Administrator

Administrator

“የዛምቢያን ባህል ሳልረሳ የፖላንድን ባህል ተምሬአለሁ”

በትውልድ ዛምቢያዊ የሆኑት ፕሮፌሰር ኪለን ሙንያማ፤ የፖላንድ የፓርላማ አባል ሲሆኑ በተለያዩ ጊዜያት በፖላንድ በተካሄዱ ምርጫዎች ተወዳድረው በከፍተኛ ድምፅ በማሸነፍ ለመመረጥ በቅተዋል፡፡ የዩኒቨርስቲ ትምህርታቸውን እዚያው ፖላንድ የተከታተሉ ሲሆን በኢኮኖሚክስ የማስትሬትና የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከፐዝናን ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኢኮኖሚክስ አግኝተዋል፡፡ ፕሮፌሰን ኪለን ባለፈው ሳምንት ከኢትዮ - ፖላንድ የፓርላማ ቡድን ጋር ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ጉብኝት አድርገዋል፡፡
የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ኤልሳቤት እቁባይ ከፕሮፌሰሩ ጋር በነበራት ቆይታ በጉብኝታቸው፣ በፖለቲካ ህይወታቸው፣ በአውሮፓ የኢኮኖሚ ቀውስና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ አነጋግራቸዋለች፡፡

