡ ሆኖም ይህ ሁኔታ እድሜአቸው ከሁለት  አመትና ሁለት አመት ተኩል በላይ ሲደርሱ በክብደትም በቁመትም ከሌሎች በጊዜአቸው ከተወለዱ ልጆች ጋር ይስተካከላሉ፡፡ ሌላው በተደጋጋሚ የሚያጋጥመን በእነዚህ ቀድመው ከ37ኛው ሳምንት በፊት የሚወለዱ ልጆች ሳንባቸው ሳይጠና ወይም ሳይዳብርና እድገቱን ሳይጨርስ ይወለዳሉ፡፡ ሳንባ ልጅ በእናት ማህፀን ውስጥ እያለ አራት የእድገት ደረጃዎች ይሩታል፡፡ ይሁንና ቀድመው ያለ ጊዜአቸው የሚወለዱ ልጆች ይህን የሳንባ እድገት ሳይጨርሱ ይወለዳሉ፡፡ ይህንም ለማስተካከል የምናደርገው ህክምና ይኖራል፡፡ በተለይ በማሞቂያ ክፍል በሚቆዩበት ጊዜ አይናቸው ላይ፣ አንጀት ላይ የተለያዩ ኢንፌክሽን እደዚሁም በደም ዝውውር ላየ የሚከሰቱ ችግሮች ይኖራሉ፡፡
ጥያቄ፡-  ሁሉም ሊከሰቱ የሚችሉት ችግሮች በሙሉ በህክምናው ሊረዳ የሚችል ነው ካደጉ በኋላስ ችግሮቹ ሊያመጡት የሚችሉት ችግር ይኖራል?
ዶ/ር ትንሳኤ፡- የሳንባ አለመዳበር ጋር በተያያዘ እናት ከመውለዷ በፊት የምሰጠው በተለይ ከ48 ሰዓት በፊት የምንሰጠው መድኃኒት አማካኝነት ሊመጡ የሚችሉ ችግሮችን ለመከላከል የሚቻልበት ሁኒታ አለ….
ጥያቄ፡- ከመደበኛው ጊዜ ቀድማ እደምትወልድ ከታወቀ ማለት ነው?
ዶ/ር ትንሳኤ፡- አዎ፣ ያለጊዜዋ ቀድማ እደምትወልድ ከታወቀ፤ ካልታወቀ ደግሞ (ድንገተኛ ከሆነ) ቀጥሎ በሚደረግ ህክምና (ይኸውም ሁሉም የህክምና መሳሪያዎችና አገልግሎቶች በተሟሉበት ሁኔታ) ከ70 እስከ 80 በመቶ የሚወለዱት ልጆች የተስተካከለ እድገት እዲኖራቸው ማገዝ ይቻላል፡፡
ጥያቄ፡- ከፍላጎት ውጭ በሆነ ሁኔታ ደግሞ እናት በተለያዩ አጋጣሚዎች አንዴ ከመደበኛው ጊዜ በፊት ምጥ ቢከሰትባት በቀጣዮቹ እርግዝናዎች ተመሳሳይ ሁኔታ ሊያጋጥማት ይችላል?
ዶ/ር ሶፋኒት፡- አዎ፣ እንዲያውም አንዳንድ ጥኖቶች አንዴ ቀድሞ ምጥ የተከሰተባት እናት በቀጣዩ ጊዜ የማጋጠሙ እድል እስከ 40 በመቶ ሊደርስ ይችላል የሚል መነሻ ያመላክታሉ። ይህ የሚሆንበት ምክንያት ምንድን ነው በመጀመሪያው እርግዝና ቀድሞ ምጥ እንዲከሰት ያደረገው ችግር በተመሳሳይ በሁለተኛውና በቀጣዮችም እርግዝናው ቀድሞ ሊወለድ ይችላል፡፡ ለምሳሌ በታችኛው የመራቢያ ክፍል ላይ ኢንፌክሽን  ከነበረ ወይም የተለያዩ የአባላዘር በሽታዎች ተከስተው ከነበረና እነዚህም ችግሮች በአግባብ ካልታከሙ ተከታዮቹ ፅንሶችም ቀድሞ የመወለድ አጋጣሚ ይኖራቸዋል፡፡  ከዚህ ሌላም ከአንድ በላይ ወይም መንታ ልጆችን ያረገዘች እናት ላይ ቀድሞ ምጥ ሊከሰት ይችላል፣ይኽም በተከታዩ እርግዝና በተመሳሳይ ሁኔታ ምጥ ከመደበኛው ጊዜ በፊት እንዲከሰት ያደርጋል፡፡ ስለዚህ ዋናው ነገር አንዴ ምጥ ከ42 ሳምንታት በፊት የተከሰተባት እናት በቀጣዮቹ እርግዝናዎች ተመሳሳይ ክስተት ሊያጋጥም ስለሚችል ቀድሞ መዘጋጀት ይጠይቃል፡፡
ጥያቄ፡- ቀድሞ ያለጊዜው የምጥ ክስተት ከዘር ጋር ይያያዛል ለምሳሌ እናት በሰባተኛው ወር ብትወልድ ልጇም እዲህ ያለ አጋጣሚ ሊኖራት ይችላል?
