Administrator

Administrator

ባለፈው ቅዳሜ በኔፓል በተከሰተውና በሬክተር ስኬል 7.8 በተመዘገበው አሰቃቂ የርዕደ-መሬት አደጋ የሟቾች ቁጥር ከ5ሺህ በላይ መድረሱ መረጋገጡን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡
በርዕደ-መሬቱ የተጎዱ ዜጎችን የማፈላለጉና እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎችን የመድረሱ እንቅስቃሴ በአስቸጋሪ የአየር ንብረት ሳቢያ አዳጋች ሆኖ የቀጠለ ሲሆን እስካለፈው ረቡዕ ድረስ ለህልፈተ ህይወት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከ5ሺህ በላይ መድረሱን ዘገባው አመልክቷል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፤ በአደጋው ከሞቱት በተጨማሪ ከ10ሺህ በላይ ሰዎችም የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ሲሆን፣ ፍለጋው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የሟቾችም ሆነ የቁስለኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር ተገምቷል፡፡  
ኔፓልን መልሶ ለማቋቋም ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ያስፈልጋል ተብሎ እንደሚገመት ያስታወቀው ዘገባው፣ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት በበኩሉ፤ በአደጋው የደረሰው ጥፋት እስከ 10 ቢሊዮን ዶላር እንደሚገመት መግለጹን አስታውቋል፡፡ ባለፈው ማክሰኞ ከሰዓት በኋላ ላንግታንግ በተባለችው የኔፓል አካባቢ በደረሱ ሁለት የመሬት መንሸራተት አደጋዎች፣ ከ200 በላይ ሰዎች የደረሱበት እንደጠፋም ዘገባው ጠቁሟል፡፡
የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሱሺል ኮይራላ በአደጋው ህይወታቸው ያለፈ ዜጎችን ለመዘከር ባለፈው ማክሰኞ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ብሄራዊ ሃዘን ያወጁ ሲሆን ባለፉት አስር አመታት በርዕደ-መሬት ሳቢያ ለህልፈተ ህይወት የተዳረጉ ዜጎች ቁጥር ከ10 ሺህ በላይ እንደሚደርስም አስታውቀዋል፡፡
በአደጋው የተጎዱ ዜጎች ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የድረሱልኝ ጥያቄ እያቀረቡ እንደሚገኙ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በሂሊኮፕተር የታገዘ እንቅስቃሴ እየተደረገ ቢገኝም፣ ከፍተኛ ዝናብና ውሽንፍር ከመኖሩና ከቦታዎቹ ተራራማነት ጋር በተያያዘ፣ በከፋ ሁኔታ በተጎዱ አካባቢዎች ፈጥኖ ለመድረስ አስቸጋሪ እየሆነ መምጣቱንም ገልጸዋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የቅዳሜው የኔፓል ርዕደ-መሬት ስምንት ሚሊዮን ያህል ሰዎችን ተጠቂ እንዳደረገ ያስታወቀ ሲሆን፣ ለአስቸኳይ የአደጋ ጊዜ እርዳታ የሚውል 15 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
የተመድ ቃል አቀባይ ፋራህ ሃቅ እንዳሉት፤ የገንዘብ ድጋፉ ተጎጂዎችን ለመታደግ በመስራት ላይ የሚገኙ የሰብዓዊ ተቋማትን እንቅስቃሴ ለማሳደግና ለተጎጂዎቹ የመጠለያ፣ የውሃ፣ የመድሃኒትና የሌሎች አገልግሎቶች አቅርቦቶችን ለማሟላት የሚውል ነው።
ህንድ፣ አሜሪካ፣ ቻይና፣ ማሌዢያ፣ ፓኪስታን እና እስራኤል ተጎጂዎችን ለመርዳት የሚደረገውን እንቅስቃሴ ለመደገፍ አውሮፕላኖችን ወደ ኔፓል የላኩ ሲሆን አሜሪካ በበኩሏ ለፈጥኖ ደራሽ እርዳታ የሚውል 10 ሚሊዮን ዶላር ለመለገስ ቃል ከመግባቷ በተጨማሪ የእርዳታ ድርጅቶቿን በአደጋው የተጎዱትን ዜጎች እንዲረዱ ወደ ኔፓል ልካለች፡፡

- ዋና ዋናዎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫው አልተሳተፉም
- ምዕራባውያን አገራት ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ አይደለም ብለዋል