     የኢትዮጵያ ጉብኝታችሁ በምን ላይ ያተኮረ ነው?
ጉብኝታችን ለኢትዮ-ፖላንድ የፓርላማ ቡድን በተደረገው ግብዣ መነሻነት የተከናወነ ነው፡፡ ግብዣው የተላከው በ2013 ዓ.ም ሲሆን ለጉዞው የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት አሁን ልንመጣ ችለናል፡፡ በጉብኝቱ የሚሳተፈው የልኡካን ቡድን በፓርላማ አባላቱ ብቻ ከሚወሰን ከኢትዮጵውያን ጋር በትብብር ለመስራት የሚፈልጉ   የተለያዩ የፖላንድ የቢዝነስ ኩባንያዎችን እንዲያካትት ባደረግነው ጥረት ስድስት ትላልቅ ኩባንያዎችን ይዘን ነው የመጣነው፡፡ የአፍሪካ ፖላንድ የንግድ ምክር ቤት ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት የሚፈልጉትን ኩባንያዎች በማደራጀት በኩል አግዞናል፡፡ ስለዚህ የጉብኝቱ አላማ ፖለቲካዊም ኢኮኖሚያዊም ነው ማለት ይቻላል፡፡
የኢትዮ - ፖላንድ የፓርላማ ቡድን ዓላማ ምንድን ነው?
ፓርላማዎች የሚመሳሰሉባቸውና የሚለያዩባቸው ነገሮች ይኖራሉ፡፡ የፖላንድ ፓርላማ የራሱ አወቃቀር አለው፡፡ ፓርላማው የተለያዩ ኮሚቴዎችና የፓርላማ ቡድኖች አሉት፡፡ የፓርላማው ቡድኖች ከተለያዩ አገሮች ፓርላማዎች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ይሰራሉ፡፡ የፓርላማ አባላቱም የሚፈልጉትን አገር የፓርላማ ቡድን ይቀላቀላሉ፡፡ የቡድኖቹ አላማ በአገሮቹ መካከል ያለውን ግንኙነት በማጠናከር ላይ ያለመ ነው፡፡ ፓርላማችን ከአስራ አምስት የአፍሪካ አገሮች ጋር የፓርላማ ቡድን ግንኙነት አለው፡፡ የኢትዮ-ፖላንድ የፓርላማ ቡድንም አንዱ ነው፡፡ እኔ የኢትዮ-ፖላንድ፣ የዛምቢያ - ፖላንድ እና የኬኒያ - ፖላንድ የፓርላማ ቡድኖችን በሊቀመንበርነት እመራለሁ፡፡ በሌሎች በተለይ ከአፍሪካ ጋር የተገናኙና በፖላንድ አሜሪካን ቡድን፣ በብሪቲሽ ፖላንድ፣ በፖርቹጋል ፖላንድ የፓርላማ ቡድኖች ውስጥ በአባልነት እሳተፋለሁ። የፓርላማ ቡድኖቹ  ሊቀመንበር ወይም አባል ከሆኑባቸው አገሮች የሚመጡ ልኡካንን ተቀብሎ ያነጋግራል፣ በተለያዩ የጋራ ጉዳዮች ላይ በትብብር ይሰራል፡፡ የኢትዮ ፖላንድ የፓርላማ ቡድን አላማም ይኸው ነው፡፡
በብረታብረትና ኢንጂኒየሪንግ ኮርፖሬሽን ያደረጋችሁት ጉብኝት አላማ ምን ነበር?
አብረውን የመጡት ኩባንያዎች ስለ ስራቸው አስተዋውቀዋል፡፡ የድርጅታቸውን የሥራ ታሪክና በትብብር መስራት የሚፈልጉባቸውን መስኮችም ለብረታብረትና ኢንጂኒየሪንግ ኮርፖሬሽን ሰጥተዋል፡፡ አንዳንዶቹ መስኮች ኮርፖሬሽኑ  በጣም ትብብር የሚፈልግባቸው እንደሆኑ ተገንዝበናል፡፡ ጉብኝታችንና የተደረጉት ውይይቶች ጥሩ ውጤት ያመጣሉ ብለን እንጠብቃለን፡፡ ምክንያቱም አብዛኞቹ አብረውን የመጡት ኩባንያዎች የብረታብረትና ኢንጂኒየሪንግ ኮርፖሬሽን ከሚሰራቸው ስራዎች ጋር የሚገናኝ ስራ ላይ የተሰማሩ ናቸው፡፡
እንዴት ነው ወደ ፖለቲካው የገቡት? አፍሪካዊ ሆነው እንዴት የፖላንድ የፓርላማ አባል ለመሆን ቻሉ?
ሁሉም ነገር የሆነው የፖላንድ ዜግነት ካገኘሁ በኋላ ነው፡፡ በመጀመሪያ ወደ ፖላንድ የሄድኩት እ.ኤ.አ በ1981 ዓ.ም ለትምህርት ነበር። ከኔ ጋር አራት ዛምቢያውያን ስንሆን፣ አስራ አራት ኢትዮጵያውያንም አብረውን ነበሩ፡፡ አንድ አመት የቋንቋ ኮርስ ከወሰድኩ በኋላ  ትምህርቴን በመቀጠል በ1987 ነበር ያጠናቀቅሁት፡፡ በነገራችን ላይ ሁላችንም አገራችንን ስንለቅ የመጀመሪያ ዲግሪያችንን ይዘን ለመመለስ በሚል ነበር፡፡ ወደ አገራችን የተመለስነው ግን የማስተርስ ዲግሪያችንን ሰርተን ነበር፡፡ ትምህርቴን እንደጨረስኩ እዚያው ፖላንድ ስልጠና የማግኘት እድል ስለተሰጠኝ ስልጠናዬን ጨርሼ ነው ወደ ዛምቢያ የተመለስኩት። ለሶስት ወራት ያህል በዛምቢያ ንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ ከሰራሁ በኋላ እንደገና የዶክትሬት ዲግሪዬን ለመስራት እዚያው ፖላንድ ስኮላርሺፕ በማግኘቴ፣ በ1988 ዓ.ም ወደዚያው ሄድኩ፡
ኮሙኒዝም እየከሰመ የነበረበት ወቅት ነው። በዚህ የተነሳ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ሁኔታዎች እየተለወጡ ነበር፡፡ በመጨረሻም ኮሙኒዝም ሙሉ በሙሉ ሲወድቅ በሰዎች ህይወት ላይ ለውጥ መጣ። የዶክትሬት ዲግሪ የመመረቂያ ፅሁፌን ከማቅረቤ በፊት የዩኒቨርሲቲ መምህር ሆኜ ተመደብኩ፡፡ በ1999 ዓ.ም ደግሞ የፖላንድ ዜግነት አገኘሁ፡፡
ይኼኔ ነው ወደ ፖለቲካው የገቡት?
በ2002 ዓ.ም የአካባቢ ምርጫ ይደረግ ነበር፡፡ የዲስትሪክት (አውራጃ) ሀላፊው ለዲስትሪክት ምክር ቤቱ እጩ ሆኜ እንድቀርብ ጥያቄ ሲያቀርብልኝ በጣም ነበር ያስገረመኝ፡፡ ፖለቲካ ውስጥ የመግባት ምንም አይነት ፍላጎት አልነበረኝም፡፡ እዚያ ብዙ አመታትን ያሳለፍኩ ብሆንም ምርጫ ተወዳድሬ አሸንፋለሁ ብዬም አስቤ አላውቅም፡፡ ለሃላፊው  “ምርጫ እኮ የመራጮች ድምፅ ነው” ስለው፤ “ምርጫውን ተወዳድረህ ማሸነፍ ትችላለህ፤ ስለዚህ መወዳደር አለብህ” ብሎ ገፋፋኝ፡፡ እንግዲህ የሚሆነውን እናያለን ብዬው ተስማማሁ፡፡ ምንም አይነት የምረጡኝ ቅስቀሳ አላደረግሁም፣ ድምፅ የማገኝ ከሆነ የራሴንና የባለቤቴን ሁለት ድምፅ ብቻ እንደሚሆን በመገመት ወደ ምርጫው ገባሁ። ግምቴ ግን በጣም የተሳሳተ ነበር፤ አብላጫ ድምፅ በማግኘት ምርጫውን አሸነፍኩ፡፡ ያልጠበቅሁት ውጤት ስለነበር በጣም አስገረመኝም አስደሰተኝም።
ከዚያ በኋላ መራጮች ከኔ የሚፈልጉትን መስጠት እችላለሁ ወይ የሚለው ነገር የሚያሳስበኝ ሰው ሆንኩ፡፡ የተመረጥኩት ለአራት አመት ስለነበር የስራ ዘመኑ ሲያበቃ፣ ራሴን ለአውራጃ ምክር ቤት  ሳይሆን ከሱ ከፍ ወዳለው የክልል ፓርላማ እጩ አድርጌ አቀረብኩ፡፡ የክልል ፓርላማው ተመራጭ ለመሆን ደግሞ የፖለቲካ ፓርቲ አባል መሆን ያስፈልጋል፡፡
ስለዚህ “ሲቪክ ፕላትፎርም” የተባለውን የሊበራል ዲሞክራቲክ ፓርቲ ተቀላቀልኩና በ2006 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ አሸንፌ የክልል ፓርላማ ገባሁ፡፡ ከአራት  አመት በኋላ እንደገና በክልል ምርጫ አሸነፍኩ፡፡ በ2011 ዓ.ም በተደረገው አገራዊ የፓርላማ ምርጫ ፓርቲዬ እንድወዳደር እጩ አድርጎ ሲያቀርበኝ “ተወዳድሮ ማሸነፍ ይችላል ብላችሁ ካመናችሁ እወዳደራለሁ” ብዬ ተስማማሁ፡፡ የፖላንድ የፓርላማ ስርአት ተመጣጣኝ ውክልና (ፕሮፖርሽናል ሪፕረሰንቴሽን) ስለሆነ እኔ በምወዳደርበት የምርጫ ጣቢያ አራት የኔን የፓርቲ ወኪሎች ጨምሮ ዘጠኝ ተወዳዳሪዎች ነበርን፡፡ ከኔ ፓርቲ አባላት ውስጥ እኔ በማሸነፌ ፓርላማውን ተቀላቀልኩ፡፡
መራጩ ህዝብ ከእርስዎ የሚፈልገውን አሟልቻለሁ ብለው ያስባሉ?
ይህን ሊመልሱ የሚችሉት የመረጡኝ ሰዎች ናቸው፡፡ በመጪው ጥቅምት ወር በሚካሄደው ምርጫ ላይም ለመወዳደር አስቤያለሁ፡፡ ያኔ የማገኘውን ድምፅ አይቼ መናገር እችላለሁ፡፡ በእኔ በኩል ለተመረጥኩበት ቦታ ብቻ ሳይሆን ለአገሪቱ ማድረግ የምችለውን ሁሉ አድርጌያለሁ ባይ ነኝ፡፡
