Administrator

Administrator

ያስደነግጣል። ከ340ሺ እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር... ከዚያም የሚያልፍ ማለት ነው። ለንግድ፣ “አይን የሆኑ ቦታዎች”

ላይ የቤት ኪራይ አይቀመስም - ከሁሉም በላይ ደግሞ በሆንክኮንግ፣ በኒውዮርክና በፓሪስ። በ64 ሃብታም አገራት ላይ

ጥናት ያካሄደው ኩሽማን ኤንድ ዌክፊልድ እንደሚለው፤ በሆንክኮንግ ሃብታሞች የሚያዘወትሩት የገበያ አካባቢ ላይ፣

ሶስት በአራት ሜትር የሆነች አንዲት ሱቅ በወር 32ሺ ዶላር ትከራያለች (ከ600ሺ ብር በላይ ማለት ነው)። በሁለተኛ

ደረጃ የተጠቀሰው ውድ ኪራይ የሚገኘው፣ በኒውዮርክ ፊቭዝ አቨኑ የሚባለው አካባቢ ነው። ተመሳሳይ አነስተኛ ክፍል

በወር 26ሺ ዶላር ኪራይ ያስከፍላል። ቀጥሎ የሚመጣው ከወደ ፓሪስ ነው - በወር 17ሺ ዶላር የሚከፈልበት።

ተራ ሰዎች የታጠቁትን መሣሪያ ለማነፃፀር እንጂ፣ ሁለቱ መንግስታት የታጠቁትን  ለመቁጠር አይደለም። በአሜሪካ

መሣሪያ የታጠቀ ቤተሰብ ነው የሚበዛው - 58 በመቶ ያህል ቤተሰቦች የመሣሪያ ባለቤት ናቸው። ብዙዎቹም፣ ሦስት እና

አራት የመሣሪያ አይነቶች አሏቸው። የተለመደ ባሕል ወይም እምነት ብቻ አይደለም። የመሣሪያ ባለቤትነት ትልቅ ዋጋ

የተሰጠው መሰረታዊ መብት ከመሆኑ የተነሳ፤ ከ230 ዓመት በፊት የአገሪቱ ሕገመንግስት ሲፀድቅ በማይደፈሩ መብቶች

ዝርዝር ውስጥ እንዲገባ ተደርጓል። ዛሬ፣ በሲቪል አሜሪካዊያን እጅ ውስጥ ያለ የጦር መሣሪያ፣ ከ300 ሚሊዮን በላይ

ነው።
በቻይና፣ የጦር መሣሪያ ባለቤትነት፣ የሚያስቀጣ ወንጀል እንጂ የሚከበር መብት አይደለም። የጦር መሳሪያ ፈልጎ

ማግኘት ያስቸግራል። በሌላው አካባቢ ይቅርና፣ የተቃውሞና የአመፅ አዝማሚያ ይታይበታል በሚባለው ጊዝሆ በተሰኘ

የቻይና ክልልም የጦር መሳሪያ ብርቅ ነው።
በቅርቡ በክልሉ በተካሄደ ሰፊ አሰሳ ግን ብዙ ሕገወጥ መሣሪያ ተገኝቶ ተወርሷል - 12ሺ ሕገወጥ ቢላዋ።

ለራስ፣ ለቤተሰብ፣ ለማህበረሰብ፣ ለአገር፣…. የሚጠቅም ራዕይና ሕልም ይዘው ወደ ት/ቤት ወደ ግል ጉዳይ፣ ወደ ሥራ፣

ወደቤት… ሲሄዱ፣ የመኪና አደጋ ካሰቡበት ሳይደርሱ መንገድ ላይ ያስቀራቸውን ዜጎች ቤቱ ይቁጠራቸው፡፡ በኮልፌ

የደረሰውን የመኪና አደጋ፣ አባይ በረሃ የተቃጠለውን ስካይ ባስ፣ በቅርቡ እንኳ በሰሜን ማዘጋጃ አካባቢ … የደረሱትን

የመኪና አደጋዎች ለአብነት መጥቀስ ይቻላል፡፡
በየዕለቱ፣ በራዲዮ በሚቀርበው የትራፊክ አደጋ፣ የሞት፣ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመት… ሲሰማ

“አሽከርካሪዎች ጆሮ የላቸውም ወይ?” ያሰኛል፡፡ ይህ ሁኔታ ሁነኛ መፍትሔ ካልተፈለገለትና በዚሁ የሚቀጥል ሆነ ከ16

ዓመት በኋላ (በ2030 እ.ኤ.አ)፣ የመኪና አደጋ በመላው ዓለም ከመጀመሪያዎቹ 5 የሞት መንስኤዎች አንዱ እንደሚሆን

የዓለም ጤና ድርጅት ተንብዮአል፡፡
ግምቱ ያለምክንያት አይደለም፡፡ በዓለም ላይ በየዓመቱ በመንገድ ላይ (በመኪና) አደጋ 1.24 ሰዎች እንደሚሞቱና 50

ሚሊዮን ያህል እንደሚቆስሉ የድርጅቱ መረጃ ያመለክታል፡፡ ከሟቾቹ ግማሽ ያህሉ፣ እግረኞች፣ ቢስክሌትና የህዝብ

ትራንስፖርት ተጠቃሚ መንገደኞች ናቸው፡፡ ከመቶ ሰዎች 90ዎቹ የሚሞቱት አነስተኛና መካከለኛ ገቢ ባላቸው አገሮች

ሲሆን ከመቶ የመኪና አደጋዎች 62ቱ የሚከሰቱት አገራችንን ጨምሮ በ10 አገሮች ብቻ እንደሆነ የጤና ድርጅቱ ሪፖርት

አመልክቷል፡
ሌላው የሚሊዮኖች ሞት ምክንያት የሥራ ቦታ አደጋና በሽታ ነው፡፡ በሥራ ቦታ አደጋና በሽታ በየ15 ሰከንዱ አንድ

ሰራተኛ ይሞታል፡፡ 160 ሰራተኞች ደግሞ የስራ ቦታ አደጋ ሰለባ ይሆናሉ፡፡ በደሌ (ሄኒከን) ቢራ የዘንድሮውን የዓለም

የደህንነትና የጤና ቀን ባሳለፍነው ሳምንት ባከበረበት ወቅት ለሰራተኞቹ ያሰራጨው በራሪ ወረቀት፣ በዓለም ላይ በየቀኑ

6,300፣ በዓመት 2.3 ሚሊዮን ሰዎች በሥራ ቦታ በሚፈጠር አደጋ እንደሚሞቱና በየዓመቱ 317ሺ የሥራ ቦታ አደጋዎች

እንደሚያጋጥሙ አመልክቷል፡፡
በዕለቱ፣ በደሌ ቢራ የመኪናና የሥራ ላይ አደጋዎች የሚያደርሱትን ጉዳትና መከላከያውን በልዩ ልዩ ዘዴዎች፣