 ዋና ዋናዎቹ የሱዳን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ነጻና ፍትሃዊ አይሆንም በሚል ራሳቸውን ባገለሉበት የአገሪቱ ምርጫ የተወዳደሩት ፕሬዚዳንት ኡመር ሃሰን አልበሽር፤ 94.5 በመቶ ድምጽ በማግኘት በቀጣይም አገሪቱን በፕሬዚዳንትነት እንዲመሩ መመረጣቸውን ቢቢሲ ዘገበ።የአገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን ሃላፊ ሙክታር አል አሳም ባለፈው ሰኞ ከካርቱም በሰጡት መግለጫ፣ ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲን በመወከል ለፕሬዚዳንትነት የተወዳደሩት አልበሽር፤ ከ5 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ድምጽ በማግኘት ማሸነፋቸውን ያስታወቁ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በበኩሉ፤ ድምጽ ለመስጠት ከተመዘገቡት 13.3 ሚሊዮን ዜጎች ውስጥ ድምጽ የሰጡት አንድ ሶስተኛ ያህሉ ብቻ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ አልበሽር በዘንድሮው የሱዳን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ይህ ነው የሚባል ፉክክር እንዳልገጠማቸው የዘገበው ዘጋርዲያን በበኩሉ፣ ከተፎካካሪዎች መካከል የተሻለ ድምጽ ያገኙት ፌደራል ትሩዝ ፓርቲን ወክለው የተወዳደሩት ፋደል አልሳይድ ሹያብ መሆናቸውንና ያገኙት ድምጽም 1.43 በመቶ ብቻ መሆኑን አስታውቋል።ከሚያዝያ 5 ቀን ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት በመላ አገሪቱ በተቋቋሙ 11 ሺህ የድምጽ ጣቢያዎች በተከናወነው የድምጽ አሰጣጥ ስነስርአት ላይ ድምጽ ለመስጠት ከተመዘገቡት ውስጥ ሁለት ሶስተኛው ድምጽ አለመስጠታቸውንና ለፕሬዚዳንታዊ ምርጫው በተፎካካሪነት የቀረቡት 15 እምብዛም እውቅና የሌላቸው ዕጩ ተወዳዳሪዎች ብቻ እንደነበሩም አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡ አሜሪካ፣ እንግሊዝና ኖርዌይን ጨምሮ በርካታ ምዕራባውያን አገራት፣ ላለፉት 25 አመታት ሱዳንን በፕሬዚዳንትነት የመሩት አልበሽር፤ በከፍተኛ ድምጽ ያሸነፉበትንና ባለፈው ሰኞ የተከናወነውን የአገሪቱ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ነጻና ፍትሃዊ አይደለም፣ እውቅና አንሰጠውም ሲሉ የተቹት ሲሆን፣ የቻይናው ፕሬዚደንት ዢ ጂፒንግ በበኩላቸው፤ ለአልበሽር የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት ልከዋል፡፡
ስቲስ ኤንድ ኢኳሊቲ ሙቭመንት የተባለው የአገሪቱ አማጺ ቡድን ባለፈው እሁድ በደቡብ ዳርፉር አካባቢ በሱዳን መንግስት ጦር ላይ በከፈተው ወታደራዊ ጥቃት የጦር ካምፕ ማውደሙንና የጦር መሳሪያዎችን መማረኩን ያስታወቀ ሲሆን፣ የአገሪቱ የጦር ሃይል በበኩሉ አማጽያኑ በሚንቀሳቀሱበት አካባቢ ባደረገው ድብደባ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱን አስታውቋል፡፡ በአየር ድብደባው 16 ሲቪል ዜጎች መሞታቸውንና ከ11 በላይ የሚሆኑ ደግሞ መቁሰላቸውን የዘገበው አይቢታይምስ ነው፡፡
በዳርፉር ግጭት የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽመዋል በሚል በአለማቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክስ የቀረበባቸውና የእስር ማዘዣ የተቆረጠባቸው የ71 አመቱ አልበሽር፣ ድርጊቱን አልፈጸምኩም ሲሉ ተቃውሟቸውን ማሰማታቸውን ዘገባው ጨምሮ አስታውሷል፡
ፕሬዚዳንት አልበሽር እ.ኤ.አ በ1989 በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ከያዙበት ጊዜ አንስቶ አገሪቱን እየመሩ ሲሆን ሱዳንን ለረጅም ጊዜ በመምራት ቀዳሚው ሰው እንደሆኑ ይታወቃል፡፡

ባለፈው ቅዳሜ በኔፓል በተከሰተውና በሬክተር ስኬል 7.8 በተመዘገበው አሰቃቂ የርዕደ-መሬት አደጋ የሟቾች ቁጥር ከ5ሺህ በላይ መድረሱ መረጋገጡን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡
በርዕደ-መሬቱ የተጎዱ ዜጎችን የማፈላለጉና እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎችን የመድረሱ እንቅስቃሴ በአስቸጋሪ የአየር ንብረት ሳቢያ አዳጋች ሆኖ የቀጠለ ሲሆን እስካለፈው ረቡዕ ድረስ ለህልፈተ ህይወት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከ5ሺህ በላይ መድረሱን ዘገባው አመልክቷል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፤ በአደጋው ከሞቱት በተጨማሪ ከ10ሺህ በላይ ሰዎችም የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ሲሆን፣ ፍለጋው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የሟቾችም ሆነ የቁስለኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር ተገምቷል፡፡  
ኔፓልን መልሶ ለማቋቋም ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ያስፈልጋል ተብሎ እንደሚገመት ያስታወቀው ዘገባው፣ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት በበኩሉ፤ በአደጋው የደረሰው ጥፋት እስከ 10 ቢሊዮን ዶላር እንደሚገመት መግለጹን አስታውቋል፡፡ ባለፈው ማክሰኞ ከሰዓት በኋላ ላንግታንግ በተባለችው የኔፓል አካባቢ በደረሱ ሁለት የመሬት መንሸራተት አደጋዎች፣ ከ200 በላይ ሰዎች የደረሱበት እንደጠፋም ዘገባው ጠቁሟል፡፡
የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሱሺል ኮይራላ በአደጋው ህይወታቸው ያለፈ ዜጎችን ለመዘከር ባለፈው ማክሰኞ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ብሄራዊ ሃዘን ያወጁ ሲሆን ባለፉት አስር አመታት በርዕደ-መሬት ሳቢያ ለህልፈተ ህይወት የተዳረጉ ዜጎች ቁጥር ከ10 ሺህ በላይ እንደሚደርስም አስታውቀዋል፡፡
በአደጋው የተጎዱ ዜጎች ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የድረሱልኝ ጥያቄ እያቀረቡ እንደሚገኙ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በሂሊኮፕተር የታገዘ እንቅስቃሴ እየተደረገ ቢገኝም፣ ከፍተኛ ዝናብና ውሽንፍር ከመኖሩና ከቦታዎቹ ተራራማነት ጋር በተያያዘ፣ በከፋ ሁኔታ በተጎዱ አካባቢዎች ፈጥኖ ለመድረስ አስቸጋሪ እየሆነ መምጣቱንም ገልጸዋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የቅዳሜው የኔፓል ርዕደ-መሬት ስምንት ሚሊዮን ያህል ሰዎችን ተጠቂ እንዳደረገ ያስታወቀ ሲሆን፣ ለአስቸኳይ የአደጋ ጊዜ እርዳታ የሚውል 15 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
የተመድ ቃል አቀባይ ፋራህ ሃቅ እንዳሉት፤ የገንዘብ ድጋፉ ተጎጂዎችን ለመታደግ በመስራት ላይ የሚገኙ የሰብዓዊ ተቋማትን እንቅስቃሴ ለማሳደግና ለተጎጂዎቹ የመጠለያ፣ የውሃ፣ የመድሃኒትና የሌሎች አገልግሎቶች አቅርቦቶችን ለማሟላት የሚውል ነው።
ህንድ፣ አሜሪካ፣ ቻይና፣ ማሌዢያ፣ ፓኪስታን እና እስራኤል ተጎጂዎችን ለመርዳት የሚደረገውን እንቅስቃሴ ለመደገፍ አውሮፕላኖችን ወደ ኔፓል የላኩ ሲሆን አሜሪካ በበኩሏ ለፈጥኖ ደራሽ እርዳታ የሚውል 10 ሚሊዮን ዶላር ለመለገስ ቃል ከመግባቷ በተጨማሪ የእርዳታ ድርጅቶቿን በአደጋው የተጎዱትን ዜጎች እንዲረዱ ወደ ኔፓል ልካለች፡፡