በአሁኑ ወቅት በአውሮፓ  ያለውን የኢኮኖሚ ቀውስ እንዴት ይገልፁታል?
አውሮፓን በአራት መክፈል እንችላለን፡፡  38 አገሮችን የሚያካትተው የአውሮፓ ህብረት፣ 19 አገሮችን ያቀፈው ዩሮላንድ የሚባለው የአውሮፓ ሞኒተሪ ህብረት፣ የአውሮፓ የነፃ ገበያ ቀጠና አገሮች እና የአውሮፓ ህብረት አገሮች ያልሆኑት የምስራቅ አውሮፓ አገሮች እነ ራሺያ፣ ዩክሬይን፣ቤላሩስ፣ ሰርቢያ፣ሞንቴኔግሮ፣ ቦስኒያሄርዞጎቪኒያ  የሚገኙበት ምድብ አለ፡፡ ከኢኮኖሚ ጋር በተያያዘ በዋነኛነት የማተኩረው ዩሮን በመገበያያ ገንዘብ በሚጠቀሙ  ዩሮላንድ ወይም የአውሮፓ ሞኒተሪ ህብረት በሚባለው ምድብ ላይ ባሉ አገሮች ነው። የኢኮኖሚ ቀውሱ የተፈጠረው ገንዘብ በአግባቡ ካለመጠቀም ጋር በተያያዘ ሳይሆን በአባል አገሮቹ በተለይ በግሪክ፣ ስፔን ፣ ፖርቹጋል፣ ጣሊያንና  አየርላንድ ውስጥ በተከሰቱ ውጣውረዶች ሳቢያ ነው፡ አገራቱ የኢኮኖሚ እድገታቸው መሻሻልን ቢያሳይም አሁንም ችግሮች አሉባቸው፡፡  ለምሳሌ ግሪክ  የበጀት እጥረትና ከፍተኛ የዕዳ ጫና አለባት፡፡ የነዚህ አገሮች እጣ ፈንታ የሚወሰነው በዩሮ ጥንካሬ ላይ ተመስርቶ ነው፡፡ የዩሮ የመግዛት አቅም ማጣት ይበልጥ ችግሩን ያወሳስበዋል፡፡ አንድ ሰው ከሰውነት ክፍሉ የተጎዳ ቦታ ካለ፣ ያንን ክፍል መቆጣጠር መከታተል ይጠበቅበታል፡ ግሪክ በአሁኑ ወቅት ልዩ ክትትል የሚያስፈልጋት የህብረቱ አገር ሆናለች። አዲሱ የግሪክ መንግስት አገሪቱ በህብረቱ ውስጥ የሚጠበቅባትን ግዴታ ለመፈፀም ጊዜ እንዲሰጣት እየተደራደረ ነው፡፡ ከዩሮላንድ ውጪ ያሉ አገሮችን ስናይ ለምሳሌ ፖላንድ፣ ሀንጋሪ፣ ቼክ ሪፐብሊክ፣ ስዊድንና ብሪቴይን አፈፃፀማቸው የከፋ አይደለም። እኛን (ፖላንድን) ብታይ እያደግን ነው፡፡
የአውሮፓ ህብረትና አይኤምኤፍ፤  ስፔይንና  ግሪክ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን በማድረግ ብድር እንዲያገኙ ቢጥሩም በተለይ በግሪክ ስልጣን የያዘው አክራሪው ግራ ፓርቲ ለማሻሻያዎቹ ዝግጁ አይደለም፡፡ አይኤምኤፍና የአውሮፓ ህብረት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ብድር እንዲለቁ ይፈልጋል። በፍላጐቱ መሰረት ምላሽ ቢያገኝ ዕዳውን የሚከፍለው ማነው?
አገሮቹ ኢኮኖሚያቸው የሚያገግምበትን መንገድ መፈለግ አለባቸው፡፡ የገንዘብ ብድርን በተመለከተ ቅድመ ሁኔታ አስፈላጊ ነው፡፡ የግሪክን ሁኔታ ስናይ አክራሪነት ብቸኛ መፍትሄ አይደለም፤ ለስለስ ማለት ያስፈልጋል፡፡ የአለምአቀፍ የገንዘብ ተቋም አባል ለመሆን ተቋሙ ለሚያስቀምጠው ህግ ተገዢ መሆን ይገባል፡፡ ዕዳውን ማነው የሚከፍለው ላልሽው… ከፋዮቹ ዜጎች ናቸው፡፡ እንግዲህ ግሪክ አትሸጥ፡፡ በዚህም የተነሳ ከፍተኛ ታክስ በመጣልና በመሳሰሉት መንገዶች ዜጎች ዕዳውን ይከፍላሉ፡፡ አፍሪካ እንደ አህጉር 300 ቢሊዮን ዩሮ ቢሰጣት ምን ያህል መሰረተ ልማት ሊገነባ እንደሚችል መገመት አያቅትም፡፡ ግሪክ 10 ሚሊዮን የማይሞላ ህዝብ ይዛ ይህን ያህል ገንዘብ ነው የጠየቀችው፡፡  ከዚህ አንፃር በአገሪቱ ጠንካራ የሆነ የሀላፊነት ስሜት፣  የተጠያቂነት ስርአት ሊኖር ይገባል፡፡
በአሁኑ ወቅት የአውሮፓ ፖለቲካ እየተለወጠ ነው፡ አክራሪ የግራ ፓርቲዎች በግሪክና በስፔይን እንዲሁም አክራሪ የቀኝ ኃይሎች በፈረንሳይና በእንግሊዝ፤ ብሔርተኞች ደግሞ በሀንጋሪ እየተጠናከሩና ምርጫዎችንም እያሸነፉ ነው፡፡ የዚህ አንደምታው ምንድን ነው?
አክራሪ ሀይሎች በአውሮፓ እየተጠናከሩ የመምጣታቸው ጉዳይ ምቾት የሚሰጥ አይደለም። ለዚህ ሁኔታ መከሰት  ብዙ ምክንያቶች አስተዋፅኦ አድርገዋል፡፡ አውሮፓ ለአውሮፓውያን ብቻ እንድትሆን እንዲሁም የአውሮፓ የመገበያያ ገንዘብ አውሮፓ ውስጥ ብቻ በስራ ላይ እንዲውል የሚፈልጉ ወገኖች አሉ፡፡  አውሮፓውያን ብቻ ሳይሆኑ ከተለያዩ ባህሎች እንዲሁም  ከሀይማኖት ጋር በተያያዘ ደስተኞች ያልሆኑ  ወገኖችም አሉ። በኔ አስተያየት አለም አንድ እየሆነ በመጣበት በግሎባላይዜሽን ዘመን የራሴ በሚል ተከልሎ መኖር አይቻልም፡፡ አሁን የሚያስፈልገው የራስን ከልሎ መያዝ ወይም ሌሎችን አግልሎ መኖር ሳይሆን ውህደት ነው፡፡
እኔ “ዘ ፓርላሜንታሪ አሴምብሊ ፎር ዘ ካውንስል ኦፍ ዩሮፕ” አባል ነኝ፡፡ 47 አገሮች በአባልነት ይገኙበታል፡፡ በስደተኞች ጉዳይና በተፈናቀሉ ሰዎች ዙሪያ እንወያያለን፡፡ አክራሪዎቹ እየጠነከሩ ነው፡፡ በግሌ ከባህልና ከሀይማኖት ጋር የተያያዙ  ግጭቶች መቀነስ አለባቸው ብዬ አምናለሁ፡፡ “ሮም ስትኖር ሮምን ምሰል” ይላል ተረቱ፡፡  የራስ ባህል ይረሳ ማለት አይደለም፡፡ እኔ የዛምቢያን ባህሌን ሳልረሳ የፖላንድን ባህል  ተምሬያለሁ፡፡ ፖላንድ ውስጥ በተካሄደ ጥናት፤ አክራሪዎች ከ7 በመቶ በታች ናቸው፡፡ ሁሉም ነገር ሚዛን ሲኖረው ነው ጥሩ የሚሆነው፡፡
በምስራቅ አውሮፓ በዘረኝነት ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠሩ አገሮች ውስጥ ፖላንድ አንዷ ናት፡፡ እንዲያውም ፖላንዳውያን ጥቁሮችን “ሙዢን” ብለው ነው የሚጠሩት፡፡ እርስዎ ደግሞ በፖላንድ ፓርላማ ውስጥ እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡ እስቲ ስለዘረኝነቱ ጉዳይ ይንገሩኝ?
ሙዚን ማለት ኒገር ማለት ነው፡፡ ቃሉ እንደ አጠቃቀሙ ሁኔታ ነው ትርጉም የሚሰጠው። የሚቀርብሽ ሰው ሙዢን ሲልና እንደ ስድብ የሚጠቀምበት ሰው ሲያጋጥም ትርጉሙ ይለያያል። ሙዚን ማለት ቆዳው የጠቆረ ማለት ነው፡፡ ፖላንዳውያን እርስ በርስ ሲጠቀሙበት ችግር የለውም፤ ጥቁር የሆኑ ሰዎች ሙዢን ሲባሉ ግን የሚያስቀይም  ይሆናል፡፡  ይህ ቃል ጥቅም ላይ እንዳይውል የምንፈልገው አሉታዊ ነገር ስላለው ነው፡፡ እኛ ከሙዚኖች በአንድ መቶ አመት ያህል እንደምንርቅ ይነገራል፡፡ ይህ አባባል ሌሎችን ስለሚያስቀይም ጥቅም ላይ ባይውል እንመርጣለን፡፡ እኔ ተማሪ ሆኜ በመጣሁበት ጊዜ ከዚህ ጋር በተያያዘ እንደማንኛውም ወጣት ተበሳጭቼና ግብግብ ገጥሜ አውቃለሁ፡፡ ያ ማለት ግን ፖላንዳውያን ዘረኞች ናቸው ማለት አይደለም። በመጀመሪያ ምርጫ ተወዳድሬ  እንዳሸነፍኩ ከዋርሶ ድረስ  እኔን ኢንተርቪው ለማድረግ የመጣ ጋዜጠኛ ነበር፡፡ ሰዎችን ቃለመጠይቅ ሲያደርግ፤ “ምን ያስገርምሀል? ከዋርሶ ድረስ መጥተህስ ለምን ቃለ መጠይቅ ልታደርግልን ፈለግህ? እሱ ከኛ ጋር የኖረ የኛ ሰው ነው፤ ስለዚህ  መረጥነው” በማለት መልሰውለታል። “እኛ የመረጥነው ኬለንን እንጂ ነጭ ወይም ጥቁር ብለን አይደለም” ብለውታል፡፡ አንቺ እንዳልሽው ስለ ፖላንድ ከዘረኝነት ጋር ተያይዘው ብዙ ነገሮች ይፃፋሉ፤ ነገር ግን የፖላንድ ፓርላማ እኔና አንድ ናይጄሪያዊን በፓርላማ አባልነት ይዟል።  ይህን ምን ትይዋለሽ?