ዶ/ር ሶፋኒት፡- በዘር የሚተላለፍ ነገር አይደለም ቀድሞ ምጥ የመከሰት ችግር፡፡ ከዚህ ይልቅ በተቃራኒው ዘግይቶ ከ42 ሳምንት በኋላ የሚወልዱ እናቶች ልጆቻቸውም ተመሳሳይ ችግር ሊያጋጥማቸው ይችላል፡፡
ጥያቄ፡-  ዘገየ ሲባል ከስንት ወራት ወይም ሳምንታት በላይ ሊዘልቅ ነው ቀደመ ሲባልስ?
ዶ/ር ሶፋኒት፡- ከሚገባው ጊዜ በላይ ዘገየ የምንለው ከ42 ሳምንታት ወይንም 294 ቀናት በላይ ሲሆን ነው፤ ይኽም የሚሰላው እናት የመጨረሻውን የወር አበባ ካየችበት የመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ግን ብዙ ጊዜ ስህተት ያጋጥማል፡፡ እናቶች የመጨረሻውን የወር አበባ ክስተት ያለማስታወስ ወይም ልብ ብሎ ያለመመዝገብ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ከዚህ ሌላም የሚዛባ የወር አበባ ክስተት ያላቸው እናቶችና ሆርሞናል የሆኑ (እንክብልና የመርፌ) ወሊድ መቆጣጠሪያ መንገዶችን የሚጠቀሙ እናቶች ላይ እርግዝና በትክክል የተከሰተበትን ቀን ያለመረዳት ሁኔታ ያጋጥማል፡፡ ስለዚህ እርግዝናው ዘግይቷል ወይም ቀድሟል ከሚለው ድምዳሜ መፊት እነዚህን ጉዳዮች ቀድሞ ማጣራት ያስፈልጋል ማለት ነው፡፡
ጥያቄ፡- በአንድና በሌላ ምክንያት እርግዝና ከተከሰተ በሰባተኛው ወር ላይ የወለደች እናት ጡቷ በዚያን ወቅት በቂ የሆነ የወተት ምርት ለልጇ ይሰጣል?
ዶ/ር ሶፋኒት፡- ጡት ወተት ማምረት የሚጀምረው እርግዝናው ልክ ከተከሰተበት ቀን ጀምሮ ነው፡፡ የተለያዩ አካላዊ ዝግጅቶች ያካሂዳል ስለዚህ ልጁ በሰባተኛውም ወር ቢወለድም  በቂ የሆነ ወተት ከእናቱ ያገኛል፡፡ ልጁ እንደተወለደ መጥባት ይጀምራል ያ እናት ወተት መስጠቷን ምልክት ሰጭ ነው፡፡ ጡት ሲጠባ ወተቱ ከእናት ወደ ልጅ ሲወርድ ደግሞ መልዕክትከእናት ጡት ወደ  መካከለኛ የጭንቅላት ክፍል  ያደርሳል፤ ይህ ወተት መመረት እዳለበት የሚጠቁም ምልክት ነው፡፡ ወተት መመረት ይቀጥላል፡፡ ብዛቱም የሚወሰነው በሚጠባው መጠን ነው፤ ብዙ በተጠባ ቁጥር ብዙ ምርት ይኖራል፣ መጥባት ሲቀንስ ይቀንሳል፡፡
አበበ፡- ዶ/ር ሶፋኒት ኃይሌ አመሰግናለሁ
ዶ/ር ሶፋኒት፡- እሺ አመሰግናለሁ

ቻይና፣ ህንድ፣ ኢንዶኔዢያ ለእግር ኳስ ባይተዋር ናቸው
በአሜሪካ ክቧ ኳስ ከሞላላ ኳስ ጋር መፎካከር አልቻለችም