ለከተማዋና ለአካባቢዋ ነዋሪዎች፣ እንዲሁም ለፋብሪካው ሰራተኞች አስተምሯል፡፡ በከተማዋ አደባባይ እግረኞች

ከትራፊክ አደጋ ለመጠበቅ ግራቸውን ይዘው እንዲጓዙ፣ አሽከርካሪዎችም የትራፊክ ሕግ አክብረው እንዲያሽከረክሩ፣

ጉዳዩ በሚመለከታቸው ሰዎች ትምህርት ከመሰጠቱም በላይ የነዋሪውን ግንዛቤ ከፍ ለማድረግ በሁለቱም ፆታ በጎዳና ላይ

ሩጫ ላሸነፉ ተወዳዳሪዎች ሽልማት ሰጥቷል፡፡  በድርጅቱ ግቢ ውስጥ የሥራ ላይ ደህንነትን አስመልክቶ ለሰራተኞች

የተለያዩ የአደጋ ዓይነቶች፣ መንስኤና መከላከያ በተለያዩ ዘዴዎች ከማስተማሩም በላይ በተደረጉ ውድድሮች ላሸነፉ

ሰራተኞች ሽልማት ሰጥቷል፡፡
በሞባይል እያወሩ መኪና ማሽከርከር፣ ሲዲ ወይም ራዲዮ መቀየር፣ መኪና ውስጥ መብላት፣ ወደ ውጪ ሌላ ነገር ማየት፣

