Administrator

Administrator

     የዓለም አገራት ፓስፖርቶች ሁሉ ተመሳሳይ ናቸው፡፡ መጠናቸውም ቢሆን 125 ሚሜ x 88 ሚሜ ገደማ ነው፡፡ የየአገራቱ ፓስፖርት አንዱ ከሌላው የሚለየው በምን መሰላችሁ? ያለ ቪዛ ወደ ስንት የዓለም አገራት በቀላሉ ያስገባሉ በሚለው ነው፡፡ ሲሼልስ ዜጎቿ ያለ ቪዛ ውጣ ውረድ በርከት ወዳሉ የዓለም አገራት በቀላሉ እንዲገቡ የሚያስችል አስተማማኝ ፓስፖርት ያላት አፍሪካዊ አገር ናት። የኤርትራ ፓስፖርት ደግሞ የዓለም አገራትን ጉዞ አስቸጋሪ ያደርጋል ተብሏል፡፡
የአፍሪካ አገራት ፓስፖርቶች ያለ ቪዛ ወይም መድረሻ ላይ በሚመታ ቪዛ ወደ ስንት የዓለም አገራት ሊያስገቡ ይችላሉ የሚለውን በመፈተሽ “Good” መፅሄት 7 ቀዳሚ የአፍሪካ አገራትን ለይቶ ደረጃ ሰጥቷቸዋል፡፡ ጥናቱ እንደሚያሳየው፤ የሲሼልስ ፓስፖርት ያላቸው ዜጎች ለቪዛ ማመልከት ሳያስፈልጋቸው 126 አገራትን በነፃነት መጎብኘት ይችላሉ፡፡ ሞሪሽየስና ደቡብ አፍሪካ ደግሞ በሁለተኛና ሦስተኛነት ደረጃ የአፍሪካ አስተማማኝ ፓስፖርቶች ሆነዋል፡፡ የአፍሪካ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት የሆነችው ናይጄሪያ ግን በዚህ ረገድ በ33ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡
በዓለም ደረጃ ፊንላንድ፣ ስዊድንና ዩናይትድ ኪንግደም የዓለማችን የመጀመሪያዎቹ ሶስት አስተማማኝ ፓስፖርቶች ባለቤት ሲሆኑ ዜጎቻቸው ወደ 137 አገራት ያለምንም ውጣውረድ በቀላሉ እንዲገቡ ያስችላሉ፡፡ አፍጋኒስታን ከዓለም የመጨረሻ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡
በዓለም ላይ ቪዛ በከፍተኛ ደረጃ ከሚጠየቅባቸው ክልሎች አንዷ አፍሪካ ስትሆን በአፍሪካ አገራት መካከል ያለው ጥብቅ የቪዛ ቁጥጥር የኢኮኖሚ ዕድገቱን ክፉኛ እንደጎተተው ይነገራል፡፡ ከዚህ በታች “Good” መፅሔት “7ቱ አስተማማኝ የአፍሪካ ፓስፖርቶች” በሚል በደረጃ ያስቀመጣቸውን አገሮች እንመለከታለን፡፡
ሲሼልስ - ለ129 አገሮች ቪዛ አያስፈልግም
የሲሼልስ ዜጎች ወይም ፓስፖርት ባለቤቶች ያለ ቪዛ ወይም መድረሻቸው ላይ በሚመታላቸው ቪዛ ወደ 126 አገራት በቀላሉ መግባት ይችላሉ፡፡ የሲሼልስ ፓስፖርት ዜጎችን ከዓለም አገራት ጋር በቀላሉ በማገናኘት ከአፍሪካ የአንደኝነት ደረጃ ሲይዝ ከዓለም በ28ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
ሞሪሺየስ - ለ125 አገሮች ቪዛ አያስፈልግም
በአፍሪካ ከሲሼልስ ቀጥሎ ወደ ብዙ የዓለማችን አገራት በነፃነት የሚጓዙት የሞሪሺየስ ዜጎች ናቸው፡፡ የዚህች አገር ፓስፖርት ያለ ቪዛ ወይም መድረሻ ላይ በሚመታ ቪዛ ወደ 123 አገራት ያስገባል፡፡ በዚህም በአፍሪካ 2ኛው አስተማማኝ ፓስፖርት ተብሏል፡፡
ደቡብ አፍሪካ - ለ94 አገሮች ቪዛ አያስፈልግም
ደቡብ አፍሪካውያን ለፓስፖርታቸው ምስጋና ይግባውና ከዓለማችን 194 አገራት ውስጥ ወደ 97 ያህሉ ያለ ቪዛ መግባት ይችላሉ፡፡ የደቡብ አፍሪካ ፓስፖርት ከሲሼልስና ሞሪሽየስ ቀጥሎ በአፍሪካ እጅግ አስተማማኙ ፓስፖርት በመሆን 3ኛ ደረጃን ይዟል፡፡
ቦትስዋና - ለ73 አገሮች ቪዛ አያስፈልግም
የአህጉሪቱ አራተኛው አስተማማኝ ፓስፖርት ያለው በቦትስዋና ዜጎች እጅ ሲሆን ከዓለም በ58ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ የቦትስዋና ፓስፖርት ወደ 73 አገራት ያለ ቪዛ የሚያስገባ ቢሆንም ከዓለማችን 5 ቀዳሚ ፓስፖርቶች አስተማማኝነቱ በ57 በመቶ ዝቅ ያለ ነው፡፡ የፊንላንድ፣ ስውዲን፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ጀርመንና አሜሪካ ዜጎች ቪዛ ሳይጠየቁ ወደ 174 የዓለማችን አገራት መግባት ይችላሉ፡፡
ጋምቢያ - ለ68 አገሮች ቪዛ አያስፈልግም
ጋምቢያ በአፍሪካ 5ኛዋ አስተማማኝ ፓስፖርት ያላት አገር ናት፡፡ የጋምቢያ ፓስፖርት ያለምንም ቪዛ 68 የዓለም አገራትን በነፃነት መጎብኘት ያስችላል፡፡
 ኬንያ - ለ68 አገሮች ቪዛ አያስፈልግም
የኬንያ ፓስፖርት በዓለማችን ላይ ወደሚገኙ 68 አገራት ያለ ቪዛ በነፃነት የሚያስገባ ሲሆን እንደ ጋምቢያ ሁሉ በ5ኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ አስተማማኝ ፓስፖርት ነው፡፡
ሌሴቶ - ለ67 አገሮች ቪዛ አያስፈልግም
የሌሴቶ ፓስፖርት በአፍሪካ 6ኛው አስተማማኝ ፓስፖርት ነው፡፡ የሌሴቶ ፓስፖርት የመግቢያ ቪዛ ሳያስፈልግ የዓለማችን 67 አገራትን ለመጎብኘት ያስችላል፡፡
(በነገራችን ላይ የአገራችን ፓስፖርት ያለ ቪዛ መግባት የሚያስችለው ጎረቤት አገር ኬንያ ብቻ ነው።)

Tuesday, 14 April 2015 08:17

የፀሐፍት ጥግ (ስለምናብ)

ርዕይ የማይታዩ ነገሮችን የማየት ጥበብ ነው፡፡
ጆናታን ስዊፍት
ምናብ ጨርሶ ወደአልነበረ ዓለም ይዞን ይሄዳል፡፡ ያለ እሱ ግን የትም መሄድ አንችልም፡፡
ካርል ሳጋን
ምናቤ አንድ ቀን ወደ ሲኦል የሚያስገባ ፓስፖርት ያመጣልኛል፡፡
ጆን ስቴይንቤክ
(East of Aden)
ምናብ እንደ ጡንቻ ነው፡፡ ብዙ በፃፍኩ ቁጥር እንደሚፈረጥም ተገንዝቤአለሁ፡፡
ፊሊፕ ጆሴ ፋርመር
ምናብህ ከትኩረት ውጭ ሲሆን በዓይንህ ላይ መተማመን አትችልም፡፡
ማርክ ትዌይን
ከምናብ የሚፈጠሩ ታሪኮች ምናብ የሌላቸውን ሰዎች ያበሳጫሉ፡፡
ቴሪ ፕራትሼት
በአቅማቸው ተገድበው የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ በምናብ እጥረት ይሰቃያሉ፡፡
ኦስካር ዋይልድ