የህንድ ቡድን በአለም ዋንጫ የመካፈል ጥሩ እድል ያገኘው ከ64 አመታት በፊት ነው። በብራዚል በተዘጋጀው የያኔው የአለም ዋንጫ ላይ ያለ ማጣሪያ እንዲካፈል የተጋበዘው የህንድ ቡድን፣ እድሉን አልተጠቀመበትም - በሁለት ምክንያቶች። አንደኛው ምክንያት፣ ድህነት ነው። የመጓጓዣና የመሰንበቻው ወጪ ከበዳቸው። ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ኋላቀርነት ነው። የህንድ ቡድን የፊፋን ህግ ለማክበር አልፈለጉም - ያለ ጫማ ነው የምንጫወተው በማለት። ጫማ ካደረግን፣ ጥቃቅን ነፍሳትን ረጋግጠን ልንገድል እንችላለን ብለው የሰጉት የህንድ ተጫዋቾች፤ ሃጥያት ውስጥ መግባት አንፈልግም ብለው ከአለም ዋንጫ ቀርተዋል። እንዲህ፣ ተረት የሚመስል ኋላቀር ባህል ምን ይባላል?
ቻይናን ጉድ ያደረጋት ግን፣ ጥንታዊ ባህል አይደለም። ለነገሩማ፣ እግር ኳስ የሚመስል ጨዋታ የተጀመረው በጥንታዊ ቻይና እንደሆነ ይነገር የለ! ቻይናዊያን ከእግር ኳስ ጋር የተራራቁት በኮሙኒዝም ምክንያት ነው። የድሮዎች የአገራችን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ እነ ደርግና እነ ኢህአፓ ጭምር በአድናቆት የዘመሩላቸው የቻይና መሪ ማኦ ዜዱንግ፣ አገሬውን ሁሉ ሌት ተቀን ፋታ በማይሰጥ ስብሰባ፣ ግምገማና የስራ ዘመቻ ወጥረው ነበር የያዙት። ኳስ ለመጫወት ጊዜ አልነበረም።
ስብሰባውና የስራ ዘመቻውም ጠብ የሚል ነገር አልተገኘበትም - 20 ሚሊዮን ቻይናዊያን በረሃብ ያለቁት በማኦ ዘመን ነው። ከማኦ በኋላ፣ በዴንግ ዚያዎፒንግ ዘመን በመንግስት ተተብትቦ የቆየው ኢኮኖሚ ለግል ኢንቨስትመንት ሲከፈት፣ ከዚያም ሲስፋፋ አገሪቱ በፍጥነት ወደ እድገት መጓዝ ጀምራለች። በመንግስት የተተበተበው ፖለቲካ ግን ብዙም አልተቀየረም። ያለ መንግስት ፈቃድ ከ10 በላይ ሰዎች በአንድ ቦታ ቢሰባሰቡ ይታሰራሉ። ክልክል ነው።
የሰፈር ወጣቶች እግር ኳስ ለመጫወት በየቀኑ ቀበሌና ወረዳ ሊቀመንበር ጋ እየሄዱ የፈቃድ ማመልከቻ ሲያስገቡ ይታያችሁ። “ስፖርት ለአገር ልማትና ለጤናማ ህብረተሰብ ወሳኝ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ይታወቃል። እኛ ስማችን ከዚህ በታች የተዘረዘረ የሰፈር ወጣቶች፣ ለአገርና ለህብረተሰብ ልማት በማሰብ ዛሬ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት እግር ኳስ ለመጫወት አስበናል። ፅ/ቤቱ ፈቃድ እንዲሰጠን እየጠየቅን፣ ለሚደረግልን ትብብር አብዮታዊ ምስጋና እናቀርባለን...”  