ጠጥቶ ማሽከርከር፣ የተለያዩ አደንዛዥ ዕፆች መጠቀም፣ እያሽከረከሩ መዋብና አጎንብሶ ዕቃ ማንሳት፣ በፍጥነትና

በግዴለሽነት መንዳት፣ መጥፎ የአየር ፀባይና የተበላሸ መንገድ ዋነኞቹ የአደጋ መንስኤ ምክንያቶች መሆናቸው

ተገልጿል፡፡
በደሌ ቢራ የሥራ ቦታ ደህንነትን ለመጠበቅና አደጋን ለመከላከል ከሰራተኞቹ ውስጥ የሙያ ደህንነት ጀግና ለመምረጥ፣

የእሳት አደጋ መኪና ለመግዛትና ጥራት ያላቸው የአደጋ መከላከያ ቁሳቁስ ከውጭ ለማስመጣት ማቀዱ ታውቋል፡፡

አንድ የኦሮሞ ተረት እንዲህ ይላል፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ሰው ወደ ዘመቻ ይሄድ ኖሮ ቤተሰቡንና ቤት ንብረቱን ሁሉ ለጎረቤቱ አደራ ብሎ፤ ቀዬውን ተሰናብቶ ወደ ጦር ሜዳ ሄደ፡፡
ጦርነቱ ከሁለት ዓመት በላይ ፈጀ፡፡ ብዙ ሰው ከወዲህ ወገን ሞተ፡፡ ከጠላትም በኩል እንደዚሁ ስፍር ቁጥር የሌለው ሰው አለቀ፡፡ ይሄንን ሁሉ አልፎ ያ ዘማች ተርፎ ወደ መንደሩ ተመለሰ፡፡
ገና ወደ ቤቱ ሳይደርስ መንገድ ላይ ያገኘውን ሰው ሁሉ፤
“መንደራችን ሰላም ነው ወይ?” ብሎ ይጠይቃል፡፡
“ሰላም ነው፡፡ ምንም የደረሰ ነገር የለም” ይለዋል አንዱ፡፡
ሙሉ በሙሉ ለማመን ስለሚቸገር ሌላውን ሰው፤
“ጎበዝ፤ መንደራችን እንዴት ነው? ሰዉስ እንዴት ከረመ” ሲል ይጠይቃል፡፡ ሌላውም ሰውዬ፤
“ኧረ አማን ነው፡፡ ምንም የተፈጠረ ችግር የለም” ይለዋል፡፡
እንዲህ እየጠየቀ ሲጓዝ በመጨረሻ ያንን ቤተሰቡንና ቤት ንብረቱን አደራ የሰጠውን ጎረቤቱን አገኘው።
ተቃቅፈው ተሳሳሙ፡፡
“እንዴት ነህ?” አለ ዘማች፡፡
“ደህና!” አለ ጎረቤት፡፡
“ሁሉ አማን፣ ሁሉ ደህና?”
“ሁሉም አማን ነው፡፡ ሰላም ነው!”
“እርግጠኛ ነህ? ምንም ችግር አልገጠማችሁም?”
“ኧረ ምንም፡፡ ያ ያንተ ውሻ ብቻ ከመሞቱ በስተቀር ምንም የሆነ ነገር የለም”
“ውሻዬ እንዴት ሞተ?”
“አጥንት ሲግጥ አንቆት ሞተ”
“የምን አጥንት?”
“አንድ የታረደ በሬ ነበር የሱን አጥንት ሲበላ አንቆት ነው፡፡”
“በሬው ለምን ታረደ?”
“ለባለቤትህ አርባ”
ዘማች ኡኡታውን ለቀቀው፡፡ ጮኸ፡፡ ዕንባው ተንዠቀዠቀ፡፡ ጎረቤትዬው አባብሎ ቀና አደረገውና፤
“እቤት ስትደርስ ያደርስህ የለም ወይ? በቃ ዝም በል” አለውና መንገድ ይጀመራሉ፡፡
ከዚያም መቼም ባል የሚስቱን አሟሟት ማወቅ አለበትና፤
“ለመሆኑ ምን ሆና ሞተች?” አለው ፡፡
“በወሊድ ነው የሞተችው” አለ ጎረቤት፡፡
“በወሊድ?!” አለ ባል፣ በድንጋጤ፡፡
“አዎ በወሊድ ነው”
“ከማን አርግዛ?” አለ ባል፤ ዘመቻ የቆየው ሁለት ዓመት መሆኑን እያሰላሰለ፡፡
“ሰው ካንተ ነው ይለኛል፤ እኔ ግን እኔ አይደለሁም እላለሁ!” አለው፡፡
*       *       *
ዛሬ በሀገራችን፤ ትንሽ መገለቻዎች፣ የትልቁ ስዕል ምልክቶች ናቸው! ማናቸውንም የነገር አካሄድ ሥረ-መሰረቱን ደብቀን የምንጓዝበት ከሆነ፤ ውጤቱ አያምርም፡፡ እያንዳንዱ የተከማቸ ነገር ድንገት አንድ ጊዜ ለመፈንዳት ቅንጣት ሰከንድ ትበቃዋለች፡፡ የTipping Point (ፍንዳታዋ ነጥብ እንደማለት) ደራሲ ነገሩ እየደለበ ይሂድ እንጂ ለመፈረካከስ አንዲት አጋጣሚ ትበቃዋለች ይላል፡፡ ዕውነት ነው፡፡ ውስጥ ውስጡን የተጠራቀመ፣ የተነፋፋ ምሬት በየት እንደሚፈነዳ አይታወቅም፡፡ ምሬት ተጠራቅሞ ወደ አንድ ቦይ ሳይገባ በፊት ካልገደቡት፤ ውሎ አድሮ ለያዥ ለገራዥ የሚያስቸግር ሊሆን ይችላል፡፡
ብዥታና ዳፍንተኝነት አብዛኛውን ጊዜ የሚከሰተው፤ ህሊናዊው (subjective) ሁኔታ ሲዘገይና ዕሙናዊው ሁኔታ (objective) እጅግ ሲቀድም ነው፡፡ ካለንበት ሁኔታ ተነስተን ስናስበው፣ ይህ ክስተት የሚመጣው፤ ምሬቱ እጅግ ሲበረክትና መፍትሔው እጅግ ሲዘገይ ነው ማለት ነው፡፡
የአሜሪካው የሲቪል መብቶች ትግል መሪ “እምቢ ብሎ መነሣት፣ ያልተሰሙ ድምፆች ቋንቋ ነው” ይለናል፡፡ ይህን ልብ እንበል፡፡ ትምህርት የረጋ አካባቢ፣ የተቀደሰ መንፈስና ንፁህ ልቦና ይፈልጋል፡፡ ታዋቂው ሳይንቲስት አልበርት አንስታይን፤
“ለእኔ፣ በመርህ ደረጃ፤ ትምህርት፤ ከፍርሃት፣ ከጉልበት እና ከአርቴፊሻል ሥልጣን ጋር የሚሰራ ከሆነ የመጨረሻ አስከፊ ነገር ነው፡፡ ይህ ዓይነት አያያዝ ድምፅን ያኮስሳል፣ ስሜትን ያቀዝዛል፣ ቅንነትንና የተማሪዎችን ሙሉ ልብ (ልበ-ሙሉነት) ያመነምናል፡፡ በዚህ ሁኔታ የምናፈራውም፤ እጁን የሰጠና ተምበርካኪ ትውልድ ነው” ሲል ጠቅልሎ ያስቀምጠዋል፡፡
በክፍል የምንማረውን ያህል ከህይወትም እንማራለን፡፡ ከአካባቢም እንቀስማለን፡፡ ስለሆነም ዕድሜ ልካችንን ተማሪዎች ነን፡፡
ነገር እስኪባባስ፣ እስኪጎመዝዝና እስከሚመር ተብሎ ታይቶ፤ ወደ ፍንዳታ ደረጃ እስከሚደርስ ማየት፤ በኋላን በመካያው ሰበብና ምክን ፈጥሮ “የአብዬን እከክ ወደምዬ ልክክ፤ አያዋጣም፡፡
ሁሉም ተማሪ የሰከነ፣ የተቀነባበረ፣ የበሰለ መልክ መያዝ ይገባዋል፡፡ ሁሉን ነገር በጥሞና መመርመር የመማር ዋንኛው አንጓ ነው፡፡ ግራ ቀኙን ማየት ክፉ ደጉን መለየት የማንኛውም ጉዞ መሰረታዊ መነሻ ነው፡፡ ዊሊያም አስበር የተባለ ካናዳዊ ሐኪም ስሞት መቃብሬ ላይ እንዲፃፍ የምፈልገው፤ ከዚህ በታች ያለው ነው፡-
‹እዚህ ለመድረስ ነው እንደዚያ የተጣደፍነው?!›
ጆርጅ ደብሊዩ ቡሽ በማዕረግ ዲግሪ ለተሸለሙት የዬል ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ባደረጉት ንግግር፤ “የክብር ተመራቂ፤ ተሸላሚ እና የማዕረግ ተሸላሚ ለሆናችሁ ተማሪዎች እንኳን ለዚህ አበቃችሁ እላለሁ። በ‹ሲ›(ር) የተመረቃችሁም አይዟችሁ፤ እናንተም እንደኔ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ለመሆን ትችላላችሁ” ብለዋል፡፡
ለሁሉም ተማሪ አገሪቱ እኩል እድል ትሰጣለች ነው ቁም ነገሩ፡፡ እኛስ? ብሎ መጠየቅ እንግዲህ የእኛ ፋንታ ነው፡፡ በየትም አገር፣ በየትም ጊዜ፤ ለሁሉ በሽታ አንድ ዓይነት መድኃኒት የለም ‹ፓናሲያ› እንዱሉ፡፡ ለሁሉ ችግር አንድ ብቸኛ መፍትሄም የለም፡፡ ሁሉም መንገድ ወደ አንድና አንድ ሰፈር ብቻ አያደርስም። የጉዳዮቻችን አፈራረጅ እንደወቅቱና ሁኔታው ተጢኖ ሳይሆን፤ ሁሉም በተለመደው መንገድ መሆኑ አሳሳቢ፡፡ “ይሄማ በዚህ በዚህ ሰበብ የመጣ ነው”፣ “ይሄማ ከጀርባ ይሄ ይሄ ነገር ቢኖረው ነው፡፡ ይሄማ ከተለመዱት ሰዎች ውጪ አይሆንም” (“Round up the usual suspect” እንዲል፤ ቃለ-ፊልም)፤ እያልን ብዙ መንገድ ለመሄድ አይቻለንም፡፡ በለሆሳስ እናስብ፡፡ ዙሪያ-መለስ ዕሳቤ ይኑረን። አገርና ህዝብ በማይጎዳ ፍትሀዊ ጎዳና እንጓዝ፡፡ አለበለዚያ “ብትናገር ያምናውን፣ ብትፈትል አንድ ልቃቂት” የሚለው የትግሪኛ ተረት እፊታችን ይደቀናል፡፡