Saturday, 21 March 2015 10:08

የፀሐፍት ጥግ

ፀሐፊ፤ የበለጠ ገንዘብ እንዴት አገኛለሁ ሳይሆን ብዙ አንባቢያን ጋ እንዴት እደርሳለሁ ነው ማለት ያለበት፡፡
ብሪያን አልዲስ
 ታሪክ ፀሐፊ ይመዘግባል፤ ልብ ወለድ ፀሐፊ ይፈጥራል፡፡
ኢ.ኤ.ፎርስተር
በአርታኢዎች ወይም በሃያሲያን አስተያየት አትዘን፡፡ እነሱ የጥበብ ትራፊክ ፖሊስ ናቸው፡፡
ጊኒ ፎውለር
ግንብን በመሬት ላይ ከመገንባት ይልቅ በአየር ላይ መገንባት የበለጠ እርካታ አለው፡፡
ኢድዋርድ ጊቦን
ስለምታውቀው ነገር ከመፃፍ ይልቅ  ስለሚሰማህ ነገር መፃፍ የተሻለ ነው፡፡
ኤል.ፒ.ሃርትሌይ
ፀሃፊ ጨርሶ እረፍት የለውም፡፡ የፀሐፊ ህይወት አንድም መፃፍ ነው አሊያም ስለሚፅፈው ማሰብ ነው፡፡
ኢዩጂኔ ሎኔስኮ
ጠዋት እነሳለሁ፤ መተየቢያ ማሽኑን እስኪያቃስት ድረስ እቀጠቅጠዋለሁ፤ ከዚያ አቆማለሁ፡፡
ክላረንስ ቡዲንግቶን ኬላንድ
የምንፅፈው ስለፈለግን አይደለም፤ የምንፅፈው መፃፍ ስላለብን ነው፡፡
ሶመርሴት ሟም
ፀሃፊውን ያላስለቀሰ፣ አንባቢውን አያስለቅስም፡
ጆርጅ ሙሬ
ሥራው መናገር ሲጀምር ደራሲው አፉን መጠርቀም አለበት፡፡
ፍሬድሪክ ኒቼ
 በትንሽ ድፍረት ማጣት ብቻ ዓለም ተሰጥኦዎችን ታጣለች፡፡
ሲድኒ ስሚዝ
የመጀመሪያው ምዕራፍ የአሁኑን መፅሃፍት ሲያሸጥ፣ የመጨረሻው ምዕራፍ ቀጣዩን መፅሃፍ ያሸጣል፡፡
ሚኪ ስፒላኔ
ሃያሲ መንገዱን የሚያውቅ ግን መኪና መንዳት የማይችል ሰው ነው፡፡
ኬኔዝ ቲናን
ለቃላት ድምፅ ትኩረት ስጥ፡፡
ዴቭ ዎልቨርተን
መፃፍ በወረቀት ላይ ማሰብ ነው፡፡
ዊሊያም ዚንሰር

ከዕለታት አንድ ቀን አንዲት ለአቅመ -ሄዋን የደረሰች የደረሰች ሴት ልጅ የነበረቻቸው እናትና አባት
በአንዲት መንደር ይኖሩ ነበር፡፡
ልጅቱ ከቀን ቀን እየወፈረች ሆዷ እየሞላ ትሄዳለች፡፡ የመንደሩ ሰው ሊጠይቃቸው ሲመጣ ጥያቄው

አንድ ዓይነት ሆነ፡፡
አንዷ ትመጣና፤
“እንዴት ዋላችሁ?”
“ደህና እግዚሃር ይመስገን”
“ጤናዎትን እንዴት ከረሙ?”
“አልፎ አልፎ ይጫጫነኝና እተኛለሁ እንጂ ብዙውን ጊዜ ተመስገን ነው ጤናዬን ደህና ነኝ”
እንግዳዋ ትንሽ ታመነታና፤
“እንደው የዚች የልጅዎ ነገር እንዴት ነው?”
እናትየው እንዳላወቀ ሆነው፤
“ምኗ?”
“እንዲያው አወፋፈሯ የጤና ነው ይላሉ?”
“አይ እንዲሁ የልጅ ገላ ሆኖ ባንዴ ወፍራ ነው እንጂ ምንም የለም”
“እንደዛስ ከሆነ ደህና” ትላለች እያመነታች፡፡
ሌላዋም ትመጣና የተለመደውን የጤናና የዝምድናዋን ያህል የእግዚሃር ሰላምታ ታቀርብና፤
“እንዲያው የዚችን ልጅ ነገር ዝም አላችሁ?”
“ምኑን” ይላሉ እናት ከመሰላቸት ጭምር፡፡
“ይሄ አወፋፈሯ አላማረኝም”
“አይ የልጅ ገላ ሆኖ ነው እንጂ ምንም የለም”
“እንደዛስ ከሆነ ደህና” ትላለች እያመነታች፡፡
ሌላዋም ትመጣና የተለመደውን የጤናና የዝምድናዋን ያህል የእግዚሃር ሰላምታ ታቀርብና፤
“እንዲያው የዚችን ልጅ ነገር ዝም አላችሁ?”
“ምኑን” ይላሉ እናት ከመሰላቸት ጭምር፡፡
“ይሄ አወፋፈሯ አላመረኝም”
“አይ የልጅ ገላ ሆኖ ነው እንጂ ምንም የለም”
እንዲህ በተከታታይ ሲመልሱ፣ ለመጣው ሁሉ የልጅ ገላ ነው ሲሉ፤ እዳር ሆነው የሚያስተውሉት