“አብዮት ወይም ሞት!” በሚል መፈክር የታጀበ ማመልከቻ እየፃፉ እግር ኳስ ለመጫወት የሚጓጓ ብዙ ወጣት አይኖርም። በኮሙኒዝም የተሽመደመደው  የቻይና እግር ኳስ፤ እስከዛሬ ገና ቆሞ የመራመድ ብርታት አላገኘም። ደግነቱ፣ እንደ ታሊባን ወይም እንደ አልሸባብ የእግር ኳስ ጨዋታ በቲቪ መመልከት አልተከለከለም። ብዙ ቻይናዊያን እግር ኳስ ባይጫወቱም፣ መመልከት ግን ይወዳሉ። 300 ሚሊዮን ቻይናዊያን በ2010 የአለም ዋንጫ ውድድሮችን በቲቪ ተከታትለዋል።
ህንድና ቻይና ከእግር ኳስ አለም የራቁት በጥንታዊ ኋላቀር ባህልና አኮራምቶ በሚተበትብ የኮሙኒዝም አፈና ሳቢያ ከሆነ፤ አሜሪካ ከእግር ኳስ ጋር ያልተወዳጀችው በምን ምክንያት ይሆን? በሌሎች ተወዳጅ ስፖርቶች ምክንያት ነው። በአሜሪካ ስቴዲየም የሚገባ ብዙ ተመልካች የሚሰበሰበው በሞላላ ኳስ የሚካሄደውን ጨዋታ ለማየት ነው። በአማካይ በእያንዳንዱ ጨዋታ ከ68ሺ በላይ ተመልካች ስቴዲየም ይገባል - ያንን ነው ፉትቦል የሚሉት። እግር ኳስን፣ ሶከር እያሉ ነው የሚጠሩት። ከዚያ በኋላ ደግሞ ቤዝ ቦል አለ። የቤዝ ቦል ጨዋታ ለመመልከት በአማካይ ከ30ሺ በላይ ሰው ስቴዲየም ይገባል። እግር ኳስ ለማየት የሚሰበሰበው ተመልካች፣ ከቅርጫት ኳስ ተመልካቾች ቁጥር ብዙም አይራራቅም - በአማካይ 18ሺ ገደማ ሰው።
በአጭሩ፤ አውሮፓን፣ ደቡብ አሜሪካንና አፍሪካን ያጥለቀለቀው የእግር ኳስ ዝና፣ በአሜሪካ ገና አልተስፋፋም። እንዲያም ሆኖ፣ ከሌሎቹ ትልልቅ አገራት (ከህንድ እና ከቻይና )ጋር ሲነፃፀር፣ የአሜሪካ ሳይሻል አይቀርም። የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን በተደጋጋሚ በአለም ዋንጫ ላይ ሲሳተፍ እያየን አይደል?
ሶስቱ ትልልቅ አገራት፤ (ህንድ፣ ቻይና እና ኢንዶኔዢያ) ግን፤ ለአለም ዋንጫ ባይተዋር ናቸው። በእርግጥ፤ ቻይና አንዴ በአለም ዋንጫ ተሳትፋለች። ግን፤ እንደተሳተፈች አይቆጠርም። የቻይና ቡድን አንድም ጊዜ አላሸነፈም። ጨርሶ፣ አንድም ጎል ሳያስገባ ነው በመጀመሪያው ዙር ከውድድሩ የተሰናበተው። እግር ኳስ ለማየት ወደ ስቴዲየም ጎራ ማለት፤ በህንድ፣ በኢንዶኔዢያና በቻይና ገና አልተለመደም።
በዚህ በዚህ ጀርመንን የሚስተካከል የለም። በእያንዳንዱ የቡንደስ ሊጋ ጨዋታ በአማካይ 42ሺ ተመልካች ስቴዲየም ይገባል። በእንግሊዙ ፕሪሚየር ሊግ ደግሞ፣ 36ሺ ሰዎች ስቴዲየም ይታደማሉ። በቅርቡ የተጠናቀቀውን የፕሪሚየር ሊግ ለማየት በድምሩ 14 ሚ. ገደማ ቲኬቶች ተሽጠዋል።

   በእያንዳንዱ ጨዋታ ላይ ለቁማርና ለውርርድ የሚከፈለው ገንዘብ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። በአለም ዋንጫ ውድድሮች ላይ በየጨዋታው በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ለቁማር እየዋለ መሆኑን የዘገበው ዘ ኢኮኖሚስት፣ በአጠቃላይ ከ30 ቢ. ዶላር በላይ ገንዘብ የቁማር መጫወቻ እንደሚሆን አመልክቷል።
የለንደን ህገወጥ ሬዲዮ ጣቢያዎች እያበቃላቸው ይሆን?