Saturday, 10 May 2014 12:13

የወቅቱ ጥቅስ

የፖለቲካ መፈክሩ፤ “የእኛ ተግባር መማር መማር መማር” የሚለው የሌኒን መርህ ነበር፡፡
አንዲት ልጅ የክፍል ፈተና እያለባት “ፎርፋ” የትም ስትዋልግ ትውላለች፡፡
አባት ይሄንን ጉድ ሰሙና አስጠሩዋት፡-
“አንቺ፤ ለምንድነው ከክፍል የቀረሺው? ሌላው ቀርቶ ትምህርት ቤታችሁ ላይ የተለጠፈውን “የእኛ ተግባር መማር መማር መማር” የሚለውን እንኳን አታስታውሺም?” አሏት፡፡
ልጅቱም፤
“አባዬ፤ ሌኒንኮ ተማሩ አለ እንጂ፤ ተፈተኑ አላለም!” አለቻቸው፡፡

         የኢትዮጵያ አየር መንገድና የቱር ኦፕሬተርስ አሶስዬሽን የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን ቁጥር ለመጨመር፣ በትራንስፖርትና በአገልግሎት ክፍያ ዋጋ ላይ ቅናሽ ማድረጋቸውን አስታወቁ፡፡ የሆቴሎች ዋጋም ይቀንሳል ተብሏል፡፡ በቅርቡ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድና አገልግሎት ሰጪ የሆነው የአስጐብኚ ድርጅቶች ማኅበር (ቱር ኦፕሬተርስ አሶስዬሽን) ከትናንት በስቲያ በጋራ በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በርካታ የቱሪስት መዳረሻ ባለቤት ብትሆንም፣ የቱሪስቶች ፍሰት ከቁጥር የማይገባ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በውጭ አገራት ያሉ የተፎካካሪ አገራት የቱሪስት ወኪሎች “ኢትዮጵያን ለመጐብኘት የትራንስፖርትና የሰርቪስ ዋጋ ውድ ነው፣ የአገልግሎት አሰጣጡ (የሆቴሎች ንፅህና፣ መስተንግዶ) ጥራት ዝቅተኛ ነው፤….” በማለት የሚያሰራጩትን የአገሪቱን ገጽታ አፍራሽ ፕሮፓጋንዳ ለማክሸፍ፣ አዲስ ስትራቴጂ ቀርፀው መንቀሳቀስ መጀመራቸውን ድርጅቶቹ ተናግረዋል፡፡ በዚሁ መሠረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቱሪስቶችን ቁጥር ለማብዛት በትራንስፖርት ክፍያ ላይ 40 በመቶ ቅናሽ ማድረጉን የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም የገለጹ ሲሆን፣ የቱር ኦፕሬተሮች አሶስዬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ፍፁም ገዛኸኝ በበኩላቸው፤ አስጐብኚ ድርጅቶች ከሚያስከፍሉት የአገልግሎት ዋጋ ላይ 20 በመቶ እንደሚቀንሱ አስታውቀዋል፡፡

የሆቴሎች ማኅበር ፕሬዚዳንት አገር ውስጥ ባለመኖራቸው ምን ያህል እንደሚቀንሱ አልታወቀም፡፡ አዲሱ ስትራቴጂ የኢትዮጵያ ተፈጥሯዊና ታሪካዊ የቱሪስት መስህቦች አውቆ መለየትና ለቱሪስቶች ማስተዋወቅ ነው ያሉት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ታደሰ፣ ለቱሪስት መዳረሻዎቹ አስፈላጊ መሠረተ ልማት (የአየርና የየብስ ትራንስፖርት፣ የንፁህ ውሃና የመብራት) አገልግሎት ማሟላት በቱሪስት መዳረሻዎቹ አካባቢ ዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ንፅህናው የተሟላ የመኝታ፣ የምግብ፣ አስተማማኝ ጥበቃና የደህንነት አገልግሎት በመስጠት፣ የኢትዮጵያ እምቅ ተፈጥሮዊና ታሪካዊ መስህቦች ለዓለም ማስተዋወቅ፣ የቱሪስቶችን ቁጥር ማብዛትና ከቱሪዝም ዘርፍ የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ የስትራቴጂው ግብ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ ቀደም ሲል በረሃብ፣ ድርቅና ጦርነት የምትታወቀው ኢትዮጵያ፤ ባለፉት 20 ዓመታት ባሳየችው የልማት እንቅስቃሴ በዓለም አቀፍ ደረጃ ገጽታዋ እየተለወጠ ነው ያሉት አቶ ተወልደ፤ ሚዲያውና በዘርፉ የተሰማራን ሁሉ ይህን አጋጣሚ በመጠቀም፣ ዓለም አቀፍ ደረጃን ያሟላ አገልግሎት በመስጠት፣ ቱሪስቶችን ለመሳብ እንረባረብ ብለዋል፡፡