አባት በመጨረሻ ተነፈሱ፤
“እናንተ ይሄን ያህል ምን አስጨነቃችሁ?
የምግብም ከሆነ ሲቀንስ እናየዋለን፡፡
የልጅም ከሆነ ሲገፋ እናገኘዋለን!” አሉና ገላገሏቸው፡፡
*   *   *
“አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ” እንደማለት ነው፡፡ ማንኛውንም ነገር መደበቅ፣ መሸፋፈኑ አይጠቅምም - ሁሉንም ጊዜ ይገልጠዋልና፡፡ ግልፅነት ዛሬ ወቅታዊ ወረት (fashion) የሆነ ይመስላል፡፡ ስንቶች በአደባባይ እየተናገሩ ጓዳ ጓዳውን ግን የልባቸውን እንደሚሰሩ ቤቱ ይቁጠራቸው፡፡ They shout at most against the vices they themselves are guality of ይላሉ ፈረንጆች፡፡ “ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮህ” እንደምንለው መሆኑ ነው በአማርኛ። ስለመልካም አስተዳደር ያወራሉ፡፡ ግን መልካም አያስተዳድሩም፡፡ ስለፍትህ ያወራሉ ግና የህግን መርህ አይከተሉም፡፡ ስለዲሞክራሲ ይናገራሉ፡፡ ግን ዲሞክራት አይደሉም፡፡ ስለእኩልነት ያወራሉ ግን ወግነው ሰው ይበድላሉ፡፡ በእኩል አያኖሩም፡፡ ስለ እጅ ንፅህና ያወራሉ፡፡ ነገር ግን እነሱ ከሙስና የፀዱ አይደሉም፡፡ በአጠቃላይ ግልፅነትን እንደሽፋን ነው የሚጠቀሙበት፡፡ ከእነሱ ጋር መከራከር ከንቱ ነው፡፡ አንድም “ዜጋና ሹም ተሟግቶ ደንጊያና ቅል ተላግቶ” ነው፡፡ አንድም ደግሞ ማርክ ትዌይን እንዲህ ይለኛልና፡- “ከደደብ ሰዎች ጋር አትከራከር፡፡ ወደ እነሱ ደረጃ ያወርዱህና በልምዳቸው ያሸንፉሃል” የሚለን ለዚህ ነው፡፡ (Don’t argue with stupid people, they will drag you down to their level and then beat you with experience) በትክክለኛው ሜዳ ተጫወት እንደማለት ነው፡፡ ልህነት የሌለበት ግጭት ለአደጋ ይዳርጋል፡፡ “ተምረህ ተምረህ ደንቆሮ ሆነሃል” ይላሉ መንግሥቱ ለማ፡፡ በዚያው ጽሑፋቸው:-
“አንድ ዓለም ተሰጠ ለአዳም ለሄዋን
ለሁለቱ፤ ተረቱ እንደሚነግረን
…ምንስ ልጆቻቸው ቢረቡስ ቢራቡ
ጥቂቶቹ ጠግበው ብዙዎች ይራቡ
ጥቂቶች ሲያምራቸው ያንሱ ጦርነት
ብዙዎችም ይሂዱ ለመሞት ለዕልቂት!”
ይላሉ፡፡ ስለብዙሃኑ እናስብ ዘንድ ማስገንዘባቸው ነው፡፡ ጥቂቶች በሀብት የናጠጡበት ብዙሃን ይልሱት ይቀምሱት ያጡበት ሥርዓት መቼም በጅቶን አያውቅም፡፡ የናጠጡት የበደሉ የማይመስላቸው ሲሆን ደግሞ የባሰ መደናቆር ነው፡፡ ዳቦው ሳይኖር ለሰልፉ ሲሉ ብቻ ይሰለፉ ነበር እንደሚባሉት ምስኪን ሩሲያውያን እንዳንሆን መጠንቀቅም ብልህነት ነው፡፡ ለምርጫ ዝግጅት እየተደረገበት ባለበት ባሁኑ ሰዓት፣ ተቃዋሚዎች ለአየር ሰዓትና ለበጀት በሚታገሉበት ባሁኑ ሰዓት፣ አሸናፊው ፓርቲ የለየለት በሚመስልበት ባሁኑ ሰዓት፣ ተቃዋሚዎች ጠንካራ ሆነዋል የሚል ይሆነኝ ተብሎ የተቀናጀ መንፈስ ያለበት በሚመስልበት ባሁኑ ሰዓት፣ ተሳትፈናል ማለት እንደ ድል በተቆጠረበት ባሁኑ ሰዓት፣ “ከመጠምጠም መማር ይቅደም” ማለት በቀረበት ባሁኑ ሰዓት…ድል እንደ ዛፉ ብስል ፍሬ ስትርቅ፤ ቀበሮዋ ዘላ ዘላ ፍሬዋን መያዝና ማውረድ ሲያቅታት፤ “ለዛውም ሩቅ ናት፤ ደሞም መራራ ናት” አለች እንደተባለው እንዳይሆን ቆም
ብሎ ማሰብ ለሁላችንም ይበጀናል፡፡ ከዚህም ይሰውረን!!

- ቢል ጌትስ ለ16ኛ ጊዜ መሪነቱን ይዘዋል
- ቻይና በአንድ አመት 71 አዳዲስ ቢሊየነሮችን አፍርታለች
   በየአመቱ የዓለማችንን ቀዳሚ ቢሊየነሮች ዝርዝር የሚያወጣው ታዋቂው ፎርብስ መጽሄት ባሳለፍነው ሳምንት የ2015ን ምርጥ 500 የዓለማችን ቢሊየነሮችን ይፋ አድርጓል፡፡
ፎርብስ ለ29ኛ ጊዜ ይፋ ያደረገውን የዘንድሮ የዓለማችን ቢሊየነሮች ዝርዝር በቀዳሚነት የመሩት አሜሪካዊው የማይክሮ ሶፍት ኩባንያ መስራች ቢል ጌትስ ሲሆኑ፣ አጠቃላይ የሃብት መጠናቸውም 79.2 ቢሊዮን ዶላር ነው ተብሏል፡፡
ባለፈው አመት በነበራቸው ሃብት ላይ የ3 ቢሊዮን ዶላር ጭማሪ በማሳየት ለ16ኛ ጊዜ የዓለማችን ቁንጮ ባለጸጋ መሆናቸውን ያረጋገጡትን ቢል ጌትስ፣ በአመቱ 1.5 ቢሊዮን ዶላር ለበጎ ምግባር በስጦታ መልክ ቢለግሱም፣ ልግስናቸው አተረፈላቸው እንጂ አልቀነሰባቸውም፡፡
እሳቸውን ተከትለው የሁለተኛነትን ደረጃ የያዙት ደግሞ፣ 77.1 ቢሊዮን ዶላር ሃብት ያላቸው ሜክሲኳዊው የቴሌኮም ዘርፍ ባለጸጋ ካርሎስ ስሊም ሄሉ ናቸው፡፡
ሌላኛው ስመጥር አሜሪካዊ ባለሃብት ዋረን ቡፌት በ72.7 ቢሊዮን ዶላር ሃብት የአመቱ የዓለማችን ሶስተኛ ባለጸጋ ተብለዋል፡፡
አመቱ በአለማችን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ቢሊየነሮች የታዩበት እንደሆነ በሚያሳየው የዘንድሮው የፎርብስ ዝርዝር ውስጥ፣ እስከ 500ኛ ደረጃ የያዙ በድምሩ 1826 ቢሊየነሮች የተካተቱ ሲሆን፣ አለማችን ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ብቻ 181 ቢሊየነሮችን አግኝታለች፡፡

 በየዕለቱ የተወሰነ ስኒ ቡና አዘውትሮ መጠጣት ከደም ስር መዘጋት ችግር እንደሚታደግና በሰውነት ውስጥ ያለው የደም ዝውውር በአግባቡ እንዲከናወን በማድረግ ለልብ ህመም ከመጋለጥ እንደሚታደግ በጥናት መረጋገጡን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
የኮርያ ተመራማሪዎች በ25 ሺህ ወንዶች እና ሴቶች ላይ የሰራውን ጥናት ዋቢ በማድረግ ዘገባው እንዳለው፣ በየዕለቱ ከሶስት እስከ አምስት ስኒ ቡና አዘውትረው የሚጠጡ ሰዎች ለልብ ህመም የመጋለጥ እድላቸው አነስተኛ እንደሆነ ተረጋግጧል፡
ቡና በልብ ጤንነት ላይ የሚያሳድረውን ተጽእኖ በተመለከተ ከዚህ በፊት የተሰሩ ጥናቶች የተለያዩ ድምዳሜዎች ላይ እንደደረሱ ያስታወሰው ዘገባው፣ አንዳንዶቹ ቡና ለልብ ህመም ያጋልጣል ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ በአንጻሩ ጠቀሜታው የጎላ ነው ማለታቸውን ገልጧል፡፡
የኮርያ ተመራማሪዎች ያወጡት የጥናት ውጤት በቡና እና በልብ ጤንነት መካከል ያለውን ትክክለኛ ግንኙነት በተመለከተ ግልጽ መረጃ እንዳልሰጠ የጠቆመው ዘገባው፣ ጉዳዩ አነጋጋሪ መሆን መጀመሩን አስረድቷል፡፡
የብሪቲሽ የልብ ፋውንዴሽን ባልደረባ የሆኑት ቪክቶሪያ ቴለርም፣ የተመራማሪዎቹን የጥናት ውጤት ለማረጋገጥና በቡና እና በልብ ጤንነት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጥራት ተጨማሪ ምርምር ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ 