 በሰከንድ 10 ማይል፤ በሰዓት 603 ኪ.ሜ ይፈተለካል

በአለማችን በፍጥነቱ አቻ የማይገኝለት የተባለውና በጃፓን የተሰራው ፈጣን ባቡር ባለፈው ማክሰኞ ከብረወሰን ባስመዘገበ ፍጥነት የሙከራ ጉዞ ማድረጉን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡በጃፓኗ ያማናሺ ከተማ የሙከራ ጉዞ ያደረገው ባቡሩ፤ በሰዓት 603 ኪሊ ሜትር ፍጥነት ሲጓዝ ያዩት የአካባቢዋ ነዋሪዎች ያዩትን ነገር ለማመን ተቸግረው እንደነበር ዘገባው ገልጧል፡፡
እ.ኤ.አ በ2027 መደበኛ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ የሚጠበቀው ይሄው ፈጣን ባቡር፣ ከተለመደው አካሄድ በተለየ ሃዲዱን ሳይነካ በማግኔቲክ ፊልድ በ10 ሲንቲ ሜትር ከፍታ የሚጓዝ ነው ተብሏል፡፡
ከዚህ በፊት የአለማችንን የፈጣን ባቡር ክብረወሰን ይዞ የነበረው፣ ሌላ የኩባንያው ምርት የሆነ ባቡር እንደነበረ ያስታወሰው ዘገባው፣ ይሄው ባቡር ከ12 አመታት በፊት በሰዓት 581 ኪሎሜትር ፍጥነት ተጉዞ እንደነበር ገልጧል፡፡
በአሁኑ ሰዓት አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው የአለማችን ፈጣን ባቡር በቻይና የተሰራና በሰዓት 431 ኪሎሜትሮችን የመጓዝ አቅም ያለው ነው፡፡

Saturday, 02 May 2015 11:50

የኩከምበር ፋይዳ!

  ኩከምበር (የፈረንጅ ዱባ) ጀምግባችን ውስጥ አዘውትሮ የማይካተትና አብዛኛዎቻችን የማንመገበው የአትክልት አይነት ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ተክል ሰውነታችን በዕለት ከሚያስፈልጉት የንጥረ ነገር ፍጆታዎች አብዛኛዎችን አካቶ የያዘና ለጤና እጅግ ጠቃሚ  ነው፡፡
ቫይታሚን ቢ1፣ ቢ2፣ ቢ3፣ ቢ5፣ እና ቢ6፣ ፎሊክ አሲድ፣ ቫይታሚን ሲ፣ ካልሲየም፣ አይረን፣ ማግኔዚየም፣ ፎስፌት ፖታሲየም እና ዚንክን ይዟል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኩከምበር በቂ ስኳር እና ኤሌክትሮላይትስ የተባሉ ንጥረ ነገሮችን የያዘ ነው፡፡ እነዚህ ለሰውነታችን እጅግ ጠቃሚ የሆኑ ንጥረ ነገሮቹን ሁሉ አካቶ የያዘው ኩከምበር ምን ጠቀሜታዎች አሉት? ጥቂቶቹን እንመልከት፡፡
ድካም ሲሰማዎት
ከድካም ስሜትዎ ለመላቀቅና እንቅልፍ እንቅልፍ እያሰኘ ከሚጫጫንዎ የድብርት ስሜት ለመንቃት ወፈር ያለ ቡና አዘው ይሆናል … እስቲ ቡናዎን ያስቀምጡና በቀጫጭኑ የተቆራረጡ ጥቂት የኩከምበር ቁራጮችን ይመገቡ፡፡ ድካምዎ ጠፍቶ ስሜትዎ ሲነቃቃ ይሰማዎታል፡፡ የቫይታሚን ቢዎችና የካርቦ ሃይድሬትስ መገኛ የሆነው የኩከምበር ፍሬ ለድካም ፍቱን መድኀኒት ነው፡፡
ሃንግኦቨር ወይንም ከባድ የራስ ምታት ይዞዎታል?
ከከባድ አልኮል መጠጥ በኋላ ወይንም የራስ ምታት ህመም ሲሰማዎ ጥቂት የኩከምበር ቁራጮችን ይመገቡና ለጥቂት ደቂቃዎች አረፍ ይበሉ፡፡ የስኳር፣ የቫይታሚን ቢ እና የኤሌክትሮላይትስ መገኛ የሆነው ኩከምበር ሃንግኦቨርዎን አጥፍቶ፣ ከከባድ የራስ ምታት ህመምዎ ይገላግልዎታል፡፡ ሰውነታችን የራስ ምታት ህመም የሚያጋጥመው ከላይ የተገለፁት ንጥረነገሮች ሲያንሱት ነው፡፡
አካልዎም ሆነ መንፈስዎ ድካም ሲሰማው
ወደ ማሳጅ ቤቶች ሄደው ሰውነትዎን ዘና የሚያደርጉ እሽታዎችን ለማግኘት ይሞክሩ ይሆናል፡፡ ሆኖም በቀላሉ አንድ የኩከምበር ፍሬን ቆራርጠው በሙቅ ውሃ ውስጥ ይዘፍዝፉትና በእሳት ጥደው እንዲፍለቀለቅ ያድርጉት፡፡ እንፋሎቱ ደስ የሚል የመዝናናት ስሜት ከመፍጠሩም በላይ ለአፍንጫ ደስ የሚያሰኝ ጠረንም ያመነጫል፡፡ ይህ በተለይ ለአራስ እናቶች ጠቀሜታው የትየለሌ ነው፡፡
የአፍ ጠረን ችግር አለብዎ?
አንድ የኩከምበር ቁራጭ ወስደው በምላስዎ የላይኛው ክፍልና በላንቃዎ መካከል አጣብቀው ለ30 ሰከንዶች ያህል የያዙት፡፡ መጥፎው የአፍ ጠረንዎ በፍጥነት ይወገዳል፡፡ በኩከምበር ውስጥ የሚገኘው ፓይቶኬሚካል የሚባለው ንጥረነገር በአፍ ውስጥ የሚገኙና ለመጥፎ ጠረን መንስኤ የሚሆኑ ባክቴሪያዎችን ይገድላል፡፡
የሻወር ቤት መስታወትዎ ጉም እያዘለ ያስቸግርዎታል?
ሻወር ከወሰዱ በኋላ የሻወር ቤት መስታዎትዎ ጉም እያዘለ የሚያስቸግርዎ ከሆነ በኩከምበር ቁራጭ መስታወትዎን ያፅዱ፡፡ በሚገርም ሁኔታ መስታዎትዎ ጥርት ያለ እንዲሆን ከማድረጉም በላይ የመታጠቢያ ቤትዎ የስፓ አይነት ጠረን እንዲኖረው ያደርግልዎታል፡፡
በተለያዩ ነገሮች ለተበላሹ ወረቀቶችና የቤትዎ ግድግዳ …
የቤትዎ ግድግዳ ላይ በተለያዩ ቀለማት የተፃፉ ፅሁፎችን ወይም በጭቃና በልዩ ልዩ ነገሮች የተበላሸ የቤትዎን ግድግዳ በኩከምበር ቁራጭ ቀስ እያሉ ይፈግፍጉት፡፡ ግድግዳዎ ወደ ቀድሞ መልኩ ይመለሳል፡፡ በእስክሪብቶ እየፃፉ ሲሳሳቱም፣ የተሳሳቱትን ጽሁፍ በኩከምበር ቁራጭ ቀስ እያሉ ያጥፉት፡፡