የምሥራቅ አፍሪካ አገሮችን (ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ታንዛንያ) የሚጐበኙ ቱሪስቶች ቁጥር በርካታ እንደሆነ የገለፁት አቶ ተወልደ፤ ለምሳሌ በዓመት ኬንያን የሚጐበኙ ቱሪስቶች ቁጥር ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ሲሆን ኢትዮጵያን የሚጎበኙት ቱሪስቶች ከግማሽ ሚሊዮን በታች እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም ታዋቂና የአፍሪካ መዳረሻውም ብዙ ስለሆነ፣ ቱሪስቶች ወደ ምስራቅ አፍሪካ አገራት የሚጓዙት በእኛ አውሮፕላን ነው፡፡ በአዲሱ ስትራቴጂ ዋጋችን ተመጣጣኝና ተወዳዳሪ ስለሚያደርገን፣ የምንሰጠውም አገልግሎት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የሚያሟላ ስለሚሆን ብዙ ቱሪስቶች ወደ አገራችን ይመጣሉ ብለዋል፡፡ የቱሪስት መስህቦቻችንን ማልማትና ማስተዋወቅ/ በቅርቡ የተቋቋሙት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ቦርድና ኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ዋነኛ ተግባር ናቸው ያሉት አቶ ፍፁም፤ 80 በመቶ መስህቦቻችንን ለማልማት፣ 20 በመቶ ዳግም ለማስተዋወቅ ሥራ የተሰጠ በመሆኑ፣ የቱሪስት መዳረሻዎችን መሰረተ ልማት ማሟላት፣ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት፣ ማህበረሰቡን ማስተማር ሰፊ ድርሻ የተሰጠው በመሆኑ፤ የቱሪስቶች ቅሬታ ስለሚወገድ ብዙ ጎብኚ ይኖረናል ብለዋል፡፡

         የሼፎችና ባሬስታዎች ውድድር ይካሄዳል ሁለተኛው “ሆቴል ሾው ኢትዮጵያ 2006”፤ ከግንቦት 8 እስከ 10 በሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ ኦዚ ሆስፒታሊቲ እና ቢዝነስ ግሩፕ አስታወቀ፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የተለያዩ ዝግጅቶች የሚቀርቡ ሲሆን ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ ማሽኖችና ሶፍትዌር አቅራቢዎች፣ የሆቴል አማካሪ ድርጅቶች፣ ሆቴሎች፣ ሪዞርቶች ፣ የሆቴል እቃ አቅራቢዎችና የአስጐብኚ ድርጅቶች የሚሳተፉበት የንግድ ትርኢት እንደሚቀርብ ተጠቁሟል፡፡ የሀገሪቱን የሆቴልና ሆስፒታሊቲ ኢንዱስትሪ ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እና ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያስችል ሲምፖዚየምም የዝግጅቱ አካል ሲሆን በሲምፖዚየሙ ላይ ከ400 በላይ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎች ምክክር ያደርጉበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የሼፎችና ባሬስታዎች ውድድርም የሚካሄድ ሲሆን ውድድሩ ከጣሊያን እና ቱርክ በመጡ ዳኞች እንደሚዳኝ ተገልጿል፡፡ “ሆቴል ሾው ኢትዮጵያ 2006” በኢፌዲሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ድጋፍ እንደሚደረግለት የተገለፀ ሲሆን ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል እንዲጐበኘውና በዘርፉ ያለው ግንዛቤ እንዲሰፋ መግቢያ በነፃ እንዲሆን መወሰኑ ተገልጿል፡፡ ዝግጅቱን ከ35ሺህ በላይ ሰዎች ይጐበኙታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አዘጋጁ ኦዚ ሆስፒታሊቲ እና ቢዝነስ ግሩፕ ጠቁሟል፡ የመጀመሪያው “ሆቴል ሾው ኢትዮጵያ 2006” ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 2 ቀን 2006 ዓ.ም በተባበሩት መንግስታት የስብሰባ አዳራሽ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ከ7500 በላይ ሰዎች የንግድ ትርኢቱን እንደጐበኙት ታውቋል፡፡

             ከሩብ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ ለመኪና ማቆሚያ የሚሆን ፎቅ እንደሚያስገነባ የገለፀው ኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል፤ በቡራዩ እና በቢሾፍቱ ሁለት ዘመናዊ ሪዞርቶችን ሊያስገነባ ነው፡፡ ባለፈው ህዳር ወር ስራ የጀመረው ኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል፤ አለማቀፍ ደረጃዎችን በማሟላት በሃገራችን አሉ ከሚባሉ ሆቴሎች አንዱ መሆኑን የገለፁት ስራ አስኪያጁ ፕ/ር ኤዲ ባሬንቶ፤ በግንባታ ጥበቡ በውስጣዊ ይዘቱ፣ በቴክኖሎጂዎች አጠቃቀሙና በሰው ኃይል አደረጃጀቱ እጅግ ዘመናዊ በመሆኑ የአፍሪካ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ ድምቀት እንደሆነ ማንም ሊመሰክር ይችላል ብለዋል፡፡ በ1690 ካሬ ሜትር ለመኪኖች ማቆሚያ (ፓርኪንግ) አገልግሎት የሚሰጥ አለማቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ፎቅ በ 258 ሚሊዮን ብር እንደሚያስገነባ ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡

የኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል ባለቤት አቶ ገምሹ በየነ፤ ዘመናዊ የመዝናኛ ስፍራዎችንና ሰፋፊ የስብሰባ አዳራሾችን ያካተተ ሪዞርት በቡራዩ እያስገነቡ ሲሆን፤ ሪዞርቱ አዲስ አበባን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ከፍታ ቦታ ላይ መሆኑን ፕ/ር ባሬንቶ ገልፀዋል፡፡ በቢሾፍቱ ባቦጋያ ሃይቅ አካባቢ እየተገነባ ያለው ሌላው ሪዞርት እጅግ ዘመናዊ መሆኑን ፕ/ር ባሬንቱ ሲያስረዱ፤ በአገሪቱ የመጀመሪያው ተጠቃሽ እንደሚሆን ጠቁመው፤ 2500 ሰው መያዝ የሚችል የስብሰባ አዳራሽ የያዘ ነው ብለዋል፡፡