በምናብህ መፍጠር የቻልከው ሁሉ እውነት ነው፡፡
ፓብሎ ፒካሶ
ምናብ የሌለው ሰው መብረሪያ ክንፎች የሉትም፡፡
ሙሐመድ አሊ
ምናብ ዓለምን ይገዛል፡፡
ናፖሊዮን ቦናፓርቴ
ሃሳቦችን አፍልቅና በክብር ያዛቸው፤ ከመሃላቸው አንዱ ንጉስ ሊሆን ይችላልና፡፡
ማርክ ቫን ዶሬን
ተጨባጩ ዓለም የሚሸፋፍነውን ሃቅ ልብወለድ ይገላልጠዋል፡፡
ጄሳሚን ዌስት
ምናብ የነፍስ ዓይን ነው፡፡
ጆሴፍ ጁበርት
ዓለምን የሚመሩት ሃሳቦች ናቸው፡፡
ጄምስ ኤ.ጋርፊልድ

“መንግስት የሌሎች አገራትን ያህል የነዳጅ ዋጋ የማይቀንሰው ለምንድነው?” ብለን ግን አንጠይቅም

     በያዝነው ሳምንት እና ከዚያም በፊት በኢዜአ የተሰራጩ ሁለት ሦስት ዜናዎችን ተመልከቱ። በአለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ ቅናሽ እንደታየ የገለፁ የንግድ ሚኒስትር ዴኤታ፤ ከዚሁ ጋር የሸቀጣ ሸቀጦች ዋጋ ላይ ቅናሽ ግን አልታየም ሲሉ የአገሪቱን ነጋዴዎች እንደወቀሱ አትቷል ኢዜአ - ረቡዕ እለት ባሰራጨው ዜና። አዎ፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በአለም ገበያ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በግማሽ ያህል መቀነሱ እውነት ነው። የተጣራ ነዳጅ (ለምሳሌ የቤንዚን) ዋጋም እንዲሁ ቀንሷል - በ35 በመቶ ገደማ። በአገራችንስ ምን ያህል እንዲቀንስ ተደረገ? ወደ 15 በመቶ ገደማ ብቻ ነው የቀነሰው። ዋጋውን የሚተምነው ደግሞ የንግድ ሚኒስቴር ነው። በአገራችን የነዳጅ ዋጋ የሌሎች አገራትን ያህል ያልቀነሰው ለምን ይሆን? ኢዜአ ይህን ጥያቄ ለሚኒስትር ዴኤታው አላቀረበም። ነጋዴዎችን መወንጀል ነው ቀላሉ ነገር።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢኮኖሚክስ ረዳት ፕሮፌሰር ተሾመ አዱኛ፣ የአገሪቱ የንግድ አሰራር የገበያ  ህግንና ስርዓትን እንደማይከተል ጠቅሰው፤ ነጋዴዎች ግልፅነት በጎደለው አርቴፊሻል የዋጋ ትመና እንደሚሰሩ ተናግረዋል ይላል ኢዜአ። “ይህም በመሆኑ፣ በአለም አቀፍ ገበያ የነዳጅ ዋጋ ከ50 በመቶ በላይ በቀነሰበት ወቅት በኢትዮጵያ ሸቀጦች ላይ ግን ቅናሽ ሳይታይ ቀርቷል”በማለት እኚሁ ምሁር ማስረጃ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል። ለመሆኑ ኢኮኖሚስቱና ኢዜአ የት አገር ነው ያሉት? በአለም ገበያ ከታየው የነዳጅ ዋጋ ቅናሽ ጋር የሚመጣጠን የዋጋ ማስተካከያ ኢትዮጵያ ውስጥ ተግባራዊ እንዳይሆን የተደረገው በንግድ ሚኒስቴር የዋጋ ትመና እንጂ በነጋዴዎች ምርጫ አይደለም። በየወሩ የንግድ ሚኒስቴር የሚያወጣውን የዋጋ ተመን ራሱ ኢዜአ ይዘግባልኮ። ግን፤ ይህችን እውነታ ከማገናዘብ ይልቅ፤ የቢዝነስ ሰዎችን በጭፍን የመወንጀል ባህልን ጠብቆ ማቆየትና “ማስቀጠል” ይበልጥብናል መሰለኝ።
የንግድ ሚኒስትር ዴኤታውም እንዲሁ፤ የአገራችን የነዳጅ ዋጋ የሌሎች አገራትን ያህል እንዳይቀንስ የተደረገው በመስሪያ ቤታቸው የዋጋ ትመናና ውሳኔ መሆኑን ይዘነጉታል? ከአለም የነዳጅ ገበያ ጋር በአገራችን የሸቀጦች ዋጋ ያልቀነሰው ነጋዴዎች በሚከተሉት ብልሹ አሰራር ምክንያት እንደሆነ ነው ሚኒስትር ዴኤታው የሚናገሩት። ምን የሚባል ብልሹ አሰራር? ሚኒስትር ዴኤታው አንድ ሁለት እያሉ ይዘረዝራሉ። በንግዱ ማህበረሰብ ውስጥ ዋጋን በስምምነት የመወሰን አሰራር አለ ብለዋል። የተለያዩ ኩባንያዎችን በማዋሃድ ሞኖፖል የመፍጠር አሰራርም አለ ብለዋል።
እስቲ አስቡት። ኢትዮጵያ ውስጥ፣ የኩባንያ ባለአክሲዮኖች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጣሉ ኩባንያቸውን ለሁለት ለሶስት ሲሰነጥቁ እንጂ፤ ውህደት ሲፈጥሩ አይታችኋል? ወይስ ስለ ሌላ አገር ነው የሚናገሩት? የቢዝነስ ሰዎች የሸቀጦችን ዋጋ በስምምነት ሲወስኑስ የሚታዩትስ የት ነው? ኢትዮጵያ ውስጥ በተመሳሳይ ቢዝነስ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች፣ የሸቀጦችን ዋጋ በስምምነት ሊወስኑ ይቅርና፤ ሰላምታ ለመለዋወጥም ያህል የመቀራረብ ልምድ የላቸውም። የገበያ ውድድርን እንደጠላትነት ነው የሚቆጥሩት። ለነገሩ ሚኒስትር ዴኤታውም ይህንን እውነት አይክዱም። በንግድ ማህበረሰብ ውስጥ፣ ሁልጊዜ በተወዳዳሪነት ለመቀጠል በፅናትና በትጋት የመስራት ባህልን ከማሳደግ ይልቅ፤ አንዱ ተወዳዳሪ ሌላውን ለማጥፋት የመመኘት ባህል እንደሚታይ ገልፀዋል ዴኤታው።
እና እንዲህ አይነት ባህል ይታይባቸዋል የተባሉት ነጋዴዎች፤ በምን ተአምር ነው ከእለት ተእለት የሸቀጦችን ዋጋ በምክክር ለመወሰንና ከዚያም አልፈው ኩባንያዎቻቸውን ለማዋሃድ የሚስማሙት? ግን፤ እንዲህ አይነቶችን ጥያቄዎች እያነሳን ነገሩን መመርመር አንፈልግም - ብዙዎቻችን። በአጠቃላይ ለቢዝነስ ስራዎች አወንታዊ አመለካከት የለንማ። እንዲኖረንም አንፈልግማ። አንዳንዶቻችን ከእውቀት እጥረትና እጦት የተነሳ፤ የቢዝነስ ስራንና የቢዝነስ ሰዎችን በክፉ አይን እንመለከታለን። በእድሜ ገፋ ያሉት ብዙዎቹ ምሁራን፤ የደርግ አይነት የሶሻሊዝም አባዜ ተጠናውቷቸው “በዝባዥ ከበርቴዎችን” በመፈክር ማውገዝ ይናፍቃቸዋል። አንዳንዶቹ ወጣት ምሁራንም እንዲሁ፤ የቢዝነስ ስራንና የቢዝነስ ሰዎችን የሚያወግዝ የትምህርት ቅኝት ውስጥ ተነክረው ከወጡ በኋላ፤ ዞር ብለው ነገሩን ለመመርመር አይሞክሩም። ያንኑን ቅኝት ሲያስተጋቡ ይኖራሉ። በዚያ ላይ... ብዙዎቻችን በደፈናውና በጭፈን የታቀፍነው ነባሩ ፀረ-ቢዝነስ ቱባ ባህላችን ከጉያችን እንዲርቅ ፈቃደኞች አይደለንም። በማናቸውም ሰበብ ነጋዴዎችንና የቢዝነስ ሰዎችን በጭፍን ማውገዝና መወንጀል ለብዙዎቻችን ሱስ ሆኖብናል ማለት ይቻላል።