በሃያኛው ክፍለዘመን’ኮ ያልተበላሸ አገር የለም ማለት ይቻላል። “የግለሰብ መብት” እና “የነፃ ገበያ ስርዓት” የተወለዱባት እንግሊዝ ሳትቀር፣ ቀስ በቀስ ከስልጣኔ ማማ ቁልቁል መንሸራተት አልቀረላትም ነበር። መንግስት፣ የግል ኩባንያዎችን እንዲወርስ ባይደረግም፤ ካሳ እየከፈለ የተወሰኑ ድርጅቶችን ወደ መንግስት ይዞታነት ሲያዛውር አልነበር? በዚያ ላይ የግል ሬድዮና ቴሌቪዥን ጣቢያዎች በብዛት እንዳይቋቋሙ በህግ ታግደው ነበር። በዚህ ምክንያት ነው፤ በርካታ የሬዲዮ ጣቢያዎች በድብቅ መስራት የጀመሩት።
የመንግስት ሪፖርት እንደሚገልፀው፣ በለንደን ውስጥ 75 ያህል ድብቅ የሬዲዮ ጣቢያዎች አሉ። ከእነዚህ “ህገወጦች” መካከል አስሩ ጣቢያዎች፣ የ24 ሰዓት ስርጭት ያስተላልፋሉ። አንዳንዶቹ ደግሞ፣ ለበርካታ አመታት ያለማቋረጥ የሰሩ ናቸው። ዛሬ ዛሬ ግን፣ ቀስ በቀስ እየተዳከሙ ህልውናቸው እያበቃለት ይመስላል። ጣቢያዎቹ የተዳከሙት በመንግስት ቁጥጥርና ክትትል ሳቢያ አይደለም።
በእርግጥ “ህገወጥ” ስለሆኑ፤ አድራሻቸውን አጥፍተው በድብቅ ካልሰሩ በቀር መዘጋታቸውና መቀጣታቸው አይቀርም። የማሰራጫ አንቴናቸውን የሚተክሉት በድብቅ ነው። ከስቱዲዮ ወደ አንቴና የሬዲዮ ስርጭት የሚያስተላልፉትም በጥንቃቄ ነው - ለቁጥጥር በማያመች ጨረር አማካኝነት። ነገር ግን፣ የመንግስት ባለስልጣናትም፣ “ህገወጥ” የሬዲዮ ጣቢያዎችን አሳድደው ለመያዝ የአሰሳ ዘመቻ አያካሂዱም። ክትትልና ምርመራ ለማካሄድ ጊዜና ገንዘብ አያባክኑም። ለድብቅ ጣቢያዎች፣ “ህጋዊ እውቅና መንፈግ በቂ ነው” ብለው ያስባሉ - ባለስልጣናት። በአጭሩ፣ ጣቢያዎቹን ያዳከማቸው ወይም ስጋት ላይ የጣላቸው መንግስት አይደለም። ቴክኖሎጂ እንጂ።
ዘመኑ የኢንተርኔት ዘመን ነው። የፅሁፍ፣ የምስል፣ የድምፅና የቪዲዮ መልእክቶችን በቀላሉ በኢንተርኔት ማሰራጨትና መለዋወጥ ይቻላል። እገዳና ክልከላ ስለሌለ፣ ድብቅነትና ህገወጥነትም አያስፈልገውም። እናም አብዛኞቹ ድብቅ የሬዲዮ ጣቢያዎች፣ ስርጭታቸውን ወደ ኢንተርኔት ማዞር ጀምረዋል።  

ዋና ስራ - የኢንተርኔት አገልግሎት፣ ሶፍትዌር እና የቴሌኮም ምርት
በአመት የ60 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው አገልግሎቶችንና ምርቶችን ይሸጣል
ባለፈው አመት 13 ቢ. ዶላር አትርፏል
የኩባንያው ሃብት 120 ቢ. ዶላር ገደማ ነው
50ሺ ሰራተኞች አሉት
በኢንተርኔቱ አለም ቀዳሚ ስፍራ ይዟል
አስር የሚሆኑ ቶዮታ፣ አውዲ እና ሌክሰስ መኪኖች ያለ አሽከርካሪ እንዲቀሳቀሱ  ለማድረግ በተራቀቁ ቴክኖሎጂዎች ሙከራ ሲያካሂድ የከረመው ጉጉል፣ ከመቶ እስከ ሁለት መቶ የሚደርሱ የራሱ አዳዲስ መኪኖችን በመፈብረክ ለገበያ እንደሚያቀርብ ገልጿል። ጉጉል ሙከራውን ያካሄደው፣ ሁለት የአሜሪካ ግዛቶች (ኔቫዳ እና ፍሎሪዳ) በየጎዳናው አሽከርካሪ አልባ መኪኖች እንዲንቀሳቀሱ የሚፈቅድ ህግ ካወጡ በኋላ ነው።