በሆቴል ዘርፍ በቢሊዮን ብር የሚቆጠር ሃብት ኢንቨስት ያደረጉት አቶ ገምሹ በየነ፤ በመሰረተ ልማት በተለይም በመንገድ ግንባታ ላይ የተሰማራ “ገምሹ በየነ ኮንስትራክሽን (GEBECON)” የተሰኘ ኩባንያ ባለቤት መሆናቸውን ፕ/ሩ ጠቅሰው፤ በሃገሪቱ የመሰረተ ልማት እድገትና የስራ እድል ፈጠራ ላይ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ እንደቻሉ ተናግረዋል፡፡ ከ6ሺ በላይ ሰራተኞች ያሉት የኮንስትራክሽን ኩባንያው፤ በእውቅ የምህንድስና ባለሙያዎች የተደራጀ መሆኑን የገለፁት ፕ/ሩ፣ ከገነባቸው መንገዶች መካከል በትግራይ ከማሃበሬ እስከ ዲማ እና ከዲማ እስከ ፈየል ውሃ፣ በጐንደር ከአዘዞ እስከ ጎርጎራ እና የመሃል ሜዳ መንገድ ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም ከድሬድዋ እስከ ደወሌ እንዲሁም በሶማሌና በሃረሪ ክልል የመንገድ ግንባታዎችን ያከናወነው ኩባንያው፣ በርካታ መንገዶችን ሰርቶ እንዳስረከበ ተገልጿል፡፡

ፕ/ር ባሬንቶ ስለ አቶ ገምሹ በየነ ሲናገሩ፤ ከኢንቨስትመንት ጋር በተለይ በበጐ አድራጐትና በአገር ወዳድነታቸው የሚታወቁ ናቸው ይላሉ፡፡ በዘርና በጎሳ የማያምኑ፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ባላቸው እውቀትና ብቃት ሰርተው ኑሯቸውን እያሻሻሉ፣ ሃገራቸውንም እንዲጠቅሙ የሚጣጣሩ በመሆናቸው፣ በፈተና እና በስራ ምዘና እንጂ በዝምድና እንኳ እንደማይቀጥሩ በማየት እናደንቃቸዋለን ብለዋል፤ ፕ/ር ባሬንቶ፡፡


ዳሽን ባንክ እና የአሜሪካው ኤክስፕረስ ኔትወርክ የኤቲኤም የካርድ አገልግሎት ስምምነት የተፈራረሙ ሲሆን በቅርቡ የአሜሪካ ኤክስፕረስ ካርድ አገልግሎት በሁሉም የዳሽን ባንክ ኤቲኤም ማሽኖች እንደሚጀምር ተገለፀ፡፡ የባንኩ የፕሮሞሽን ዋና ክፍል ኃላፊ አቶ እስጢፋኖስ በፈቃዱ፤ የኤቲኤም ማሽን የካርድ አገልግሎቶችን እየተገበረ መሆኑን አስታውሰው፤ በሃገሪቱ ብቸኛ ባንክ የሚያደርገው፤ የአሜሪካን ኤክስፕረስ ካርድ አገልግሎት፣ የሙከራ ሂደቱ እንደተጠናቀቀ በይፋ ይጀምራል ብለዋል፡ በርካታ የውጭ ሃገር ቱሪስቶች የአሜሪካን ኤክስፕረስ ካርድ ተጠቃሚ ናቸው ያሉት ኃላፊው እስከዛሬ በዚህ ካርድ በኢትዮጵያ ውስጥ ገንዘብ ማውጣት እንደማይቻል ጠቁመው፤ ዳሽን ባንክ አገልግሎቱን መጀመሩ ብቸኛው እንደሚያደርገው ተናግረዋል፡፡ የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ ወ/ስላሴ በስምምነት ፊርማው ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ባንካቸው በኢትዮጵያ ያለውን የልማት እንቅስቃሴ እየደገፉ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁን ካሉት የኤቲኤም ካርዶች በተጨማሪ፣ የአሜሪካን ኤክስፕረስ ካርድ አገልግሎት መጀመሩ፣ ባንኩንም ሃገሪቱንም ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡ ዳሽን ባንክ በኢትዮጵያ ተጠቃሽ ከሆኑ የፋይናንስ ተቋማት አንዱ ነው ያሉት የአሜሪካ ኤክስፕረስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፒተር ላይስ በበኩላቸው፤ ባንኩ ለደንበኞች አገልግሎት እርካታ የሚተጋ መሆኑን፣ የአሜሪካን ኤክስፕረስ ካርድ ተጠቃሚነቱ ይመሰክራል ብለዋል፡፡

ይኸው ተገልጦ ከማያልቀው ታሪካችን ለዛሬ ይህን ገፅ ፈቅዳችሁ ብታነቡኝ በመጨረሻ አእምሮአችሁ ውስጥ በርካታ ጥያቄዎች ሊነሱ እንደሚችሉ እገምታለሁ፡፡ አንባቢው ፀሃፊ (የስነ ፅሁፍ ሰው) ከሆነ ደግሞ ቀጥሎ ከማወጋችሁ ብጥስጣሽ የህይወት ገፅታዎች ጫፋቸውን ይዞ በመከተል ሌሎች ደርዞችን ሊያወጣ ይችላል፡፡
በየትኛው ግለሰብ ታሪክ ልጀምር፡- ስሜትን በሚጎዱ፣ በሚያሳዝኑ፣ እጅግ በሚደንቁና በሚያስደስቱ፣ የሚገርም የስነ ልቦና ብርታት በሚታይባቸው፣ ወደ ስጋት ስሜት በሚጨምሩ? ቆይታዬ እስከ አስር የሚደርሱ ታዳጊ ወጣቶች ጋር ነበር እድሜአቸው ከ14 እስከ 18 ነው፡፡ የተለያዩ ጥያቄዎችን እያነሳሁ፡፡ የግል ጉዳይ ከመሆኑ አንፃር አንድ በአንድ ለማውጋት ችለናል፡፡
እድሜህ ስንት ነው?
   “14”
ስንተኛ ክፍል ነህ?
  “9ኛ”
የትምህርት ደረጃህ እዴት ነው ጎበዝ ነህ ወይስ?
  “ በጣም ጎበዝ ተማሪ ነኝ 8ኛ ክፍል በት/ቤቴ ከፍተኛ
   ውጤት ካመጡ ውስጥ አንዱ ነኝ 92 ነው ያመጣሁት
   ከ7 ወደ 8ኛ አንደኛ ነው የወጣሁት”
ቤት ምን ይደረግልሃል እደዚህ ከፍተኛ ውጤት   ስታመጣ?
   “ ብስክሌት ሁሉ ተሸልሜ አውቃለሁ”