እንዲያ ባይሆን ኖሮማ፤ እውነታውን ለማየትና ለማገናዘብ ዳተኛ ባልሆንን ነበር። ከደርግ የሶሻሊዝም ስርዓት ወዲህ፤ መጠነኛ የነፃ ገበያ አሰራር በመፈጠሩ ብቻ፤ የቢዝነስና የንግድ ውድድር እንደተሻሻለ የበርካታ ኢኮኖሚስቶች ጥናት ያረጋግጣል። በየጊዜው የዋጋ ንረት የሚፈጠረውም፤ መንግስት አለቅጥ በሚያሳትመው የብር ኖት ምክንያት እንደሆነ የመንግስት መረጃዎች ያረጋግጣሉ። በ2000 ዓ.ም፣ ከዚያም እንደገና በ2003 ዓ.ም ጣራ የነካ የዋጋ ንረት የተፈጠረው፤ በሌላ ሰበብ ሳይሆን የብር ኖር በገፍ ስለታተመ ነው። የአገሪቱ ውስጥ የተሰራጨው የብር ኖት በግማሽ አመት ውስጥ በሃምሳ በመቶ ያህል ሲጨምር፤ ብር መርከሱና የዋጋ ንረት መከሰቱ ይገርማል እንዴ? ይሄው ነው በ2003 ዓም የተከሰተው። ራሱ መንግስት ለፓርላማ ያቀረበው ሪፖርት መሆኑንም ልብ በሉ።
እንዲያም ሆኖ፤ ሁሌም በነጋዴዎችና በቢዝነስ ሰዎች ላይ ነው የሚሳበበው። ለመሆኑ፤ ባለፉት ሶስት ዓመታት የዋጋ ንረቱ ረገብ ያለው፤ የነጋዴዎችና የቢዝነስ ሰዎች ባሕርይ ስለተለወጠ ይሆን? አይደለም። መንግስት የብር ህትመቱን ረገብ ስላደረገ ነው የዋጋ ንረት የተረጋጋው - ሙሉ ለሙሉ ባይጠፋም። እውነታው የዚህን ያህል ግልፅ ቢሆንም፤ ነጋዴዎችንና የቢዝነስ ሰዎችን በጭፍን የማውገዝ ሱሳችን እንዲቀርብን ስለማንፈልግ፤ እውነታውን አይተን እንዳላየን ማለፍን እንመርጣለን።
እስቲ ተመልከቱ። ከአመት በፊት የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በበርሜል፣ 110 ዶላር ገደማ ነበር። መቶ ሊትር ቤንዚን ወደ ኢትዮጵያ የሚገባው ደግሞ በ100 ዶላር ገደማ እየተገዛ ወጪ ነበር። ያኔ የአንድ ሊትር የችርቻሮ ዋጋ በንግድ ሚኒስቴር ተመን 20 ብር ከ50 ሳንቲም ነበር የምንገዛው። ካለፈው ሰኔ በኋላ የነዳጅ ዋጋ መቀነስ ሲጀምር፣ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ወደ መቶ ዶላር፤ የመቶ ሊትር ቤንዚን ዋጋ ደግሞ ወደ 95 ዶላር ገደማ ወረደ - በነሐሴ ወር። ነገር ግን፤ የንግድ ሚኒስቴር በወቅቱ የችርቻሮ ዋጋ ለመቀነስ አልፈለገም። በአለም ገበያ ግን የነዳጅ ዋጋ በዚህ አላቆመም።
መስከረምና ጥቅምት ላይ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ወደ ዘጠና ብር፣ ከህዳር በኋላ ከሰባ ዶላር በታች ወርዶ ታህሳስ ላይ ነው 60 ቤት የገባው። የብሔራዊ ባንክ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ ከጥቅምት እስከ ታህሳስ ወር ባለው ጊዜ ውስጥ፣ መቶ ሊትር ቤንዚን በአማካይ በ72 ዶላር ወጪ ነው ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ የነበረው። እንግዲህ አስቡት። የመቶ ሊትር ቤንዚን ዋጋ ከመቶ ዶላር ወደ 72 ዶላር ቀንሷል። ከታህሳስ ወዲህ ደግሞ ከ65 ዶላር በታች ሆኗል። በብር ሲመነዘር አንዱ ሊትር ከ13 ብር በታች ይሆናል ማለት ነው። የንግድ ሚኒስቴር ግን፤ የነዳጅ የችርቻሮ የአለም ገበያን በሚመጥን ሁኔታ እንዲቀንስ አላደረገም። 20 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረውን የአንድ ሊትር ቤንዚን ዋጋ፤ ቢያንስ ቢያንስ ወደ 14 ብር ማውረድ ነበረበት። ግን አላደረገውም። 17 ብር ከ50 ነው ያደረገው።
ለምን? የተለያዩ አጓጉል ምክንያቶች ሲቀርቡ እንደነበር ታስታውሱ ይሆናል። በአለም ገበያ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ቢቀንስም የቤንዚን ዋጋ ያን ያህልም አልቀነሰም የሚል ሰበብ ቀርቦ ነበር። ይሄ ሃሰት ነው። የአለም ዋጋ ከመቀነሱ በፊት፣ ለበርካታ ወራት እየጨመረ ስለነበረ፣ ብዙም ለውጥ የለውም የሚል ማመካኛም ቀርቦ ነበር። ይሄም ሃሰት ነው። የነዳጅ ዋጋ ካለፈው ሰኔ ወር በፊት ለሁለት አመታት ያህል ብዙ ውጣውረድ አልነበረውም። እና እውነተኛው ምክንያት ምንድነው? ማለቴ የንግድ ሚኒስቴር የነዳጅ መሸጫ ዋጋ በአግባቡ ያልቀነሰበት ምክንያት ምንድነው? እስቲ በኢዜአ የተሰራጨ ሌላ ዜና ተመልከቱ።     
በአለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ በመቀነሱ መንግስት እንደተጠቀመ የገለፀው ኢዜአ፤ በስምንት ወራት ውስጥ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ወጪ ለማዳን ተችሏል ሲል ዘግቧል። 20 ቢሊዮን ብር መሆኑ ነው። ነዳጅ ወደ አገር የሚገባበት ወጪ ከቀነሰ፤ ለምን የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በዚያው መጠን አልቀነሰም? መንግስት እንዳሰኘው ሊያተርፍብን ፈርልጎ ይሆን? የንግድ ሚኒስትር ዴኤታ በሰጡት ምላሽ፣ የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በተወሰደነ ደረጃ ብቻ እንደቀነሰ ጠቅሰው፤ ሌላው ትርፍ ግን እስካሁን የተከማቸ የውጭ እዳ ለመክፈል እየዋለ መሆኑን ገልፀዋል።

ከዕለታት አንድ ቀን አንድ አዋቂና አንድ አላዋቂ በመንገድ ላይ እየተጓዙ ሳለ አንድ አውራዶሮ አጥር ላይ ሆኖ ሲጮህ ያያሉ፡፡
ይሄኔ አላዋቂው፤
“ይሄ አውራ ዶሮ እዚህ መሬት ላይ ሲጮህ‘ኮ እመንግስተ - ሰማይም ልክ ይሄንኑ የሚመስል አውራ ዶሮ በዚሁ ሰዓት ይጮሃል” ይላል፡፡
አዋቂው አዋቂ ነውና፤
“እኔ አይመስለኝም” ይላል፡፡
አላዋቂው፤
“ለምን? አስረዳኛ!”