ለሙከራ ያገለገሉት አስር መኪኖች ያለ አሽከርካሪ እንዲንቀሳቀሱ፣ ለእያንዳንዳቸው የ70ሺ ዶላር የራዳር ሲስተምን ጨምር 150ሺ ዶላር የሚያወጡ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ተገጥሞላቸዋል። በአመት ውስጥ ለገበያ ይቀርባሉ የተባሉት የጉጉል መኪኖች፣ ቢያንስ ቢያንስ ሰፊ ገበያ እስኪያገኙ ድረስ ዋጋቸው ውድ ሊሆን ይችላል ተብሏል። መሪ አልያም ፍሬን የሚባል ነገር የላቸውም። ማብሪያና ማጥፊያ በመንካት ነው መኪናውን የሚያስነሱት።
በፅሁፍ ወይም በካርታ የት መሄድ እንደሚፈልጉ ሲያሳውቁ፤ መኪናው በራሱ ጊዜ ይንቀሳቀሳል። ለሙከራ የተገጣጠሙት መኪኖች በመቶ ሺ ኪሎሜትር የሚቆጠር መንገድ በከተማና በገጠር ተጉዘዋል፤ አንድም ጊዜ ግጭት አላገጠማቸውም።

ዋነኛ ስራው - የኢንተርኔት አገልግሎት
በአመት ወደ 8 ቢ. ዶላር ገደማ የአገልግሎት ሽያጭ ያገኛል
ባለፈው አመት 1.5 ቢ. ዶላር አትርፏል
የኩባንያው ሃብት 18 ቢ. ዶላር ገደማ ይገመታል
በኢንተርኔት አለም በ2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል - 1.3 ቢ. ገደማ ደንበኞችን በማስተናገድ
በደንበኞች ብዛት አቻ ያልተገኘለት ፌስቡክ፣ ገና የረካ አይመስልም። ተጨማሪ ደንበኞችን ለማፍራት ዘዴ ማፈላለግ ከጀመረ ውሎ አድሯል። ከከተማ ርቀው የሚገኙና በቀርፋፋ የኢንተርኔት ግንኙነት የተቸገሩ ብዙ ሚሊዮን ሰዎች አሉ።
እነዚህን ሁሉ ደንበኛ ለማድረግ አዲስ ብልሃት ያስፈልጋል። በየአገሩ እየሄደ የግንኙት መስመር መዘርጋት አይችልም። እንደኢትዮጵያ በመሳሰሉ አገራትማ፣ ከመንግስት ውጭ የቴሌኮም አገልግሎት መስጠት ክልክል ነው።
ፌስቡክ የወጠነው ዘዴ፣ ከሰማይ ላይ የኢንተርኔት አገልግሎት ማቅረብ ነው። ከምድር በ30 ኪሎሜትር ርቀት የሚያንዣብቡ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ለማሰማራት ሙከራ እያከናወነ የሚገኘው ፌስቡክ፤ በፀሐይ ሃይል ለረዥም ጊዜ አየር ላይ የሚቆዩ አውሮፕላኖችን ሰርቷል።
ከሰማይ ላይ የኢንተርኔት አገልግሎት ለማቅረብ እየሞከረ ያለው ፌስቡክ ብቻ አይደለም። ጉጉልም በፊናው እየተጣጣረ ነው።
በአንድ በኩል በከፍተኛ ርቀት የሚንሳፈፉ “ባሉኖች”ን ለመጠቀም ራሱን የቻለ ፕሮጀክት ሲያከናውን የቆየው ጉጉል፤ በፀሃይ ሐይል ለ5 ዓመታት አየር ላይ የሚያንዣብቡ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ሰርቷል።