   እንቅልፍ ከዓለም መሸሸጊያ ጥግ ነው፡፡ ከህይወት ተፋቶ፤ ከኑሮ ተለይቶ ሌላ ዓለም ውስጥ መግባት ነው፤ መተኛት፡፡
በእንቅልፍ ቡልኮ መጋረድ፣ ከዓለም ለተኳረፈ ምቹ ምሽግ ነው፡፡ ህይወት ጥልቅ ናት፤ በጥልቀትዋ ልክ መጥለቅና ከሁሉ በላይ መምጠቅን መታደል ቀላል አይደለም፡፡ ቀላል አይደለም ሳይሆን ከባድ ነው፡፡ ክብደቱ የሚሰማው ደግሞ ልብ ላይ ነው፡፡
መጥለቅና መምጠቅ የተለያዩ የሚመስሉ ነገር ግን ተመሳስሎን የታደሉ ቃላት (ወይም ሀሳቦች) ናቸው፡፡
ህይወት ጥልቅ ናት ብለናል፡፡ በህይወት ጥልቀት ልክ መጥለቅ ለሰው የሚቻል አይመስልም። የህይወት ጥልቀትዋና ርቀትዋ ሩቅ ነው፡፡ ወደ ህይወት ለመጥለቅ፣ በጥልቀት ተመልካችና አጥልቆና አርቆ አሳቢ መሆን ያስፈልጋል፡፡ ውጫዊ ገፅታን ለማሳመር ቀለም መቀባባት እና የላይ የላይ ኑሮ መኖር ወይም የለብለብ ዕውቀት ባለቤት መሆን ህይወት ላይ አያነግስም፡፡ ህይወት ላይ ለመንገስ ህይወትን በጥልቀትና በርቀት መገንዘብ የተገባ ነው።
እርግጥ ነው ይህን ሳያደርጉ የሆነ ደረጃ ላይ ደርሰው ወይም ስኬታማ መስለው የሚታዩ ሰዎች አሉ፡፡ ነገር ግን የአጭር ርቀት ተጓዦች እንጂ ከህይወት ጋር በማይሎች የሚጓዙ አይደሉም፡፡ ከጥቂት ርቀት ጉዞ በኋላ ዘሎ ወራጆች ናቸው፡፡
ህይወት ጥልቅና ውስብስብ የሆነች፤ እንደ ዕጢ የጠጠረች፤ በተፈጥሮ ንጥረ ነገሮች የተሞላች ግዙፍ ክስተት ናት፡፡ ኑሮ አድካሚና ለቀቢፀ-ተስፋ የሚድር፣ በቀላሉ ግን የማይሰበር ወይም የማይሞነጫጨር አለት ነው፡፡
የህይወትን የመምጠቅ ዓይነት ወይም የምጥቀት ደረጃ ለመገንዘብ ምጡቅ (ጂኒየስ) መሆን ሳያስፈልግ አይቀርም፡፡ ህይወት እንዲሁ ዝም ብላ መለስ ቀለስ የምትል፤ እንዲሁ ዝም ብላ የምትንጎራደድ ባልቴት አይደለችም፡፡ በርካታ ምርጫዎችን ከፊት ለፊታችን ታቀርብልናለች፡፡ የተሻለና የሚስማማኝ ነው የሚለውን መምረጥ የባለቤቱ ኃላፊነት ነው፡፡
ዓለም በተቃርኖ የተሞላች ናት፡፡ እያንዳንዱ ማንነት ወይም ክዋኔ አቻው የሆነ ሌላ ማንነት ወይም ክዋኔ አለው፡፡ ለወንድ ሴት፣ ለፀሐይ ዝናብ፣ ለመዓልት ሌሊት፣ ለብርሀን ጨለማ፣ ለህይወት ሞት፣ ለቅጥነት ውፍረት፣ ለርዝመት እጥረት፣ ለሀዘን ደስታ፣ ለለቅሶ ሳቅ … ወዘተ ….
ኑሮ ትግል ነው፡፡ እንደ በላይ ዘለቀ የበረታ፤ እንደ ማህተመ ጋንዲ ሰፊ ልቦና የታደለ፤ እንደ አብርሀም ሊንከን የፀና፤ እንደ ማርቲን ሉተር ኪንግ “በቃን!” ለማለት የደፈረ፤ እንደ ሶቅራጠስ በጥልቀት ያሰበ የሚረታው!
ያለበለዚያስ?!
ያለበዚያማ የሚሆነው ግልፅ ነው፡፡ ምርጫው ሁለት ነው፡፡ መርታት ወይም መረታት፡፡ መርታቱ ካልሰመረልን መርታት ዕጣ ፈንታችን ይሆናል፡፡ …
እውነት ነው፤ የኑሮ ጫና ከባድ ነው፡፡ እንደ ቀምበር ትከሻ የሚቆረቁር፤ እንደ ገጀራ አንገት የሚቀላ፤ እንደ ታቦት ስጋነ የሚያኮሰምን፤ እንደ ጅቡቲ በወበቅ የሚያፍን፤ እንደ ራስ ዳሽን ተራራ በቅዝቃዜ የሚያኮማትር ወዘተ …
የኑሮ ጫና ክብደት በቀላል ቃላት የሚገለፅ አይደለም፡፡ ጫናውን አጉልቶ አግዝፎ ለማሳየት የቃላት ኃይል ደካማ ነው፡፡
ለማንኛውም ህይወት እንዲህና እንዲያ ናት፡፡
* *  *
የሰው ልጅ ሸክላ ነው፡፡ በቀላሉ የሚሰነጠቅና በቀላሉ የሚሰበር! …
የየሰው ልጅ ሸክላ መሆኑን መረዳትና ለማስረዳት መሞከር ከንቱነትን መስበክ አይደለም። መሬት ላይ ያለውንና ስር የያዘውን እውነት ከመገንዘብ የሚመነጭ ራሱን የቻለ አንድ እውነት ነው፡፡ ሰው ሸክላ ነው ስል ተሰባሪ ነው ለማለት ብቻ አይደለም። ተሰባሪነቱ እንዳለ ሆኖ ከተሰበረ በኋላም በሌላ መልኩ ይሁን እንጂ ህልውናው መቀጠሉን ለመጥቀስ ጭምር ነው፡፡
በዕውቀቱ ስዩም እንዳለው ነው፡-
“ጋን ከጀርባ ወድቆ፣ ገል ሆኖ ቀጠለ
ከመሰበር ወድያም ሌላ ህላዌ አለ፡፡”