አዋቂው፣
“አየህ እንደ ዶሮ ያለ ልክስክስና ኩሳም ነገር መንግስተ-ሰማይን ያህል ንፁህ ቦታ አይገባም” አለው፡፡
አላዋቂው አላዋቂ ነውና ለምን እሸነፋለሁ ባይ ነው፡፡
“አይ ዶሮው ሲጮህ አፉን ወደ መንግስተ-ሰማይ፣ ቂጡን ወደ ሲዖል አድርጎ ስለሆነ ምንም ችግር አይኖርም” ይላል፡፡
አዋቂው፤ አዋቂ ነውና አልለቀቀውም፡፡
“እኔ እንደሰማሁት ሲዖል እርጥቡን የሰው ስጋ እንኳን እንደጉድ ያነደዋል ነው የሚባለው፡፡ እንዲህ ያለውን የአውራ ዶሮ ላባማ እንዴት አድርጎ ይምረዋል?” ሲል ጠየቀ፡፡
ይሄኔ አላዋቂው፤ ቆጣና ፍጥጥ ብሎ፤
“ዎ!ዎ! እኔ ምን ቸገረኝ ያባቴ ዶሮ አይደለ ቢያንበገብገው?!” አለ፡፡
*       *       *
በየግል መድረኩ፤ በየመሸታ ቤቱ፣ በየሻይ ቤቱ፣ በየሬስቶራንቱ ወዘተ…  በዕውቀት መከራከር ከቀረ ውሎ አድሯል፡፡ የተማረ የማይከበርበት፣ ያልተማረ ዘራፍ ሲል የሚደመጥበት ሁኔታ እየበረከተ የመጣበት ዘመን ነው፡፡ በመናገርና አውቆ በመናገር መካከል ልዩነቱ ከመከነ ሰንብቷል! አገሩን፤ “እኔ ምን ቸገረኝ ያባቴ ዶሮ አደለች!” ብሎ በምንግዴ የሚያየው ዜጋ በሚያስገርም ሁኔታ እንደባክቴሪያ የሚራባበት አየር እየተፈጠረ ነው፡፡ አገርን መሰረት አድርጎ ፖለቲካን፣ ኢኮኖሚን አሊያም ባህልን ማየት የተነወረበት ጊዜ እየመጣ ይመስላል፡፡ አለማወቅና ስግብግብነት ሲቀናጁ ምን ዓይነት አደጋ ላይ እየጣሉን እንደሆነ ማየት ተስኖናል፡፡
ካፒታሊዝም፤ እናት - አይምሬ ነው! የገዛ ወላጁን ሳይበላ የማይተኛ ሥርዓት ነው፡፡ ሼክስፔር እንደሚለው፤
“ያባትክን አሟሟት ሰበብ፣ ለማወቅ ሲፈላ ደምህ
ወዳጁንም ጠላቱንም፣ አብሮ መጥረግ ነው በቀልህ??” ሊባል የሚችል ጣጣ ውስጥ እየገባን እንደሆነ ማስተዋል ደግ ነው
ካፒታሊዝም፤ “ለሰላምታም ለጭብጨባም ቫት የሚከፈልበት መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን” ሊያሰኘን የሚችል ምስጥም ዐይን - አውጣም ስርዓት መሆኑን አንዘንጋ፡፡ በአሁኑ ሰዓት ዕውቀት የሚያቀጭጭ ክፉ ባህል ጭበጨባ ነው! አደጋም ነው! ባመኑበትም ባላመኑበትም ማጨብጨብ፣ ባወቁትም ባላወቁትም ማጨብጨብ እርግማን ነው፡፡ ምክን (Reason) የማይገዛው ማህበረሰብ ለገደል ቅርብ ነው ይላሉ ጸሀፍት፡፡
“እባካችሁ ክቡር እምክቡራን
የተከበሩ፣ አቶ ወይም ወ/ሮ እገሌን ወደ መድረኩ ጋብዙልኝ” ይላል የመድረክ መሪው፡፡ ከዚያ ጭብጨባ ነው፡፡ ቸብ! ቸብ! ቸብ! ትንሽ ቆይቶ፤ “እባካችሁ የተከበሩ ክቡር እምክቡራን አቶ ወይም ወይዘሮ እገሌን ወደቦታቸው ሸኙልኝ!” አሁንም ቸብ!...ቸብ!...ቸብ!... ይቀጥላል፡፡ የጭብጨባ ባህል! የፓርቲ አባል ያጨበጭባል፡፡ የድርጅት አባል ያጨበጭባል፡፡ የጎሣ አባል ያጨበጭባል፡፡ ጓደኛና ቲፎዞ ያጨበጭባል፡፡ የተማረው ያጨበጭባል! ያልተማረው ያጨበጭባል! አዋቂው ያጨበጭባል! አላዋቂው ያጨበጭባል! ሃይማኖተኛው ያጨበጭባል! ሃይማኖት - አልባው ያጨበጭባል! የኪነ-ጥበቡ ሰው እያጨበጨበ ጭብጨባ ይቀላውጣል!... ከዚህ የጭብጨባ ባህል ማን ይገላግለን ይሆን? ለጭብጨባም የአየር ሰዓት የሚጠየቅበት ወቅት እየመጣ ነው፡፡
ከማቴሪያል ሙስና ወደ ህሊና ሙስና እየተሸጋገርን ይመስላል! የድንቁርና ሙስናና የዕውቅና ሙስና ምን ያህል እንደሚተጋገዙ የምናይበት ጊዜ ሩቅ አይደለም፡፡ ይሄ ሁሉ ሆኖ አውራ - ዶሮው መጮሁን ይቀጥላል፡፡ የውሻና ግመሎቹ ነገር (The dog barks but the caravan goes) አብቅቶ፤ ግመሎቹም ውሻዎቹም አውራ - ዶሮውን እያዳመጡ መከራከር የጀመሩበት ጊዜ ነው፡፡ አውራ ዶሮ የጮኸውን ያህል ክርክሩም ይጮሃል፡፡ ያገራችን ነገረ በተመለደና ባልተለወጠ ነገረ - ሥራ መጯጯህ መሆኑ ያሳዝናል!
ልማዳዊ አካሄዳችን አልለወጥ የሚለው ለውጥ ስለሌለ ይሆን? ሁሉ ነገር የልማድ፣ የወግ፣ የወረት (የfashion) ተገዢ የሆነ መምሰሉ ይገርማል፡፡ የእገሌ ራዕይ፣ ራዕይ፣ ራዕይ … እንደጀመርን … እንደጀመርን … (አንዴ ከገባንበት ስሜት ዓይነት ጭምር)… እንዳጋመስን … እንዳጋመስን … ስንጨርስስ? … እንደጨረስን… እንጨርሰዋለን … እንዳይሆን ያሰጋል፡፡ ከዘፈን ወደ መፈክር መሄድ፣ ከዘፈን ወደ ዘፈን ከመሄድ የተሻለ ነው ወይ? የሚለውን ለማረጋገጥ መሞከር ብልህነት ነው፡፡
የእኛው ፀሐፌ ተውኔት፣ ገጣሚ ፀጋዬ ገ/መድህን የሚለንን መስማት ደግ ነው፡-
“አንድ የፍየል ሙክት ቆዳ እያለፋ ስልቻ የሚያወጣና የሚያዜም ሰራተኛ ነበር፡፡ ደግሞ ጆሮ ደግፍ ይዞታል፡፡ እና ቆዳ ሲያለፋ በረገጠ ቁጥር ያመው ነበር፡፡ በዚያ ምክንያት ዘፈኑ ይበላሽበትና ወደ ለቅሶ ይለወጥበታል፡፡ ወደ ህመም ይለወጥበታል፡፡ ግን ህመሙን በዘፈኑ ማስታመም እንጂ ከእዚያ እቤት የሚሰማውን ቻቻታ መስማት አይፈልግም፡፡ እዚያማ የሙክቱ ሥጋ ይበላል፡፡ ሰዎች በደስታ ያሳልፋሉ፡፡ እሱ ግን እዚህ ቆዳ እያለፋ ይሰቃያል”
ያው ያንዱ ደስታ ላንዱ ዋይታ ነው፡፡ “ህመምን በዘፈን ማስታመም” አንዱ በሽታችን ነው፡፡ ፖለቲካችን የዚህ በሽታ ልክፍት እንዳለበት ልብ ካላልን አንድንም!
የሀገራችን ኢኮኖሚ፤ እሱን ተከትሎም የኑሮ ደረጃውን፤ ማመዛዘን ግራ አጋቢ ነው፡፡ በዚህ ፋሲካ ወይም በሌላ ማናቸውም ክብረ በዓል የሰውን አኗኗር ለማሰብ ብንሞክር፤ …ከዓመታት በፊት ዶሮ እንዴትና በምን ዋጋ ይበላ እንደነበር የሚተርክ ሰው ይገኛል፡፡ ዛሬ አይበላም፤ “አይ ኑሮ” ይላል፡፡ ሌላው ዶሮ አርዷል፡፡ በግም አርዷል፡፡ “የቅርጫውን ዋጋ አልቻልነውም‘ኮ፤ ይሄ ኑሮ ውድነት ተጫወተብን! አይ ኑሮ!” ይላል፡፡
የመጨረሻው ዶሮም አለው፡፡ በግም አርዷል፡፡ “በሬው ግን ከቄራ ይገዛ ወይስ ተነድቶ ከገጠር ይምጣ? ቀረጡ፣ ማስነጃው ሰማይ ወጣ እኮ!” “አይ ኑሮ!” እያለ ያማርራል፡፡ በዚህ ኢኮኖሚ ጥላ ሥር ፖለቲከኛው የራሱ ቋንቋ ነው ያለው፡፡ አሰብ ቢመለስ ኖሮ… አሥመራ ገብተን ቢሆን ኖሮ… በቂ የአየር ጊዜ ቢሰጠን ኖሮ… ሰብዓዊ መብት ቢከበር ኖሮ… ዲሞክራሲ ዕውነት ቢሆን ኖሮ… ኮንዶምኒየም በር የለው፣ መስኮት የለው፤ ውሃ የለው… የፕሬስ ችግር ቢፈታ ኖሮ…” አይ ኑሮ
አገራችን ከምትችለው በላይ ኑሮና ኗሪ ተሸክማ የምትጓዝ ናት፡፡ ይሄን ሁሉ ኑሮ፣ ድህነትና ሃሳዊ ጥጋብ መፍቻ ቁልፉ፣ የህዳሴው ግድብ ከነዙሪያ ገባ ዲፕሎማሲው ነው… ለማለት ለጤናማ ኢኮኖሚስትም ለጤናማ ሀገራዊ ፖለቲከኛም ያስቸግራል፡፡ አንድ ያላት ጥርስ በዘነዘና ትነቀስ አይሆንም፡፡ ዶሮ ብታልም ጥሬዋንም አይሠራም፡፡ ዘርፈ - ብዙና መረበ - ብዙ መፍትሔ እናገኝ ዘንድ ዘርፈ - ብዙ ልብ ይስጠን፡፡
በትንሣኤው ስለትንሣኤው እናስብ ዘንድ ልብና ልቦና ይስጠን!!” “ለሰው እንተርፋለን እንኳን ለራሳችን” የሚለው የዱሮ መፈክር፣ ትዝ ይለናል፡፡ ሁሌ እንግዳ ተቀባይ ነን እንደምንል ሁሉ፣ ሁሌ ለጋሥ ነን ማለትን እንፈልገዋለን፤ ቅንነታችን የተባረከ ይሁን!