Monday, 16 March 2015 09:59

የአዲስ አድማስ ምስጋና

ባለፈው ሰኞ በብሔራዊ ቴአትር በተከበረው የአዲስ አድማስ ጋዜጣ የ15ኛ ዓመት በዓል ዝግጅት ላይ ግጥምና ሙዚቃ በማቅረብ፣ እንዲሁም ፕሮግራሙን ስፖንሰር በማድረግ ድጋፋችሁን ለሰጣችሁን ሁሉ ልባዊ ምስጋናችንን ልናቀርብ እንወዳለን፡፡
በዝግጅቱ ላይ በመታደም በዓላችንን ላደመቃችሁልን የአዲስ አድማስ ወዳጆችም ምስጋናችን የላቀ ነው፡፡
ዝግጅት ክፍሉና ማኔጅመንቱ

Monday, 16 March 2015 09:44

የፀሐፍት ጥግ

አዲስ ሃሳብ እንደ ህፃን ነው፡፡ ከመውለዱ ይልቅ መፀነሱ ይቀላል፡፡
ቴድ ኮይሲስ
አንዴ በአዲስ ሃሳብ የሰፋ አዕምሮ ወደቀድሞ ቦታው ፈፅሞ አይመለስም፡፡
ኦሊቨር ዌንዴል ሆልሜስ
ሁሉም ስኬቶችና በልፋት የተገኙ ሃብቶች መነሻቸው ሃሳብ ነው፡፡
ናፖሊዮን ሂል
ሁሉም ነገር የሚጀምረው ከሃሳብ ነው፡፡
ኧርል ናይቲንጌል
ሃሳብ ማግኘት ስፒል ላይ እንደመቀመጥ መሆን አለበት፡፡ አዘልሎ የሆነ ነገር ሊያሰራህ ይገባል፡፡
ኢ.ኤል ሲምፕሶን
ሁሉም ታላላቅ ሃሳቦች አወዛጋቢ ናቸው፤ ወይም የሆነ ጊዜ ላይ አወዛጋቢ ነበሩ፡፡
ጊልበርት ሴልዴስ
ሃሳቦች በእርግጥም በዓለም ላይ እጅግ አደገኛ መሣሪያዎች ናቸው፡፡
ዊልያም አርቪሌ ዳግላስ
ብዙ ሃሳቦች ከበቀሉበት አዕምሮ ይልቅ ወደ ሌላ አዕምሮ ሲዛወሩ የተሻለ ያድጋሉ፡፡
ኦሊቨር ዌንዴል ሆልሜስ
ሃሳብ ሳይለወጥ ከአንድ ቋንቋ ወደ ሌላ  አይተላለፍም፡፡
ሚጉልዲ ኡናሙኖ ይጁጉ
ሃሳቦች አሻፈረን ሲሉ ሰዎች ቃላትን ይፈጥራሉ፡፡
ማርቲን ኤች ፊሸር
ሁሉም ነገር ተብሏል፡፡ ግን ሁሉም ሰው አላለውም፡፡
ስታኒስሎው ሌስ

Monday, 16 March 2015 09:40

የውሃ ህክምና ፈውስ

የውሃ ህክምና (ሃይድሮቴራፒ) ጥንታውያን ግሪኮች፣ ግብፆችና ሮማውያን ከበሽታ ለመፈወስ  ሲጠቀሙበት የኖሩት ህክምና ሲሆን በቀላሉ ሊገኝ የሚችልም ነው፡፡ ውሃ በፈሳሽ፣ በበበረዶና በጋዝ መልኩ የተለያዩ ጠቀሜታዎችን ይሰጣል፡፡ ቀዝቃዛ፣ ሙቅና ፍል ውሃም አገልግሎቱ ለየቅል ነው፡፡
ውሃን በመጠጣት የሚገኝ ፈውስ
 ንፁህ ውሃን በመጠጣት ለህመም ፈውስ ማግኘት ከብዙ ሺህ ዓመታት በፊት ሲተገበር የቆየ ህክምና ነው። ውሃን መጠጣት የሰውነታችን በሽታ የመከላከል አቅምን                                                                                ያዳብራል፡፡ ውሃን በመጠጣት የኩላሊት፣ የጨጓራ፣ የፊኛ፣ የመገጣጠሚያ አካላት፣ አንጀትና ጣፊያ በሽታዎችን፣ ኪንታሮት፣ የሳንባ ምች፣ የተለያዩ ተላላፊ በሽታዎችን፣ የጡንቻና አጥንት ጤና ችግሮችን ማስወገድ ይቻላል፡፡
ሁልጊዜ ጠዋት ቁርስ ከመመገባችን በፊት ከአምስት ብርጭቆ ያላነሰ ውሃ ብንጠጣ ለተለያዩ ውስጣዊ የጤና ችግሮቻችን መፍትሄ እናገኛለን፡፡ ውሃ በተፈጥሮው የአሲድነት ፀባይ የሌለው በመሆኑ ለሰውነታችን ውስጣዊ ኡደት መቀላጠፍ የሚሰጠው ጠቀሜታ ከፍተኛ ነው። በአግባቡ ሳይሰለቀጡ ወደ አንጀታችን የሚገቡ ምግቦች በቀላሉ እንዲብላሉና በጥቅም ላይ እንዲውሉ በማድረግ ረገድ ውሃ የሚሰጠው ጠቀሜታ ከፍተኛ ነው፡፡
ውሃን በመነከር የሚገኝ ፈውስ
በጣም የቀዘቀዘ ውሃ ማይግሪን ለተባለው ራስ ምታት ፍቱን መድኀኒት ነው፡፡ ህመሙ በሚነሳበት ወቅት በጣም የቀዘቀዘ ውሃን ለአምስት ደቂቃዎች ያህል አናት ላይ በመያዝ ህመሙን ማስታገስ ይቻላል፡፡
ቀዝቃዛ ውሃ ለአለርጂ፣ ለጡንቻ መዛል፣ ለአዕምሮ መረበሽ (ለድብርት)፣ ለውጥረት፣ ለትኩሳትና ለሌሎችም በሽታዎች ፍቱን መድኀኒት ነው፡፡ ውሃ በሞቃትና በፍል መልኩ ጥቅም ላይ ሲውል ደግሞ ለመገጣጠሚያ ችግሮች፣ ለጉንፋን፣ ለብርድ፣ ለኢንፍሉዌንዛ ፍቱን መድኀኒት ነው። የሙቀት መጠኑ 750c የሆነ ውሃ ህመም በሚሰማን ቦታ ላይ ማፍሰስ (መነከር) ከህመም እፎይታን ሊያስገኝ ይችላል፡፡
ውሃን በበረዶ መልክ መጠቀም  
በመገጣጠሚያ አካላት ላይ በአደጋ (መውደቅ፣ መጋጨት) ለሚደርስ ጉዳትና በዚህ ሳቢያ በሰውነታችን ላይ ለሚከሰት እብጠት፣ የጡንቻ መሸማቀቅ ወይም ውልቃት በረዶ ፈጣን ፈውስን ያስገኛል፡፡ በረዶ በተጎዳው ሰውነታችን ላይ ሲደረግ ከህመም እፎይታን ከማግኘታችንም በሻገር እብጠቱን ለመቀነስ ያስችላል፡፡
ውሃን በመታጠን መፈወስ
ውሃን አፍልቶ መታጠን (በጋዝ መልኩ) ለጉንፋን፣ ለሳል፣ ለኢንፍሉዌንዛና ለጉሮሮ ህመሞች ፈጣን ፈውስ ይሰጣል፡፡  
የውሃ ህክምና ጥንቃቄዎች
በውሃ ህክምና በመታገዝ ፈውስ ለማግኘት በምንሞክር ወቅት ያሉብንን የጤና ችግሮች በሚያባብስ መልኩ እንዳይሆንብን ልንጠነቀቅ ይገባል፡፡ ቁስለት ባለባቸው የሰውነት አካላት ላይ ሙቅም ሆነ ቀዝቃዛ ውሃ መጠቀም የለብንም፡፡
እርጉዝ ሴቶች በውሃ ህክምና ከመጠቀማቸው በፊት ከሃኪማቸው ጋር መማከር ይኖርባቸዋል፡፡ በተለይ ህክምናውን በብልት (በማህፀን አካባቢ) ላሉ ችግሮች መጠቀም የሚፈልጉ እርጉዝ ሴቶች ህክምናውን ከመጀመራቸው በፊት ሃኪማቸውን ማማከር ይገባቸዋል፡፡