…ለመልማትም ለመጥፋትም መንገዱ ክፍት ነው፡፡ ማዕከላዊው ነገር ሰው ነው፡፡ ትልቁ ቁም ነገር ሰው መሆን ነው፡፡ ሰው ነን ካልን በኋላ ማንዴላን መሆንም ሆነ ሂትለርን መሆን የምርጫችን ጉዳይ ነው፡፡ ፈጣሪ ሰው አድርጎ ፈጥሮናል፡፡ ፈጥሮ ግን አልጨረሰንም፡፡ ትንሽ ዕድልና መጠነኛ ድርሻ ለ‘ኛ ትቷል፡፡ ሰው አርጎ ከፈጠረን ወዲያ ሰናይ ወይም እኩይ የሚባለውን ማንነት ለመጎናፀፍ ምርጫው ያለው በእጃችን ነው፡፡ ማንዴላንም ሆነ ሂትለርን ሰው አድርጎ የፈጠረው ፈጣሪ ‘ራሱ ነው፡፡ ማንዴላን ማንዴላ፣ ሂትለርን ሂትለር ያደረገው ሰብዕና የተፈጠረው ግን በ ‘ራሳቸው (በማንዴላና በሂትለር) ነው፡፡
ሁለቱም የ‘ራሳቸውን የተለያየ መንገድ ተከትለዋል፡፡ ማንዴላ ሰናይ፤ ሂትለር እኩይ!...
ህይወት ፈተና ናት፡፡ ደካማውና ጠንካራው በወንፊት የሚጠለልባት!... የብርቱው ብርታትም ሆነ የለፈስፋሳ ሰው ደካማነት በሰፌድ የሚበጠርባት!..
ህይወት ፈተና ናት፡፡ ህይወት ጦር ሜዳ ናት፡፡ ህይወት ፈተናና ጦር ሜዳ በመሆንዋ ምክንያት ብቻ ሁለት አማራጭ እንደ ጅግራ ከፊታችን ይገተራል፡፡ ተኝቶ ማልቀስ ወይም በርትቶ መታኮስ!
ውጣ ውረድ ያዘለው፤ ወድቆ መነሳት ያጣመነው ማንነት ላይ እንደ በቆሎ የተዘራን፤ እንደ ዛፍ የበቀልን፤ እንደ ፅጌረዳ ያበብን ሰዎች ነን፡፡ (ፅጌረዳ ስል ከአበባው ጋር እሾህም መኖሩን ጠቆም አድርጎ ማለፍ መልካም ነው!)…
ትግል የህይወታችን አንዱ ክፍል ነው፡፡ በአካባቢያችን ከሚገኝ ደንቃራ ጋርም ሆነ ከ‘ራስ ጋር ሳይታገሉ ውሎ ማደር፤ አንግቶ ማምሸት፤ አምሽቶም ማንጋት፤ የሚቻል አይደለም፡፡ ደደቢት በረሀ ባንገባም፤ አሲምባ ተራራ ላይ ዳስ ባንጥልም፤ ሁላችንም ታጋዮች ነን፡፡ በህይወት ናቅፋ፣ በኑሮ ሳህል ላይ የተሰማራን ተራ ዜጎች ነን፡፡
“ተራ!” አልኩ?! … ተራ ምንድን ነው?
እውነት ለመናገር “ተራ” የሚባል ሰው የለም፡፡ ዜግነትም በተራነት የሚገለፅ ነገር አይደለም፡፡
ከፍታና ዝቅታ በህይወት ውስጥ የሚፈራረቅ ነገር ስለሆነ፣ ባንዱ ረክቶና ሰክኖ ለሁሌው የሚዘልቅ፤ በአንድ ቦታ ተረጋግጦ ስር ሰዶ የሚገኝ ፍጡር፤ ከፍጡርም ሰው አይገኝም፡፡
ወርቅ በእሳት እንደሚፈተነው፤ ሰው በመከራ ይፈተናል፡፡ ፈተና የሚጥላቸው ሰዎች እንዳሉ ሁሉ፤ በፈተና የሚሰሩ፣ በፈተና የሚፈጠሩ ሰዎችም አሉ፡፡ ስንዴ ፈካ፣ ፀዳ የሚለው ከተፈተገ በኋላ እንደሆነው ሁሉ፤ ከፈተናው በፊት ምንም የሆኑ ከፈተናው በኋላ ግን እንደ አዲስ፣ አዲስ ሆነው የሚፈጠሩ ሰዎች አሉ፡፡
መሰናክል ብልሀት ለመፍጠር አዕምሮአችንን እንድናሰራው ያደርገናል፡፡ የሰው አዕምሮ ደግሞ ረቂቅና መጢቅ አይደል?! ከደንቃራው ለማለፍ በምናደርገው መፍጨርጨር ብርታትን እንጎናፀፋለን፡፡ መሰናክልን እናሰናክላለን፡፡
በፈተና የተገነባ ሰውነት በቀላሉ አይዝልም። በፈተና ያደገና የጎለመሰ ተክለ-ሰብዕና በቀላሉ አይዘምም፡፡ በፈተና የታሸ ልብ በቀላሉ ሊወድቅ ወይም ሊመታና ሊረታ አይችልም፡፡
ህይወት የትግል መድረክ ናት፤ ተኝቶ ያለቀሰ ሳይሆን በርትቶ የተታኮሰ የሚነግስባትና ዘውድ የሚጭንባት ልዕልት!... ችግርን በመሸሽ ሳይሆን ፊት ለፊት ተጋፍጦ በማሸነፍ የማይነቃነቅ፣ ፅኑና ብርቱ ማንነትን ልንገነባ እንችላለን፡፡ ይገባልም፡፡
በርትተን ከተታኮስን ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገንም የግላችን ማድረግ እንችላለን፡፡
ዛሬ ብቻ ሳይሆን ነገም የኛ ነው፡፡
በሮበርት ስቹለር ስንኞች ልሰናበት፡፡
“The sun is shining, the sky is blue!
There is a new day dawning for me and you.
With every dawning of the sun
New possibilities have just begun
With every breaking of the morn
Fresh opportunities are newly born.”