በተጨባጭና ከልብ እንግዳ ተቀባይ፣ በተጨባጭና ከልብ ያለን የተረፈንና ለሌላ የምንለግስ ልንሆን ይገባል፡፡ በመብራቱም፣ በውሃውም፣ በቡናውም፣ በጤፉም፣ በበጉም በከብቱም የዚህ ዕውነታ ዕሙን ሊሆን ይገባል፡፡ አለበለዚያ “ሳይተርፋት አበድራ ሳትቀበል ሞተች” የሚለው ተረት ዕሙን ይሆናል!!   

“መንግስት የሌሎች አገራትን ያህል የነዳጅ ዋጋ የማይቀንሰው ለምንድነው?” ብለን ግን አንጠይቅም
     በያዝነው ሳምንት እና ከዚያም በፊት በኢዜአ የተሰራጩ ሁለት ሦስት ዜናዎችን ተመልከቱ። በአለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ ቅናሽ እንደታየ የገለፁ የንግድ ሚኒስትር ዴኤታ፤ ከዚሁ ጋር የሸቀጣ ሸቀጦች ዋጋ ላይ ቅናሽ ግን አልታየም ሲሉ የአገሪቱን ነጋዴዎች እንደወቀሱ አትቷል ኢዜአ - ረቡዕ እለት ባሰራጨው ዜና። አዎ፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በአለም ገበያ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በግማሽ ያህል መቀነሱ እውነት ነው። የተጣራ ነዳጅ (ለምሳሌ የቤንዚን) ዋጋም እንዲሁ ቀንሷል - በ35 በመቶ ገደማ። በአገራችንስ ምን ያህል እንዲቀንስ ተደረገ? ወደ 15 በመቶ ገደማ ብቻ ነው የቀነሰው። ዋጋውን የሚተምነው ደግሞ የንግድ ሚኒስቴር ነው። በአገራችን የነዳጅ ዋጋ የሌሎች አገራትን ያህል ያልቀነሰው ለምን ይሆን? ኢዜአ ይህን ጥያቄ ለሚኒስትር ዴኤታው አላቀረበም። ነጋዴዎችን መወንጀል ነው ቀላሉ ነገር።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢኮኖሚክስ ረዳት ፕሮፌሰር ተሾመ አዱኛ፣ የአገሪቱ የንግድ አሰራር የገበያ  ህግንና ስርዓትን እንደማይከተል ጠቅሰው፤ ነጋዴዎች ግልፅነት በጎደለው አርቴፊሻል የዋጋ ትመና እንደሚሰሩ ተናግረዋል ይላል ኢዜአ። “ይህም በመሆኑ፣ በአለም አቀፍ ገበያ የነዳጅ ዋጋ ከ50 በመቶ በላይ በቀነሰበት ወቅት በኢትዮጵያ ሸቀጦች ላይ ግን ቅናሽ ሳይታይ ቀርቷል”በማለት እኚሁ ምሁር ማስረጃ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል። ለመሆኑ ኢኮኖሚስቱና ኢዜአ የት አገር ነው ያሉት? በአለም ገበያ ከታየው የነዳጅ ዋጋ ቅናሽ ጋር የሚመጣጠን የዋጋ ማስተካከያ ኢትዮጵያ ውስጥ ተግባራዊ እንዳይሆን የተደረገው በንግድ ሚኒስቴር የዋጋ ትመና እንጂ በነጋዴዎች ምርጫ አይደለም። በየወሩ የንግድ ሚኒስቴር የሚያወጣውን የዋጋ ተመን ራሱ ኢዜአ ይዘግባልኮ። ግን፤ ይህችን እውነታ ከማገናዘብ ይልቅ፤ የቢዝነስ ሰዎችን በጭፍን የመወንጀል ባህልን ጠብቆ ማቆየትና “ማስቀጠል” ይበልጥብናል መሰለኝ።
የንግድ ሚኒስትር ዴኤታውም እንዲሁ፤ የአገራችን የነዳጅ ዋጋ የሌሎች አገራትን ያህል እንዳይቀንስ የተደረገው በመስሪያ ቤታቸው የዋጋ ትመናና ውሳኔ መሆኑን ይዘነጉታል? ከአለም የነዳጅ ገበያ ጋር በአገራችን የሸቀጦች ዋጋ ያልቀነሰው ነጋዴዎች በሚከተሉት ብልሹ አሰራር ምክንያት እንደሆነ ነው ሚኒስትር ዴኤታው የሚናገሩት። ምን የሚባል ብልሹ አሰራር? ሚኒስትር ዴኤታው አንድ ሁለት እያሉ ይዘረዝራሉ። በንግዱ ማህበረሰብ ውስጥ ዋጋን በስምምነት የመወሰን አሰራር አለ ብለዋል። የተለያዩ ኩባንያዎችን በማዋሃድ ሞኖፖል የመፍጠር አሰራርም አለ ብለዋል።
እስቲ አስቡት። ኢትዮጵያ ውስጥ፣ የኩባንያ ባለአክሲዮኖች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጣሉ ኩባንያቸውን ለሁለት ለሶስት ሲሰነጥቁ እንጂ፤ ውህደት ሲፈጥሩ አይታችኋል? ወይስ ስለ ሌላ አገር ነው የሚናገሩት? የቢዝነስ ሰዎች የሸቀጦችን ዋጋ በስምምነት ሲወስኑስ የሚታዩትስ የት ነው? ኢትዮጵያ ውስጥ በተመሳሳይ ቢዝነስ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች፣ የሸቀጦችን ዋጋ በስምምነት ሊወስኑ ይቅርና፤ ሰላምታ ለመለዋወጥም ያህል የመቀራረብ ልምድ የላቸውም። የገበያ ውድድርን እንደጠላትነት ነው የሚቆጥሩት። ለነገሩ ሚኒስትር ዴኤታውም ይህንን እውነት አይክዱም። በንግድ ማህበረሰብ ውስጥ፣ ሁልጊዜ በተወዳዳሪነት ለመቀጠል በፅናትና በትጋት የመስራት ባህልን ከማሳደግ ይልቅ፤ አንዱ ተወዳዳሪ ሌላውን ለማጥፋት የመመኘት ባህል እንደሚታይ ገልፀዋል ዴኤታው።
እና እንዲህ አይነት ባህል ይታይባቸዋል የተባሉት ነጋዴዎች፤ በምን ተአምር ነው ከእለት ተእለት የሸቀጦችን ዋጋ በምክክር ለመወሰንና ከዚያም አልፈው ኩባንያዎቻቸውን ለማዋሃድ የሚስማሙት? ግን፤ እንዲህ አይነቶችን ጥያቄዎች እያነሳን ነገሩን መመርመር አንፈልግም - ብዙዎቻችን። በአጠቃላይ ለቢዝነስ ስራዎች አወንታዊ አመለካከት የለንማ። እንዲኖረንም አንፈልግማ። አንዳንዶቻችን ከእውቀት እጥረትና እጦት የተነሳ፤ የቢዝነስ ስራንና የቢዝነስ ሰዎችን በክፉ አይን እንመለከታለን። በእድሜ ገፋ ያሉት ብዙዎቹ ምሁራን፤ የደርግ አይነት የሶሻሊዝም አባዜ ተጠናውቷቸው “በዝባዥ ከበርቴዎችን” በመፈክር ማውገዝ ይናፍቃቸዋል። አንዳንዶቹ ወጣት ምሁራንም እንዲሁ፤ የቢዝነስ ስራንና የቢዝነስ ሰዎችን የሚያወግዝ የትምህርት ቅኝት ውስጥ ተነክረው ከወጡ በኋላ፤ ዞር ብለው ነገሩን ለመመርመር አይሞክሩም። ያንኑን ቅኝት ሲያስተጋቡ ይኖራሉ። በዚያ ላይ... ብዙዎቻችን በደፈናውና በጭፈን የታቀፍነው ነባሩ ፀረ-ቢዝነስ ቱባ ባህላችን ከጉያችን እንዲርቅ ፈቃደኞች አይደለንም። በማናቸውም ሰበብ ነጋዴዎችንና የቢዝነስ ሰዎችን በጭፍን ማውገዝና መወንጀል ለብዙዎቻችን ሱስ ሆኖብናል ማለት ይቻላል።
እንዲያ ባይሆን ኖሮማ፤ እውነታውን ለማየትና ለማገናዘብ ዳተኛ ባልሆንን ነበር። ከደርግ የሶሻሊዝም ስርዓት ወዲህ፤ መጠነኛ የነፃ ገበያ አሰራር በመፈጠሩ ብቻ፤ የቢዝነስና የንግድ ውድድር እንደተሻሻለ የበርካታ ኢኮኖሚስቶች ጥናት ያረጋግጣል። በየጊዜው የዋጋ ንረት የሚፈጠረውም፤ መንግስት አለቅጥ በሚያሳትመው የብር ኖት ምክንያት እንደሆነ የመንግስት መረጃዎች ያረጋግጣሉ። በ2000 ዓ.ም፣ ከዚያም እንደገና በ2003 ዓ.ም ጣራ የነካ የዋጋ ንረት የተፈጠረው፤ በሌላ ሰበብ ሳይሆን የብር ኖር በገፍ ስለታተመ ነው። የአገሪቱ ውስጥ የተሰራጨው የብር ኖት በግማሽ አመት ውስጥ በሃምሳ በመቶ ያህል ሲጨምር፤ ብር መርከሱና የዋጋ ንረት መከሰቱ ይገርማል እንዴ? ይሄው ነው በ2003 ዓም የተከሰተው። ራሱ መንግስት ለፓርላማ ያቀረበው ሪፖርት መሆኑንም ልብ በሉ።