Monday, 16 March 2015 09:42

ካፌይን እና መዘዞቹ

ካፌይን አዕምሮን ለማነቃቃት የሚረዳና በተለይ በቡና፣ በሻይና በተለያዩ የለስላሣ መጠጦች ውስጥ በስፋት የሚገኝ ኬሚካል ነው፡፡ ካፌይን ከእነዚህ መጠጦች በተጨማሪ በቸኮሌቶች፣ በብስኩቶችና በተለያዩ የህመም ማስታገሻና የራስ ምታት መድሃኒቶች ውስጥ ይገኛል፡፡ ይህ ኬሚካል ሱስ የማስያዝ ባህርይው ከፍተኛ ነው፡፡ የተጠቀሱት መጠጦችና ምግቦች እንዲሁም መድሃኒቶች ካፌይን የመያዝ አቅማቸው እንደየሁኔታው የተለያየ ሲሆን በቡና ውስጥ የሚገኘው የካፌይን መጠን ከፍ ያለ ነው፡፡ አንድ ስኒ ቡና ከ100-150 ሚሊ ግራም ካፌይን በውስጡ ይይዛል፡፡ አንድ ሰው በቀን በአማካይ 80 ሚሊ ግራም ካፌይን ይወስዳል ተብሎ ይገመታል፡፡ ከመጠን ያለፈ ካፌይንን መጠቀም ለከፋ የጤና ችግር ይዳርጋል፡፡ በካፌይን ሳቢያ ከሚከሰቱ የጤና ችግሮች መካከል የካፌይን ስካር (ኢንቶክሲኬሽን)፣ ሱሰኝነት፣ የእንቅልፍ ማጣትና ጭንቀት ይጠቀሳሉ፡፡  
የካፌይን ስካር (ኢንቶክሲኬሽን)
ከ250 ሚሊ ግራም በላይ የሆነ ካፌይን ከተወሰደ የካፌይን ስካር ይጀምራል፡፡ የዚህ ችግር ምልክቶች ጭንቀት፣ መቅበጥበጥ፣ የህሊና መረበሽ፣ ማቅለሽለሽ፣ ማላብ፣ የሽንት መብዛት፣ እንቅልፍ ማጣት፣ እጅና እግርን የመውረር ስሜት መኖርና መነጫነጭ ናቸው፡፡ የካፌይን መጠኑ እየጨመረ ከሄደ እና 1000 ሚሊ ግራም ከደረሰ የአፍ መኮላተፍ፣ የሃሳብ መደነጋገርና የልብ ትርታ መዛባት ሊከተል ይችላል፡፡ መጠኑ ከዚህ እየጨመረ ከሄደም ድንገተኛ የልብ ምት መቆም (ሞትን) ሊያስከትል ይችላል፡፡
የካፌይን ሱሰኝነት
ራስ ምታት፣ ድብርት፣ ጭንቀት፣ ድካም፣ ማቅለሽለሽና ማስመለስ፣ እንቅልፍ እንቅልፍ የማለት ስሜት--- በካፌይን ሱሰኝነት ምክንያት የሚከሰቱ የጤና ችግሮች ናቸው፡፡
ይህ ችግር ካፌይኑ ከቀረ ከ10-12 ሰዓታት ውስጥ የሚጀምር ሲሆን ከጥቂት ቀናት ተደጋጋሚ ስሜት በኋላ ሊጠፋ የሚችል ነው፡፡
የእንቅልፍ ማጣትና ጭንቀት
መረበሽ፣ መነጫነጭ፣ በአንድ ቦታ ተረጋግቶ አለመቀመጥ፣ መርበትበትና መጨነቅ በካፌይን ሰበብ ከሚከሰቱ የጤና ችግሮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ካፌይን ለእንቅልፍ ማጣት ሰበብ ከመሆኑም በተጨማሪ  ለድብርት፣ ለጭንቀትና ለውጥረት ዋንኛ ምክንያትም ነው፡፡
የመፍትሔ እርምጃዎች
የሚወሰደውን የካፌይን መጠን በአንድ ጊዜ ለመቀነስ መሞከር አይመከርም፡፡ ይልቁንም ዕለት በዕለት ቀስ እያሉ የሚወስዱትን የካፌይን መጠን በመቀነስ በሂደትም ማቆም በካፌይን ሰበብ ከሚደርሱ የጤና ችግሮች ሊታደገን ይችላል። ካፌይን የሌለባቸውን ምግቦችና መጠጦች ለይቶ በማወቅ እነሱ ላይ ትኩረት በማድረግ መጠቀም፣ ራስን በሌሎች ነገሮች ለማዝናናት መሞከርና ውሃን አብዝቶ መጠጣት በካፌይን ሳቢያ የሚከሰቱትን የጤና ችግሮች ለማስወገድ ይረዳል፡፡