Saturday, 02 May 2015 11:48

የፀሐፍት ጥግ

አዕምሮዬን ባዶ ለማድረግ ካልፃፍኩኝ አብዳለሁ፡፡
ሎርድ ባይረን
መፅሃፍ በውስጣችን እንደ አለት ረግቶ ለተጋገረው ባህር እንደመጥረቢያ ማገልገል አለበት፡፡
ፍራንዝ ካፍካ
ከምፅፈው ውስጥ ግማሹ ትርኪምርኪ ነው፡፡ ካልፃፍኩት ግን ጭንቅላቴ ውስጥ ይበሰብሳል፡፡
ጃሮድ ኪንትዝ
ብዙ ሰዎች ስለ መፃፍ ያወራሉ፡፡ ምስጢሩ ግን ማውራት ሳይሆን መፃፍ ነው
ጃኪ ኮሊንስ
በህይወት ውስጥ ሁሉም ነገር ለመፃፍ ተራ የሚጠብቅ ታሪክ ነው፡፡
ሜ.ጂ. ማርሽ
ፕሮፌሽናል ፀሐፊ፤ መፃፍ ያላቆመ አማተር ነው፡፡
ሪቻርድ ባች
 እንደምንፈልገው አን    ፅፍም፤ እንደምንችለው እንጂ፡፡
ሶመርሴት ሟም
መፅሐፉ አፍቃሪዎች ፈፅሞ ለብቻቸው ወደ መኝታቸው አይሄዱም፡፡
ያልታወቀ ደራሲ
አሜሪካኖች ወፈር ያሉ መፃህፍትና ቀጠን ያሉ ሴቶች ይወዳሉ፡፡
ራስል ቤከር

Saturday, 02 May 2015 11:46

የፍቅር ጥግ

ሚስት በባሏ ላይ ከመንግስት የበለጠ ሥልጣን አላት፡፡
ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን
ሰው ሚስትህን ሲሰርቅብህ እንዲወስዳት ከመፍቀድ የበለጠ በቀል የለም፡፡
ሳቻ ጉይትሪ
ሚስትህን ፈፅሞ አትምታት - በአበባም ቢሆን፡፡
የሂንዱ አባባል
ሚስቴ አለቀሰች፡፡ ዳኛው በእኔ “ቼክ” እንባዋን አበሱላት፡፡
ቶሚ ማንቪሌ
ወንደላጤዎች ከባለትዳር ወንዶች የበለጠ ስለ ሴቶች ያውቃሉ፡፡ እንዲያ ባይሆን ኖሮ እነሱም ያገቡ ነበር፡፡
ኤች.ኤል.ሜንኬን
ባሎች እንደ እሳት ናቸው፤ ካልቆሰቆሷቸው ይጠፋሉ፡፡
Zsa Zsa Gaber
ሚስት የሌለው ወንድ፣ አበባ የሌለው የአበባ ማስቀመጫ ማለት ነው፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
ማንኛውም ያገባ ወንድ ስህተቶቹን መርሳት ይኖርበታል፡፡ ሁለት ሰዎች ተመሳሳይ ነገር ማስታወሳቸው ጥቅም የለውም፡፡
ዱአኔ ዴዌል
ስለ ፍቅርና ስለ ትዳር ማንበብ ከፈለግህ ሁለት የተለያዩ መፃህፍት መግዛት አለብህ፡፡
አላን ኪንግ
ከልብ የወጣ ልብ ይነካል፡፡
ያልታወቀ ደራሲ
ፍቅር፤ ምንም ነገር የመጋፈጥ ኃይል ይሰጠኛል፡፡
አሊሰን አስርንዎልፍ

Saturday, 02 May 2015 11:45

የግጥም ጥግ

አ ቤት!
ኤሎሄ  ቅኝቱ  ጠፍቶኝ
የነገለ በገና አቅፌ
በጉልበቴ ተቀምጬ፤
በፍታቴ እስክስታ ብወርድ
እዝል አራራዩን ባላዝነው
ቅኔ ማህሌቱን  ገልብጬ፤
የሀሩር በረሀ አበባው
ዋግ እንዳጠናፈረው እሸት
እማሳው መሀል ብገተር፤
አለቅጥ ጠግበው በሚያናፉ
ዝሆኖች መሀል እንደ ድርጭት
አቅሌን ስቼ እምውተረተር፤
ፈተና ያቆመኝ ሀውልት
አልሟሟም ያልኩ ቢመስል
ባያነባ ሙጭሙጭ አይኔ፤
እምነቴ ቢያጠጥረኝ ነው
ምናቤ የረገጠው እርካብ
ቢያዝለኝ ጣራ ውጥኔ፡፡
እንደ ምኞታችንማ ጉስቁልና
እንደ ሚዛናችን መራቆት
እንደ ነፍሳችን ግልቢያ መጃጀት፤
መርዷችን ባይሰማ እንጂ
ወገን ከሌለንማ ቆየን
እንደ ሩቁ ተስፋችን መዘግየት፡፡
አቤት!    አቤት!!    አቤት!!!
/ፈለቀ አበበ፤ 1989 ዓ.ም -
ተረት ሰፈር/