እንዲያም ሆኖ፤ ሁሌም በነጋዴዎችና በቢዝነስ ሰዎች ላይ ነው የሚሳበበው። ለመሆኑ፤ ባለፉት ሶስት ዓመታት የዋጋ ንረቱ ረገብ ያለው፤ የነጋዴዎችና የቢዝነስ ሰዎች ባሕርይ ስለተለወጠ ይሆን? አይደለም። መንግስት የብር ህትመቱን ረገብ ስላደረገ ነው የዋጋ ንረት የተረጋጋው - ሙሉ ለሙሉ ባይጠፋም። እውነታው የዚህን ያህል ግልፅ ቢሆንም፤ ነጋዴዎችንና የቢዝነስ ሰዎችን በጭፍን የማውገዝ ሱሳችን እንዲቀርብን ስለማንፈልግ፤ እውነታውን አይተን እንዳላየን ማለፍን እንመርጣለን።
እስቲ ተመልከቱ። ከአመት በፊት የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በበርሜል፣ 110 ዶላር ገደማ ነበር። መቶ ሊትር ቤንዚን ወደ ኢትዮጵያ የሚገባው ደግሞ በ100 ዶላር ገደማ እየተገዛ ወጪ ነበር። ያኔ የአንድ ሊትር የችርቻሮ ዋጋ በንግድ ሚኒስቴር ተመን 20 ብር ከ50 ሳንቲም ነበር የምንገዛው። ካለፈው ሰኔ በኋላ የነዳጅ ዋጋ መቀነስ ሲጀምር፣ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ወደ መቶ ዶላር፤ የመቶ ሊትር ቤንዚን ዋጋ ደግሞ ወደ 95 ዶላር ገደማ ወረደ - በነሐሴ ወር። ነገር ግን፤ የንግድ ሚኒስቴር በወቅቱ የችርቻሮ ዋጋ ለመቀነስ አልፈለገም። በአለም ገበያ ግን የነዳጅ ዋጋ በዚህ አላቆመም።
መስከረምና ጥቅምት ላይ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ወደ ዘጠና ብር፣ ከህዳር በኋላ ከሰባ ዶላር በታች ወርዶ ታህሳስ ላይ ነው 60 ቤት የገባው። የብሔራዊ ባንክ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ ከጥቅምት እስከ ታህሳስ ወር ባለው ጊዜ ውስጥ፣ መቶ ሊትር ቤንዚን በአማካይ በ72 ዶላር ወጪ ነው ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ የነበረው። እንግዲህ አስቡት። የመቶ ሊትር ቤንዚን ዋጋ ከመቶ ዶላር ወደ 72 ዶላር ቀንሷል። ከታህሳስ ወዲህ ደግሞ ከ65 ዶላር በታች ሆኗል። በብር ሲመነዘር አንዱ ሊትር ከ13 ብር በታች ይሆናል ማለት ነው። የንግድ ሚኒስቴር ግን፤ የነዳጅ የችርቻሮ የአለም ገበያን በሚመጥን ሁኔታ እንዲቀንስ አላደረገም። 20 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረውን የአንድ ሊትር ቤንዚን ዋጋ፤ ቢያንስ ቢያንስ ወደ 14 ብር ማውረድ ነበረበት። ግን አላደረገውም። 17 ብር ከ50 ነው ያደረገው።
ለምን? የተለያዩ አጓጉል ምክንያቶች ሲቀርቡ እንደነበር ታስታውሱ ይሆናል። በአለም ገበያ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ቢቀንስም የቤንዚን ዋጋ ያን ያህልም አልቀነሰም የሚል ሰበብ ቀርቦ ነበር። ይሄ ሃሰት ነው። የአለም ዋጋ ከመቀነሱ በፊት፣ ለበርካታ ወራት እየጨመረ ስለነበረ፣ ብዙም ለውጥ የለውም የሚል ማመካኛም ቀርቦ ነበር። ይሄም ሃሰት ነው። የነዳጅ ዋጋ ካለፈው ሰኔ ወር በፊት ለሁለት አመታት ያህል ብዙ ውጣውረድ አልነበረውም። እና እውነተኛው ምክንያት ምንድነው? ማለቴ የንግድ ሚኒስቴር የነዳጅ መሸጫ ዋጋ በአግባቡ ያልቀነሰበት ምክንያት ምንድነው? እስቲ በኢዜአ የተሰራጨ ሌላ ዜና ተመልከቱ።     
በአለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ በመቀነሱ መንግስት እንደተጠቀመ የገለፀው ኢዜአ፤ በስምንት ወራት ውስጥ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ወጪ ለማዳን ተችሏል ሲል ዘግቧል። 20 ቢሊዮን ብር መሆኑ ነው። ነዳጅ ወደ አገር የሚገባበት ወጪ ከቀነሰ፤ ለምን የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በዚያው መጠን አልቀነሰም? መንግስት እንዳሰኘው ሊያተርፍብን ፈርልጎ ይሆን? የንግድ ሚኒስትር ዴኤታ በሰጡት ምላሽ፣ የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በተወሰደነ ደረጃ ብቻ እንደቀነሰ ጠቅሰው፤ ሌላው ትርፍ ግን እስካሁን የተከማቸ የውጭ እዳ ለመክፈል እየዋለ መሆኑን ገልፀዋል።


     በቅርቡ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ መቀነሱን ተከትሎ በትራንስፖርት አገልግሎት ታሪፍ ላይ ቅናሽ ቢደረግም በፋሲካ ገበያ የሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ ማሳየቱን ሸማቾችና ነጋዴዎች ተናገሩ፡፡
የአዲስ አድማስ ሪፖርተሮች በአዲስ አበባ በሚገኙ የተለያዩ የገበያ ስፍራዎች ተዘዋውረው ባደረጉት ቅኝት፤ ሠንጋ በሬዎች ከ8ሺህ እስከ 17 ሺህ ብር ሲሸጡ፣ የፍየል ዋጋ ከዓምናው የፋሲካ በአል የ300 ብር ጭማሪ በማሳየት ከ2ሺ 4500 ብር እየተሸጠ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የበግ ዋጋ በሾላ ገበያ ትንሹ 1500 ብር፣ መካከለኛው እስከ 1800ብር እንዲሁም ትልቁ  እስከ 3500 ብር ሲሸጥ፣ በሣሪስና ጐተራ አካባቢ ትንሹ እስከ 1800 ብር፣ መካከለኛው 2500 ብር፣ ትላልቅ የሚባሉት ደግሞ እስከ 4000 ብር የሚገኙ ሲሆን መሲና የሰቡ ሴት በጐች ከ2200 እስከ 3ሺህ ብር እየተሸጡ ነው፡፡
በሾላ ገበያ የሚገኘው የከብቶች መሸጫ ቦታ በመንግስት በመውሰዱ፣ ሰሞኑን ነጋዴዎች ከደንብ አስከባሪዎች ጋር እየተሳደዱ በየመንገዱ ሲሸጡ የነበረ ሲሆን ከከተማው ርቆ በሚገኘው የካራ ገበያ እንዲጠቀሙ ማሳሰቢያ እንደተሰጣቸውም ተናግረዋል፡፡ የካራ የገበያ ቦታ ግን ደንበኞቻቸውን ለማግኘት ምቹ ባለመሆኑ በየመንገዱ ለመሸጥ መገደዳቸውን ነጋዴዎቹ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡
በከተማዋ ያሉ አንዳንድ እንቁላል አቅራቢ ድርጅቶች አንዱን እንቁላል በ2.50 ብር ሂሳብ ሲሸጡ፣ በየአካባቢው ያሉ ሱቆችና መደብሮች ደግሞ ከ3.00 ብር እስከ 3.50 እየሸጡ ይገኛሉ፡፡ የእንቁላል ዋጋ ከዓምናው የትንሳኤ በዓል ከ1.00 ብር እስከ 1.75 ብር ድረስ ጭማሪ ማሳየቱንም ነጋዴዎችና ሸማቾች ተናግረዋል፡፡
ሽንኩርት በኪሎ ከ12.00 ብር እስከ 12.50 ብር እየተሸጠ ሲሆን ከወትሮው ገበያ እምብዛም የዋጋ ለውጥ እንዳልታየበትና ካለፈው ዓመት ጋርም ተመሳሳይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ የቅቤ ዋጋ በአሉን ተከትሎ የጨመረ ሲሆን በአብዛኞቹ ገበያዎች 1ኛ ደረጃ የሚባለው ቅቤ 185 ብር በኪሎ ሲሸጥ፣ ከዚያ በታች የሆኑት ከ165 እስከ 175 ብር በኪሎ እየተሸጡ ነው፡፡
ሳሪስ አካባቢ የበዓል ሸቀጦች ሲሸምቱ ያገኘናቸው ወ/ሮ ፀዳለ ይልማ፤ የትራንስፖርት ዋጋ መቀነሱን ተከትሎ የበዓል ሸቀጦች ዋጋ ቅናሽ እንደሚያሳይ ገምተው እንደነበር ጠቁመው ሆኖም እንደገመቱት ሳይሆን መቅረቱን ተናግረዋል፡፡
ጎተራ መስቀል ፍላወር አካባቢ በጎች ሲሸጥ ያገኘነው ጉልማ ዳዲ፤የበግ ዋጋ ከወትሮው የጨመረው ገበሬው ዋጋ በመጨመሩ ነው ብሏል። ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ ከሚገኘው ፍቼ በጎቹን እንደሚያመጣ የጠቆመው ነጋዴው፤ ገበሬው ካለፈው የገና በዓል በኋላ እንኳ በአንድ በግ ከ150 እስከ 200 ብር ጭማሪ ማድረጉን ገልጿል፡፡
በሾላ ገበያ አስፓልት ዳር በጎቹን ሲሸጥ ያገኘነው ነጋዴም ከደብረ ብርሃንና ለአዲስ አበባ ቅርብ ከሆኑ የኦሮሚያ አካባቢዎች በጎች እያመጣ እንደሚሸጥ ጠቁሞ፤ ገበሬው ከ200 እስከ 300 መቶ ብር የዋጋ ጭማሪ ማድረጉን ተናግሯል፡፡ ያነጋገርናቸው አንዳንድ የበሬ ነጋዴዎች በበኩላቸው፤ በበሬ ዋጋ ላይ ካለፉት በአላት እምብዛም የዋጋ ጭማሪ አለመስተዋሉን ገልፀዋል፡፡
በበአላት ወቅት በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚዘጋጁ የጐዳና ላይ የንግድ ባዛሮች  እንደ አንድ የገበያ አማራጭ የሚታዩ ቢሆንም በዋጋ አንፃር ከመደበኛ የገበያ ስፍራዎች ብዙም ለውጥ እንደሌላቸው ሸማቾች ይናገራሉ። ኢንተርፕራይዞቹ ከመንግስት ነፃ የንግድ ቦታ የተመቻቸላቸው እንደመሆኑ ዋጋቸው ከፍተኛ ግብር ከሚከፍሉት ነጋዴዎች እኩል መሆን አልነበረበትም የሚሉት ሸማቾች፤ ለመንግስት ግብር ሣይከፍሉ ህብረተሰቡን በዋጋ መበዝበዛቸው ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡
በለገሃር አካባቢ በተዘጋጀው የንግድ ባዛር ላይ ጫማ ሲገዙ ያገኘናቸው አንድ ሸማች፤ በመደበኛ ቡቲኮች ከ250 እስከ 400 ብር የሚሸጡ ጫማዎች በባዛሮቹም ላይ በተመሳሳይ ዋጋ ሲሸጡ መታዘባቸውን ጠቁመዋል፡፡ የአልኮል መጠጦችም በተመሳሳይ በግሮሰሪዎች ከሚሸጡበት ዋጋ ምንም ለውጥ እንደሌላቸው ሸማቾች ጠቅሰው፤ ባዛሮቹ በመንግስት ድጋፍ የሚዘጋጁ እንደመሆናቸው ዋጋቸው ቅናሽ ማሳየት ነበረበት ብለዋል፡፡ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተደራጁ ነጋዴዎች በበኩላቸው፣ እንዲህ ያለውን ዕድል የምናገኘው በዓመት ውስጥ ለተወሰኑ ጊዜያት ብቻ በመሆኑ ቅናሽ ማድረግ አያዋጣንም ብለዋል፡፡

     የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቻይና በየአመቱ በሚካሄደው “ኢንደስትሪ ጎልደን ቼር አዋርድስ” በተሰኘ አለማቀፍ ሽልማት የዓመቱ ምርጥ አየር መንገድ ተብሎ ለሁለተኛ ጊዜ መሸለሙን አስታወቀ፡፡
አየር መንገዱ ባወጣው መግለጫ እንዳለው፤ ለስምንተኛ ጊዜ በተካሄደውና በአለማቀፍ ደረጃ የላቀ አፈጻጸም ያሳዩ አየር መንገዶች፣ ሆቴሎች፣ የጉዞ ወኪሎችና የቱሪዝም መዳረሻዎች በሚሸለሙበት በዚህ ዝግጅት ተሸላሚ መሆኑ እንደሚያኮራቸው ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም ተናግረዋል፡፡
ሽልማቱን ለሚያዘጋጀው ኤምአይሲኢ የተባለ መጽሄት፣ እንዲሁም ለአየር መንገዱ ድምጻቸውን በመስጠት ለተሸላሚነት ላበቁት የቻይና ደንበኞችም ዋና ሥራ አስፈፃሚው ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዘመናዊዎቹና በምቹዎቹ 787 እና 777 አውሮፕላኖቹ ቻይና ውስጥ ወደሚገኙት የቤጂንግ፣ የሻንጋይ፣ ጉዋንግዡና ሆንግ ኮንግ መዳረሻዎች በየሳምንቱ በድምሩ 28 በረራዎችን በማድረግ ምርጥና ፈጣን አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
በዘንድሮው የፈረንጆች አመት ኤር ትራንስፖርት ወርልድ በተባለው ታዋቂ የአቪየሽን ዘርፍ መጽሄት “ቤስት ሪጅናል ኤርላይን” የተሰኘ ሽልማት የተሰጠው አየር መንገዱ፣ ባለፈው አመትም ከአሜሪካ ታዋቂ የጉዞ መጽሄቶች አንዱ በሆነው ፕሪሚየር ትራቭለር “የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ” ተብሎ መሸለሙንም መግለጫው አስታውሷል፡፡ በ “ፓሴንጀር ቾይዝ” እና በአፍሪካ አየር መንገዶች ማህበርም፣ “ቤስት ኤርላይን ኢን አፍሪካ” እና “አፍሪካን ኤርላይን ኦፍ ዘ ይር” ሽልማቶችን መሸለሙንም አክሎ ገልጿል፡፡

 ከዚህ በፊትም መታጠቢያ ክፍል ውስጥ ያገኘችውን የአልማዝ ቀለበት ለባለቤቱ መልሳለች
-በኳታር በመታጠቢያ ቤት ውስጥ ያገኘቻቸውን 129 ሺህ ዶላር የሚያወጡ ሁለት የአልማዝ የጣት ቀለበቶች ለባለቤቶቹ ያስረከበችው ኢትዮጵያዊት የጽዳት ሰራተኛ፣ ላሳየችው ታማኝነት በአሰሪዎቿ መሸለሟን ዶሃ ኒውስ ዘገበ፡፡