ኢህአፓም “አሲምባ”ን ማስጎብኘት ይችላል----

  ልጅ ያሬድ የተባለው ታዋቂ ኮሜዲያን ሰሞኑን በዋሽንግተን ሆቴል (የአዲስ አበባው ነው!) ባቀረበው የኮሜዲ ምሽት ላይ የታደመችው የሥራ ባልደረባዬ ሰምታ ካጣጣመቻቸው ቀልዶች ውስጥ  ጥቂቶቹን ስለነገረችኝ እኔም ለናንተ ላጋራችሁ፡፡ (“sharing is caring” አሉ!)
ወደ ልጅ ያሬድ ቀልድ፡- አንድ የሆነ ሰፈር ነው አለ፡፡  ሌላው ጋ 3 ብር የሚሸጠውን አንድ እንጀራ 4 ብር ነው የሚሸጡት ---- ለምንድን ነው እዚህ ሰፈር  4 ብር የሚሸጠው ሲል ይጠይቃቸዋል፡፡ ምን ቢሉት ጥሩ ነው --- እኛ ሰፈር ውሃ ስለሌለች ሊጡን በሃይላንድ ውሃ ነው የምናቦካው፡፡ (የጨረሰች  ቀልድ!)  
ባለፈው ሳምንት ትዝ ይላችሁ እንደሆነ ስለ ህወሃት 40ኛ ዓመት በዓል ሳወጋችሁ አንዳንድ ተቃዋሚዎች፤ ኢህአዴግ በዓሉን ለምርጫ ቅስቀሳነት እየተጠቀመበት ነው የሚል ክስ መሰንዘራቸውን ጠቅሼ ነበር (ነገርዬው ባይሆን ለወቀሳ እንጂ ለክስ እንኳን አይበቃም!) የሆኖ ሆኖ ---- ተቃዋሚዎች ለምን እንዲህ ያለ ወቀሳ ሰነዘሩ ብዬ ሳሰላስል ሁለት መላ ምቶች ብልጭ አሉልኝ፡፡ አንደኛው፤ ህወሃት ለምን ለበዓሉ አልጠራንም የሚል የአበሻ ቅያሜ ቢጤ ይመስለኛል፡፡ ለነገሩ አይፈረድባቸውም፡፡ ለምን መሰላችሁ ----- ሱዳኖችንና የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲን በሰበብ አስባቡ እየጋበዙ ለአገር ቤት ተቃዋሚ ጀርባ መስጠት ያናድዳላ፡፡ (ቀላል ያጨሳል!)  
በነገራችሁ ላይ በእንዲህ ያሉ መልካም አጋጣሚዎች (የህወሃት 40ኛ ዓመትን ማለቴ ነው!) ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የዘለቀውን የፖለቲካ ኩርፍያ (የኩርፍያ ፖለቲካም ያስኬዳል!) ለመስበር መትጋት እኮ ብልህነት ነው፡፡ (አረ ብልጥነትም ጭምር!) ፖለቲከኞቻችን ሌላው ቢቀር … ለአዲሱ  ትውልድ የሚያስረክቡትን አገር ማሰብ አለባቸው፡፡ (ኩርፍያ የሞላት አገር ማን ይረከባል!)
እናላችሁ----በተለይ የመንግስትን ስልጣን የያዘው ኢህአዴግ ተነሳሽነቱን መውሰድ አለበት ባይ ነኝ፡፡    (ከተቃዋሚም ቢገኝ አንጠላም!) አያችሁ ቢገባን እኮ---ለሰላምና ለፍቅር መሸነፍ ከማሸነፍ እኩል ነው፡፡ (ኧረ ኩርፊያው ይሰበር!) አሁንስ እኔ ለእነሱ ደከመኝ… (ስፖንሰር ከተገኘ “ኩርፊያው ይሰበር” የሚል የ6 ወር አገራዊ ንቅናቄ ለመጀመር አስቤያለሁ!)
ሁለተኛውን መላ ምት እንኳ ሳምንትም ጠቀስ አድርጌዋለሁ (የአርቲስቶች ደደቢትን መጎብኘት ማለቴ ነው!) ዛሬ ግን ችግሩን ብቻ ሳይሆን መፍትሄውንም ይዤአለሁ፡፡ ባለፈው ጠቀስ እንዳደረግሁላችሁ ተቃዋሚዎች በዚህ ነገር ደስ የተሰኙ አይመስሉም፡፡ ለዚህ ነው ኢህአዴግ በዓሉን ለምርጫ ቅስቀሳ ተጠቀመበት የሚል ወቀሳ የመጣው፡፡ (ሁሉ ነገር በአስተማማኝ ግምት ላይ የተመሰረተ ነው!)
ለነገሩ እስቲ ራሳችሁን በተቃዋሚዎች ቦታ አድርጋችሁ አስቡት፡፡ (ለአፍታ የእነሱን ጭንቅላት ልዋስ!) እናላችሁ--ለምሳሌ አርቲስቶችን ደደቢት ድረስ ወስዶ ማስጎብኘት ለምን አስፈለገ? (ያውም በምርጫው 11ኛ ሰዓት ላይ!) ግን እኮ ጥያቄው መቅረብ የነበረበት ለራሱ ለህወሃት ነው! የጉብኝቱ ዓላማ እንደተባለው ታሪክን ለትውልድ ማስተላለፍ ነው? (እንዴት አሁን ትዝ አላቸው?) ወይስ በምስኪንነት ሆድ አባብቶ አሊያም በጀግንነት ቀልብ ማርኮ የአርቲስቶችን ድምፅ ለመግዛት ነው? እኒህ ሁሉ ጥያቄዎችና መላምቶች  የእኔ አይደሉም … እኔ ለእነሱ የመታሁት መላ እንጂ!! (ራሴን በተቃዋሚዎች ጫማ ውስጥ አስገብቼ ማለት ነው!)
እናም ማንም ተቃዋሚ የሆነ (ያውም ደግሞ ያኮረፈ!) ከላይ ከቀረቡት ውስጥ ልቡ ወደ ሁለተኛው ጥያቄና መላ ምት እንደሚያደላ ሳይታለም የተፈታ ነው!! እናም ለዚህ ይሆናል የህወሃትን 40ኛ ዓመት  ለምርጫ ቅስቀሳ ተጠቀሙበት የሚለው ክስ (ይቅርታ ወቀሳ!) የመጣው፡፡ አሁን ወደ መፍትሄው እንግባ፡፡ የእኔ ሃሳብ ምን መሰላችሁ? ተቃዋሚዎችም ልክ እንደ ህወሃት የየራሳቸውን “ደደቢት” ለአርቲስቶች እንዲያስጎበኙ ዕድል መስጠት! (ከከተማ ሳይወጡ ደደቢት!) ግን ምን መሰላችሁ? ምንም እንኳን ተቃዋሚዎች እንደ ህወሃት በረሃ ገብተው ባይዋጉም አልታገሉም ማለት ግን አይደለም፡፡ የሰላማዊ ሰልፍ ዕውቅና ማግኘት፣ ህዝባዊ ስብሰባ ለማካሄድ አዳራሽ ወይም ሆቴል መከራየት፣ በየክልሉ ካሉ ትናንሽ የወረዳ ንጉሶች ጋር መወዛገብ፣ ሰላማዊ ፈቃዱ ህገወጥ ነው ከሚል የጸጥታ ኃይል ጋር መጋፈጥ (ዱላና ድብደባን ያካትታል!) ------ እኒህ ሁሉ የትግሉ አካል ናቸው፡፡
 ሌሎችም የትግል ቦታዎች አሉ፡፡ ለምሳሌ---ተቃዋሚዎች ፓርቲያቸውን ለመመስረት ሃሳብ የጠነሰሱበት ሥፍራ፣ በኢህአዴግ ካድሬ ተዋከብን የሚሉበት ቦታ፣በየጊዜው እነሱ ወይም ጓዶቻቸው የታሰሩበት፣(ቃሊቲ፣ዝዋይ፣ማዕከላዊ--ወዘተ) እነዚህ ሁሉ የእነሱ የትግል ቦታዎች ናቸው፡፡ አብዛኞቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚጋሩት አንድ የድል ቦታም አላቸው -የህዝብ ማዕበልን የሚያስታውሳቸው፡፡ መስቀል አደባባይ!! (የ97 ምርጫን ልብ ይሏል!) አያችሁ----ተቃዋሚዎችም ለአርቲስቶች ሊያስጎበኙት የሚችሉት ከበቂ በላይ የትግል ቦታና ታሪክ  አሏቸው፡፡ (የየራሳቸው ደደቢት እንደማለት!) በነገራችሁ ላይ የትጥቅ ትግሉን ያሸነፈው ኢህአፓ ቢሆን ኖሮ---- አርቲስቶቹ የሚጎበኙት ደደቢትን ሳይሆን አሲምባን ይሆን ነበር፡፡
 እናላችሁ … ተቃዋሚዎች አርቲስቶችን ሰብስበው የየራሳቸውን “ደደቢት” ቢያስጎበኙ ኩርፊያውን ለማርገብ የሚያግዝ ይመስለኛል፡፡ (አርቲስቶች የህዝብ ሃብት ናቸው ብዬ እኮ ነው!) በነገራችሁ … ላይ የህዝብ ሃብት ያልሆነ ነገር እኮ ፈልጋችሁ አታገኙም! ለምሳሌ መሬት የህዝብ ሃብት ነው (ይቅርታ እና የመንግስት!)፣ ቲቪና ሬዲዮ ጣቢያም የህዝብ ሃብት ነው፡፡ የኢህአዴግ ኢዶውመንቶች ራሳቸው - የህዝብ ሃብት ናቸው፡፡ የሥልጣን ባለቤት ማነው? ህዝብ ነው!! የመንግስት ሹማምንት የማን አገልጋይ ናቸው? የህዝብ!! ግን እኮ አርቲስቶች ሃብታቸውን ሲጠየቁ----ሃብታችን ህዝብ ነው ይላሉ፡፡ (ከምራቸው እንዳይሆን!)