ሠማያዊ ፓርቲ የአይኤስን የሽብር ድርጊት ለማውገዝ መንግስት የጠራውን ሠልፍ አውኳል በሚል በመንግስት እየተወነጀለ ሲሆን ፓርቲው በበኩሉ፤ በተፈጠረው ረብሻ እጄ የለበትም፤ መንግስት ያለ አግባብ የስም ማጥፋትና ውንጀላ ዘመቻ ከፍቶብኛል ሲል አማሯል፡፡ መንግስትና የመንግስት ሚዲያዎችን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት አካላት በፓርቲው ላይ የሚሠነዝሩትን ውንጀላ ካላቆሙም ፓርቲው ጉዳዩን ወደ ፍ/ቤት ሊወስደው እንደሚችል አስታውቋል፡፡ መንግስት ግን ሠማያዊ ፓርቲ ሁከቱን ስለመፍጠሩ በቂ ማስረጃ አለኝ ብሏል፡፡ በሌላ በኩል፤ ሠማያዊ ፓርቲ ሠሞኑን በቅስቀሳ ፖስተር አለጣጠፍ ጉዳይ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማስጠንቀቂያ ደርሶታል፡፡ በእነዚህ አወዛጋቢ ጉዳዮች ዙሪያ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬን የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ አነጋግሯቸዋል፡፡