አንድነት ዘለቀው የተባለችው የ32 አመት ኢትዮጵያዊት የጽዳት ሰራተኛ፣ በምትሰራበት የኳታር ብሄራዊ የስብሰባ ማዕከል መታጠቢያ ክፍል ውስጥ ተረስተው ላለፉት አራት አመታት በማዕከሉ በጽዳት ሰራተኛነት ተቀጥራ ስትሰራ ለቆየችው አንድነት የገንዘብ ስጦታውን ያበረከቱት የማዕከሉ ዋና ስራ አስኪጅ ኬን ጄሚሰን፣ ግለሰቧ ያሳየችው የታማኝነት ተግባር እንደሚያስመሰግናትና ለማዕከሉም ኩራት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ቀለበቶቹን ባገኘችበት ቅጽበት፣ ይሄኔ የቀለበቶቹ ባለቤት እንደጠፋት ስታውቅ ምን ይሰማት ይሆን የሚል ስሜት እንደተሰማትና ባአፋጣኝ ለማዕከሉ ረዳት ስራ አስኪያጅ ደውላ ስለጉዳዩ በመንገር ቀለበቶቹን እንደመለሰች አንድነት ለዶሃ ኒውስ ተናግራለች፡፡ ታማኝነት ታላቁ የህይወት መርህ እንደሆነ አምናለሁ ስትልም ተናግራለች፡፡ አንድነት ከዚህ በፊትም አል ሙክታር በተባለ የኳታር የጽዳት ኩባንያ ውስጥ ተቀጥራ በምትሰራ ወቅት ውድ ዋጋ የሚያወጣ ከአልማዝ የተሰራ የጣት ቀለበት በመታጠቢያ ክፍል ውስጥ ወድቆ አግኝታ ለባለቤቶቹ ማስረከቧን ዘገባው አስታውሷል፡፡
የጣት ቀለበቶቹ ባለፈው የካቲት ወር በማዕከሉ በተካሄደው የዶሃ የጌጣጌጦችና የእጅ ሰዓቶች ኤግዚቢሽን ላይ የጠፉ እንደነበሩ ያስታወሰው ዘገባው፤ ማእከሉ ለኢትዮጵዊቷ የሸለመው ገንዘብ ምን ያህል እንደሆነ አለመገለፁን ጠቁሟል፡፡

    የ1997 ዓ.ም የኮንዶሚኒየም ቤት ፈላጊዎች ምዝገባ ሂደት የተወሳሰቡ ችግሮች የነበሩበት በመሆኑ ለተመዝጋቢዎች የመረጃ ሰነድ መጥፋትና አሁን ድረስ ለዘለቁ በርካታ ቅሬታዎች መነሻ ሆኗል ተባለ፡፡
በወቅቱ ምዝገባው በአዲስ አበባ አስሩም ክፍለከተሞችና በሌሎች ተቋማት የተከናወነ ሲሆን ሁሉም ወገን የምዝገባ ተራ ቁጥሮችን ከ001 የጀመሩ በመሆናቸው መረጃዎቹ ወደ አንድ ማዕከል ሲሰባሰቡ የመደበላለቅ ችግር ፈጥሯል ያሉት የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ሥራ አሥኪያጅ አቶ መስፍን መንግስቱ፤ አንድ ግለሰብ በተለያዩ መዝጋቢ ተቋማት ሶስትና አራት ጊዜ የተመዘገበበት አጋጣሚ እንዳለም ገልፀዋል፡፡
የምዝገባ ማረጋገጫ የነበረውን ቢጫ ካርድ ተመሳሳይ ቁጥር እስከ 15 የሚደርሱ ግለሰቦች ይዘው ወደ ማዕከሉ እንደሚቀርቡ ያስረዱት አቶ መስፍን፤ “ሁሉም መረጃዎች በአንድ ማዕከል ተሰባስበው ከተራ ቁጥር 001 እስከ 453ሺህ ድረስ በመቀመጡ፣ እነሱ ቁጥራችን የሚሉትና ሲስተሙ የሚያውቀው የምዝገባ ቁጥር የተለያዩ ናቸው” ብለዋል፡፡
ለወቅቱ ቤት ፈላጊዎች ምዝገባ እንደ ችግር የተጠቀሰው ሌላው ጉዳይ የ97 ምርጫን ተከትሎ የተፈጠረው ግርግር መረጃን በተገቢው መንገድ ለማደራጀት አለማስቻሉ ነው ይላሉ አቶ መስፍን። በወቅቱ ከተማዋን እንዲያስተዳድር አደራ የተሰጠው የባለአደራ አስተዳደር ስራውን ተላምዶ ወደ ተግባር እስኪገባ ድረስ መረጃዎቹ በተገቢው መንገድ ተይዘው ነበር ለማለት አያስደፍርም ብለዋል - ሃላፊው፡፡
በወቅቱ የተበላሸውን ለማስተካከል በርካታ ስራዎች መሠራታቸውን የጠቀሱት ሃላፊው፤ በ2005 ዓ.ም በተደረገው ምዝገባ፤ “መረጃን ጠፍቶብናል” ያሉ ቤት ፈላጊዎች በነባር የምዝገባ ስርአት ውስጥ ተካተው እንዲስተናገዱ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
የጋራ መኖሪያ ቤቶች መሠረተልማት ሳይሟላላቸው ለተጠቃሚዎች ይተላለፋሉ በማለት የቤት ባለቤቶች ቅሬታ የሚያቀርቡ ሲሆን የገላን ሶስት ኮንደሚኒየም ነዋሪዎች እስካሁን ድረስ የመብራት አገልግሎት እንደሌላቸው፣ በሌላው የገላን ሳይት ደግሞ የግቢው መንገድ በተገቢው መንገድ ባለመስተካከሉ ለአደጋ የተጋለጡ መሆናቸውን ይናገራሉ፡፡ ሃላፊው በበኩላቸው፤ የነዚህ ቅሬታዎች መነሻ ከመሠረተ ልማት ጋር ተያይዞ የነበሩ ክፍተቶች ናቸው ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም የቤቶቹ ግንባታ 80 በመቶ ሲደርስ እድለኞች እንዲረከቡ ይደረግ እንደነበር የጠቆሙት ሃላፊው፤ በአሁን ወቅት ግን መቶ በመቶ ተጠናቀውና መሠረተ ልማት ተሟልቶላቸው እንደሚተላለፉ ገልፀዋል። በፊት ለነዋሪዎች መሠረተ ልማት ሳይሟላላቸው የተላለፉትም በአሁን ወቅት ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሟላላቸው እንደሆነ ሃላፊው ጨምረው ገልፀዋል፡፡ “አካባቢውን ለኑሮ የሚመች ማድረግ ግን የነዋሪው ሃላፊነት ነው” ብለዋል ሃላፊው፡፡
በስም አሊያም በሌላ የማጭበርበር ዘዴ በህገወጥ መንገድ የኮንዶሚኒየም ቤት ተጠቃሚ የሆኑ ግለሰቦች ካሉ ህብረተሰቡ በጥቆማ ማጋለጥ እንደሚገባው ያሳሰቡት አቶ መስፍን፤ እንዲህ ያሉ ችግሮች በተደጋጋሚ  እንደሚያጋጥሙ ሳይጠቅሱ አላለፉም፡፡  

     የየመን ሁቲዎች በባብኤል መንደብ በሚገኙ ደሴቶች ላይ ያከማቹት ከባድ የጦር መሳሪያ በአለምአቀፉ የመርከብ እንቅስቃሴ ላይ ስጋት እንደጋረጠ የጠቆመችው ጅቡቲ፤ በሳዑዲ አረቢያ የሚመራውና የመን ላይ ወታደራዊ እርምጃ በመውሰድ ላይ የሚገኘው ጥምር ሀይል እንዲያስወግደው ጠየቀች፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ ብዙ የባህር ላይ እንቅስቃሴዎችን በማስተናገድ የሚታወቀው የቀይባህር የፀጥታና ደህንነት ሁኔታ በየመኑ ሁቲ አማፂያን ምክንያት ስጋት እንደተጋረጠበት መረጃዎች ይጠቁማሉ። ኢትዮጵያ በብቸኝነት የምትጠቀምበት ወደብ ባለቤት የሆነችው ጅቡቲ፤ የሁቲዎቹ እንቅስቃሴ በአለም አቀፉ የመርከቦች ደህንነት ላይ ስጋት መደቀኑን አስታውቃለች፡
የጅቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ ሰሞኑን በሰጡት መግለጫ፤ አገራቸው ጥምር ሀይሉን እንደምትደግፍ ጠቁመው በባብኤል መንደብ ሰርጥ  ባሉ ደሴቶች ላይ በሁቲዎች የተከማቸው ከባድ የጦር መሳሪያ ለአለም አቀፍ የመርከቦች ዝውውር ስጋት በመሆኑ በጥምር ሀይሉ እንዲወገድ ጠይቀዋል፡፡
 በቀይባህር በኩል የተፈጠረው የፀጥታና የደህንነት ስጋት በኢትዮጵያ መርከቦች ጉዞ ላይ የፈጠረውን ሁኔታ በተመለከተ ለማጣራት ያደረግነው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