ሌላዋ የ 18 ዓመት ታዳጊ ወጣት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ስትሆን የጤና ትምህርት ትማራለች፡፡ መቼና እንዴት ከቫይረሱ ጋር እንደምትኖር አወጋችኝ፡፡ የሰባት አመት ልጅ ከሆነች በኋላ የጊዜ ቁጥጥር እየተደረገ መድሃኒት እንድትወስድ ይደረጋል፡፡ ይህን መድሃኒት ግን ሌሎች ታላላቆቿ አይወስዱም፡፡ እንክብካቤ ይበዛባል፡፡ በተወሰኑ ጊዜያት በሁለትና በሶስት ወራት ጊዜ ሃኪም ቤት በመሄድ የጤና ምርመራ እንድትወስድ ይደርጋል፡፡ ይች ህፃን እያደገች ስትሄድ የንባብ አቅሟም ከነበረበት ሲጎለብት ከመድሃኒቷና ምርመራዋ ጋር የተያያዙ ወረቀቶችን ታነባለች፡፡ ልጆች እንኳንስ እንዲህ የተለያዩ ጉዳዮችን እየተመለከቱ እንዲሁም በርካታ ጥያቄዎችን ማንሳታቸው የማይቀር ነው፡፡ ይች ልጅም ጥያቄዎችን ማጉረፍ ጀመረች… ቀጠለች፡፡ እድሜዎ 13 ሲደርስ ግን የሆነው ሁሉ በሃኪሟ አማካኝነት ተገለጠላት
“ ግን ያኔ አብዛኛውን ጉዳይ ቀድሜ ስለጠረጠርኩና ስላወኩ ብዙ አልተደናገጥኩም፡፡ ቤተሰቦቼም በጣም አገዙኝ፡፡”
ሌላዋ የሞያና ቴክኒክ ተማሪ የሆነችው የ17 ዓመት ታዳጊ ወጣትም በተመሳሳይ መንገድ ነው ከቫይረሱ ጋር መኖሯን ያወቀችው፡፡ የምትወስዳቸው መድሃኒቶችና ሌሎች የምርመራ ወረቀቶቿን (CD4 መጠንን የሚገልፁ) አስቀድማ ታነብ ነበር፡፡ ሆኖም እናቷን  ላለማስጨነቅ ጥያቄውን ማንሳት አልፈለገችም፡፡ በኋላ ሃኪሟ ከቫይረሱ ጋር እንደምትኖር (አግባብ ነው ባለችው እድሜ) ስትገልፅላት አውቃለሁ አትጨነቂ በሚል ነው የተቀበለችው፡፡ ጊዜውን ጠብቆ መድሃኒት መውሰድ ለብዙዎቹ ታዳጊ ወጣቶች መደበኛና በጣም ተለመደ ድርጊት ነው፡፡ “ለእኔ ኖርማል ነው፡፡ ቁርስ ምሳ ትበላለህ ውኃ ትጠጣለህ እነዚህ ጉዳዮች ለመኖር አስፈላጊ ናቸው፤ ሳትበላ ወይም ሳትጠጣ መኖር አይቻልም መድሃኒቱም ለእኛ እንደዛው ነው” ይላል ሌላው የ16 ዓመት ታዳጊ፡፡
ከእነዚህ ታዳጊ ወጣቶች ጋር በነበረኝ ቆይታ ሌላው በጣም አስፈላጊ የነበረው ጉዳይ የፆታ ግንኙነትን የተመለከተው ­ጥያቄ ነው፡፡ ወጣቶች ናቸው፣ በርካታ ጓደኞች ይኖራሉ፤ ትምህርት፣ ጨዋታ፣ መዝናናት፣ ይኖራል፡፡ በዚህ እድሜና የህይወት ገፅ ላይ ደግሞ መወደድም መውደድም (ማፍቀርም መፈቀርም) ይኖራል፡፡ የፆታ ጓደኝነትና የፍቅር ግንኙነት ጥያቄም ሊቀርብ ወይም ሊያቀርቡ ይችላሉ፡፡ ይህን በተመለከተ ያለው አስተሳሰብ የተለያየ ነው፡፡ አንዳንዶቹ ይህን ጉዳይ ፈፅሞ አስበውበት የማያውቁ ናቸው፤ አንዳንዶቹ ጓደኛ አላቸው፡፡ ሆኖም ጓደኛ የያዙት በተመሳሳይ መንገድ (ከእናት ወደ ልጅ ቫይረሱ ከተላለፈባቸውና) ከቫይረሱ ጋር ከሚኖሩ የእድሜ አቻዎቻቸው ጋር ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ ፍቅሩ መዋደዱ ወይም ጥያቄው ከቫይረሱ ጋር ከማይኖር ሰው ከመጣስ ወይም ከተፈጠረስ ለሚለው ጥያቄ አንዳንዶች ፈፅሞ አላደርገውም ተገቢም አይደለም ብለው ያስባሉ፡፡ ከዚህ ሁኔታም መራቅ እንደሚፈልጉ ይገልፃሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ እንደሁኔታው ሊወሰን ይችላል፡፡ ለምሳሌ “ጥያቄውን የሚያነሳው ከቫይረሱ ጋር የማይኖር ሰው ከሆነ ራሴን እገልፅላታለሁ፡፡ ሆኖም ፍቅሩ ካየለና መለያየቱ ከባድ ከሆነ አብሬ ልሆን እችላለሁ” ሌላዋ ወጣት ደግሞ “ይከብዳል ምናልባት ዛሬ በአፍላ እድሜና ፍቅር ምንም አይደለም ሊባል ይችላል ነገ ከነገ በኋላ ግን ግጭት ሊፈጠር ይችላል፣ ስሜትን የሚጎዱ ነገሮች ሊከሰቱ ይችላሉ” የሚሉ አስተሳሰቦች ይሰማሉ፡፡