ሠማያዊ ፓርቲ መንግስትንና የመንግስት ሚዲያዎችን እከሣለሁ ሲል ምን ማለቱ ነው?
መንግስት የፓርቲው ተግባር ያልሆነን ጉዳይ አንስቶ “በረቡዕ እለቱ ሠላማዊ ሠልፍ ላይ ሁከት የፈጠረው ሠማያዊ ፓርቲ ነው” በሚል በሃሰት መወንጀሉና በፍርድ ቤት ሣይረጋገጥ ጥፋተኛ አድርጐ በመፈረጁ፤ ፌደራል ፖሊስ “7 የሰማያዊ አመራሮችን አስሬያለሁ” ያለውም ሃሰት ነው፤ የታሠሩት 6 ናቸው፤ እነሱም ከሠልፉ በፊት ነበር የታሠሩት፤ አንደኛው የዚያኑ ቀን ነው የተፈቱት፡፡
ኢቢሲንም እንከሣለን ብላችኋል፤ ምክንያቱ ምንድን ነው?
የውሸት ዘገባ በማሠራጨቱ ነው፡፡ “አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች” እያለ በምርመራ ያልተያዘን ጉዳይ አንስቶ ሠማያዊ ነው ሁከቱን ያቀነባበረው የሚሉ መሠረት የሌላቸው ስም አጥፊ ዘገባዎችን ሲሰራ ከርሟል፡፡ እነዚህ ሃሰተኛና የአንድ ወገን ዘገባዎች ደግሞ በምርጫው እንቅስቃሴ ላይ እክል እየፈጠረብን ነው፡፡ ይህ የጣቢያው ድርጊት የማይቆም ከሆነ ወደ ክስ መሄዳችን አይቀርም፡፡
“ፓርቲው የህብረተሰቡን መሪር ሃዘን ተጠቅሞ የራሱን አጀንዳ ለማስፈፀም ሲተጋ ነበር” ነው የተባለውና ከተጐጂ ቤተሰቦችና ከህብረተሰቡ የገጠማችሁ  ተቃውሞ አለ…
ኧረ ምንም አይነት ተቃውሞ አላጋጠመንም፡፡ እኛ እንደ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖምና ከንቲባ ድሪባ ኩማ ሀዘንተኞችን አጽናንተናል ብለን ለሚዲያ ፍጆታ ባናውለውም፣ አመራሮቻችን ሃዘንተኞቹን  በየቤታቸው በመገኘት አጽናንተዋል፡፡
እንደውም በአጋጣሚ ከሠማያዊ ፓርቲ የመጣን አልመሠላቸውም ነበርና ሠማያዊ ፓርቲዎች እንዴት ነው ያላፅናኑን የሚል ሃሜት እዚያው ቁጭ ብለን ስንሰማ ነበር፡፡ እናም የሟቾቹ ቤተሰቦች በጥሩ መንፈስ ነበር የተቀበሉን፡፡ አሁንም ፈጣሪ መጽናናቱን ይስጣቸው እንላለን፡፡
በሠልፉ ላይ የፓርቲው አመራሮችም ሆኑ አባላትና ደጋፊዎች የነበራቸው ተሣትፎ በምን መልኩ ነበር?
መንግስት ሠልፉን ቢጠራም እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ አይኤስ የፈፀመውን አሠቃቂ ግድያ ለማውገዝ አባሎቻችንና ደጋፊዎቻችን እንዲገኙ በዋዜማው ጥሪ አስተላልፈናል፡፡ ሠልፉን በሚገባ ደግፈን ነው የወጣነው፡፡
በሠልፉ ላይ መንግስትን ነው ወይስ አይኤስን ነው ለመቃወም የወጣችሁት? አጀንዳችሁ ምን ነበር?
በመግለጫችን ላይ ግልጽ አድርገነው ነበር፡፡ አይኤስ በወገኖቻችን ላይ የፈፀመውን አሠቃቂ ግድያ እንቃወም የሚል ነው፡፡ ሃዘናችሁን ለመግለጽና ድርጊቱን ለማውገዝ አደባባይ ውጡ ነው ያልነው፡፡ ከዚያ በተረፈ መንግስትን መቃወም የተጀመረው ረቡዕ ብቻ አይደለም፤ በዚህ ጉዳይ ቀደም ብሎ ተቃውሞ ሲገጥመው ነበር፡፡
ማክሰኞ እለት ሰው ራሱ ወጥቶ ነበር የተቃወመው፡፡ ማክሰኞ በራሱ የወጣው ህዝብ እኮ ነው ረቡዕ እለት በድጋሚ ተቃውሞውን ያሰማው፡፡ እኔ እንደሚገባኝ ተቃውሞ የተፈጠረው ማንም ስላደራጀው ሣይሆን መንግስት ከዚያ በፊት ይሠጣቸው በነበሩ መግለጫዎች የተነሳ ነው፡፡
“ኢትዮጵያዊነታቸውን እናጣራ፣ ህገወጥ ስደተኞች ናቸው” የሚሉት መግለጫዎች ሰው ያስቆጣል፡፡ የሰውን የቁጣ ስሜት የአንድ የፖለቲካ ፓርቲ አጀንዳ አድርጐ መግለጽ ተገቢ አይደለም
መንግስት ተቃውሞውን ሠማያዊ ፓርቲ ስለማቀነባበሩ ማስረጃ አለኝ እያለ ነው …
ይሄ አዲስ አይደለም፡፡ በኢህአዴግ ቤት የተለመደ ነው፡፡ የውሸት ማስረጃ ማቀነባበር የተለመደ ነው፡፡ የታሠሩት አምስት አባሎቻችን ሌሊት እንደሚመረመሩና በምርመራው ወቅትም ፓርቲውን እንዲለቁ ግፊት እንደሚደረግባቸው ሰምተናል፡፡ ለምሣሌ አመራራችን ወይንሸት ሞላ የተያዘችው ገና ሰልፉ ሣይጀመር ነው፡፡ እሷ ላይ ታዲያ ምን አደረገች ተብሎ ነው ማስረጃ የሚቀርብባት፡፡ በእለቱ ምን ያደረገችው ነገር አለ? ማስረጃ ብለው የሚያቀርቡት የውሸት ነገር በኢህአዴግ ቤት በሽበሽ ነው፡፡ የኛን ነገር ግን የሚፈርደው ታሪክ ብቻ ነው፡፡
በዚህ ሰሞን ደግሞ በክልክል ቦታዎች ላይ የቅስቀሳ ፖስተር ፓርቲው ለጥፏል በሚል ከምርጫ ቦርድ ማስጠንቀቂያ ደርሶታል፤ በእናንተ በኩል በዚህ ጉዳይ ላይ ያለው መረጃ ምንድነው?
ይሄ  ፓርቲው በጣም የተቸገረበት ጉዳይ ሆኗል፡፡ ለምርጫ ቦርድም ረቡዕ እለት ከኛ ቁጥጥር ውጪ እንደሆነ በመግለጽ ደብዳቤ ፅፈናል፤ በግለሰብ ደረጃ ሣይሆን በተቀነባበረ ደረጃ ይሄን ነገር የሚያደርግ አካል እንዳለም ተረድተናል፡፡
ስለዚህ ይሄን ምርጫ ቦርድ ተገንዝቦ ጉዳዩ ከአቅማችን በላይ በመሆኑ ክትትል እንዲያደርግልን ጠይቀናል፤ ነገር ግን ለደብዳቤው ትኩረት ሣይሰጡ መልሰው እኛኑ ነው እየከሰሱ ያሉት፡፡ በእኛ በኩል የተሠሩ ስህተቶችን እየፈለግን እያረምንም ነው፡፡ በጋራ መኖሪያ ቤት አካባቢ፣ በፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች አካባቢ ሣይታወቅ የተሠሩ ስህተቶች ሲያጋጥሙንም ፈጥነን እንዲነሣ እያደረግን ነው፡፡
ፖስተሮቻችን እየተቀደዱ ከመጣላቸውም በላይ በአንዳንድ ቦታዎች የተቀደዱት ከመሬት ተነስተው የተከለከሉ ቦታዎች ላይ ሆን ተብለው ተለጥፈው ተመልክተናል፡፡ እኛ በጭራሽ ያልተንቀሳቀስንባቸው አንዳንድ ቦታዎች ላይ ለምሳሌ በመስጊድ ላይ ተለጥፎ አይተናል፡፡ በአካባቢው ግን የኛ የቅስቀሳ ቡድኖች ድርሽም አላሉም ነበር፡፡
እነዚህን ችግሮች እንግዲህ ለቦርዱ አመልክተናል፡፡ ቦርዱ እርምጃ የማይወስድ ከሆነ ህብረተሰቡ እንዲከታተልልን ጥሪ እናቀርባለን፡፡
በእናንተ በኩል የደረሳችሁበት ምንድነው?
ሆን ብለው የፓርቲውን ስብዕና ለማጠልሸት የሚንቀሳቀሱ አካላት እንዳሉ ተረድተናል፡፡ ለዚህም ነው ለቦርዱ ከአቅማችን በላይ ሆኗል ብለን ደብዳቤ የፃፍነው፡፡ ቦርዱ ከኛ ጐን በመቆም ለህዝቡም ይሄን ነገር እንዲያሳውቅልን እንፈልጋለን፡፡
እስካሁን ያለው የቅስቀሳ ሂደታችሁ ምን ይመስላል?
በአራቱም የሃገሪቱ ጫፎች የቅስቀሳ ቡድን አሠማርተናል፡፡ ነገር ግን በአንዳንድ ቦታዎች ተግዳሮት እየገጠመን ነው፡፡ ለምሣሌ በአዋሣ አትቀሰቅሱም በሚል ከፖሊስ ተቃውሞ ገጥሞን ነበር፤ ነገር ግን አባሎቻችን ጉዳዩን አለዝበው በማየታቸው በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም ቢሆን ቅስቀሳ ማድረግ ተችሏል፡፡ ግን የምርጫ ኮሚቴ አባላችን ሳምሶን ግዛው “በሞባይል ፖሊስ ፎቶ አንስተሃል” በሚል ፍ/ቤት ቀርቦ የ7 ቀን ቀጠሮ ተጠይቆበታል፡፡ እንግዲህ ፎቶ ማንሣትም ወንጀል ሆኖ፣ ዋስትናም አስከልክሎ ለእስር ዳርጓል ማለት ነው፡፡
ሌላው ምስራቅ ጐጃም እና ምዕራብ ጐጃም ላይ አስተባባሪዎቻችን ሣሙኤል አወቀ እና አዲሱ ጌታነህ ተደብድበውብናል፡፡ ለከፍተኛ ጉዳትም ተዳርገው ህክምና እየተከታተሉ ነው፡፡ ከዚያ በተረፈ የምርጫ ቅስቀሳ ፖስተሮች መቀደድ አንዱ ያስመረረን ጉዳይ ነው፡