ልጆቹ በአብዛኛው እንደገለፁልን በመኖርያ አካባቢያቸውና በትምህርት ቤቶቻቸው ያላቸው የህይወት ጉዳይ ሁለት የተለያየ ገፅ የያዘ ነው፡፡ በሰፈራቸው አብረዋቸው ለመብላት የሚፈሩ አብሮ መጫወት የሚሰጉ፣ ተገቢ ያልሆኑ ድርጊቶችን የሚፈፀሙ ሰዎች እንዳሉ ይነገራሉ፡፡ በአንፃሩ በት/ቤቶቻቸው ደግሞ የልጆቹ ማንነት ምንም ስለማይታወቅ ሁሉም ነገር ምንም ባልተለየ መንገድ ይጓዛል(ማግለል፣ መፍራት፣ መፈራት፣ አይታይም)፡፡ ይሁንና ትላለች የዩኒቨርሲቲ የጤና ተማሪ የሆነችው የ18ዓመት ታዳጊ ወጣት አብዛኞቹ የጤና ተማሪዎች አይመስሉም ስለ ኤች አይ ቪ ያላቸው አስተሳሰብና እውቀት ያስደነግጠኛል ፍፁም ከእነሱ የማይጠበቅ ጉዳይ ያጋጥማል በቁንጫ ቫይረሱ ይተላለፋል የሚል ግምት ያለው ሰው ያጋጥማል፡፡
አብዛኞቹ ከቫይረሱ ጋር በሚኖሩ ታዳጊ ወጣቶች ዘንድ የተገነዘብኩትና ተመሳሳይ ሆኖ ያገኘሁት አንድ ጉዳይ አለ፣ ከቫይረሱ ጋር መኖራቸውን እያወቁ(እየተጠራጠሩ) ደጋግመው ጥያቄዎችን ለወላጆች (ለአሳደጊዎቻቸው፡- በአያት፣ በአክስት፣ በእናት ብቻ፣ ወዘተ የሚያድጉ አሉ) ማንሳት አይፈልጉም መድሃኒት በየቀኑ ለምን እንደመሚወስዱና ሃኪም ቤት በተደጋጋሚ ለምን እንደሚሄዱ አይጠይቁም፣ አባታቸው ወይም እናታቸው (ወይም ሁለቱም) በህይዎት ይኑሩ አይኑሩ አይጠይቁም፡፡ ለምን ለሚለው ጥያቄ የአብዛኞቹ  አስተሳሰብ ሲጠቀለል ወላጆቻቸው እንዲጨነቁ ስለማይፈልጉ ነው፡፡ በፈለጉት ጊዜ ይንገሩንየሚል ሃሳብ ነው ያላቸው፡፡ በእርግጥ ይህ አስተሳሰብ የአብዛኞቹ እንጂ የሁሉም አይደለም፡፡ ለምሳሌ የ17 አመት ታዳጊ ወጣት የሆነችው ባለታሪክ እድሜዋ 14 እስኪደርስ ከቫይረሱ ጋር እንደምትኖር አታውቅም፡፡ ሁለት ወንድሞች አሏት ፣ እናቷ ከቫይረሱ ጋር ይኖራሉ፣ አባትዋ በህይወት የሉም፡፡ ይች ታዳጊ ወጣት ጉዳዩን እናቷ እስከዚህ እድሜ በመደበቃቸው እጅግ እንዳዘነች (እያለቀሰች) ትናገራለች፡፡ እናቴ ይህን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ብዙ ጉዳዮች እንደምትደብቀኝ ተሰማኝ በወቅቱ መድሃኒቱን በአግባብና ለምን እነደምወስድ ሳልጨነቅ መውሰድ እችል ነበር፡፡ ሆኖም ለብዙ ጊዜ ደበቀችኝ፡፡ ይህች ታዳጊ ወጣት ከሁለት ወንድሞቿ ውስጥ አንዱ ቫይረሱ የለበትም፡፡ የሌላኛው ሁኔታ ግን አይታወቅም፡፡ የራሱ ሁኔታ አለመታወቁ ብቻ ሳይሆን ስለ ቤተሰቦቹ(ስለ እናትና እህቱ) ከቫይረሱ ጋር መኖር አያውቅም፡፡ ይህም በጣም እንዳሳሰባት ትገልፃለች፡፡
እንግዲህ ወደ ኋላ መለስ ብለን ያለፈውን ጊዜ ስንመለከት ከ20 ዓመታት በፊት ከነበረው ጊዜ ጀምሮ የቫይረሱ ስርጭት እየጨመረ በርካቶች የእድሜ ማራዘሚያ መድሃኒት ባለማግኘታቸው እንዲያልፉ ግድ ነበር፡፡ በዚያን ወቅት ወላጆች ብቻ ሳይሆኑ ከእነርሱ የሚወለዱ ልጆች ከተወለዱበት ቀን ጀምሮ በወራት እድሜ ውስጥ በርካቶች ከእቅፍ አምልጠዋል፡፡ ጊዜ ተለውጦ መድሃኒቱ ወደ ሀገራችን ከገባበት ( በተለይ በነፃ ከቀረበበት) ጊዜ ጀምሮ በርካታ ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ወገኖች ህይወታቸውን በአግባቡና በጤና ለመመራት ያስቻለ ሲሆን ራስን የመተካት ምኞትም እውን ሆኗል፡፡ መድሃኒቱ በተለይ ቫይረሱ ከእናት ወደ ልጅ የመተላለፍ እድል እንዳይኖር ረድቷል፡፡ ይሁንና ዛሬ የዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆኑት ታዳጊዎች ምንም እንኳን መድሃኒቱ ደርሶላቸው ከቫይረሱ ነፃ መሆን ባይችሉም እድሜያቸውን ለማራዘም ግን መደበኛውን መድሃኒታቸውን ተግተው ይወስዳሉ፡፡ አብዛኞቹ ትልቅ ተስፋ አላቸው የሳይንስ እድገት በእነሱ እድሜ መፍትሄ እንደሚወልድ፡፡ የሁላችንም ተስፋ ነው፡፡ በርቱልን
 የዚህ ርእሰ ጉዳይ ወግ አልተጠናቀቀም፣ ከፈቀዳችሁ ሳምንት አንብቡኝ፡፡