Administrator

Administrator

ጠ/ሚ ኃይለማርያም የግብጽን መንግስት አመስግነዋል
   በሊቢያ ታግተው የቆዩና የግብጽ መንግስት ባደረገው ድጋፍ የተለቀቁ 27 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ትናንት ማለዳ አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖምና ሌሎች ባለስልጣናት በቦሌ አለማቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ በመገኘት ለስደተኞቹ አቀባበል አድርገዋል፡፡በግብጽ ወታደራዊ ሃይል ድጋፍ ከእገታ ተለቀዋል የተባሉት እነዚሁ ስደተኞች ከትናንት በስቲያ ካይሮ አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ ሲደርሱ በአገሪቱ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ አቀባበል እንደተደረገላቸው  ሮይተርስ፣ ፕሬዚደንቱ፤ “ስደተኞቹ በሊቢያ የታጠቁ ሃይሎች ታግተው በአስከፊ ሁኔታ ውስጥ የቆዩ ናቸው” ማለታቸውን የአገሪቱ የዜና ተቋም “ሜና መዘገቡ ታውቋል፡፡የዜና ተቋሙ ስለስደተኞቹ ማንነት፣ ስለተለቀቁበት ሁኔታ እና ታግተው በቆዩበት ወቅት ስለነበረው ሁኔታ ግልጽ መረጃ ባይሰጥም፣ ሮይተርስ በበኩሉ፤ የሊቢያ ባለስልጣናት ከግብጽ የስለላ ተቋማት ያገኙትን መረጃ በመጠቀም በዴርና እና ሚስራታ ከተሞች በታጠቁ ሃይሎች ታግተው የነበሩትን እነዚህን ስደተኞች እንዳስለቀቁ መረጃ ደርሶኛል ብሏል፡፡ ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ
አንድ የግብፅ ዲፕሎማት በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያውያኑ ከሊቢያ የወጡት በወታደራዊ ሃይል ድጋፍ ሳይሆን የግብፅ መንግስት ባደረገው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንደሆነ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ከኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች አንዱ በበኩሉ፣ የሊቢያ መንግስት ከነበርንበት ቦታ ወደ አገሪቱ የጸረ ህገወጥ ስደት አካል ከወሰደን በኋላ፣ የግብጽ መንግስት ወደ ካይሮ አምጥቶናል ሲል መናገሩን ዘገባው አስረድቷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በበኩላቸው፤ የስደተኞቹን መለቀቅ ተከትሎ ከትናንት በስቲያ ከግብጹ ፕሬዚዳንት አል ሲሲ ጋር በስልክ ባደረጉት ንግግር፣ ግብጽ ኢትዮጵያውያኑን ለማስለቀቅ ላደረገችው አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን ገልጸው፤ መሰል ጥረቶች በግብጽ፣ በአረቡ አለምና በአፍሪካ አገራት መረጋጋትን ለመፍጠር አስተዋጽኦ ያበረክታሉ ማለታቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ባወጡት መረጃ እንዳሉት፤ በሊቢያ ከሚገኙት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች መካከል የመጀመሪያዎቹ 11 ስደተኞች ባለፈው ረቡዕ በካርቱም በኩል ወደ አዲስ አበባ መግባታቸውን ጠቁመዋል፡፡

Saturday, 02 May 2015 12:48

የተፈጥሮ እውነታዎች

ብብታችን በአንድ ስኩዌር ኢንች ክፍሉ ብቻ እስከ 516ሺ የሚጠጉ ባክቴሪያዎች አሉበት፡፡
አንድ ሰው በህይወት ዘመኑ በአማካይ 18 ኪሎ ግራም የሚሆን የቆዳ ግፋፊ ያስወግዳል።
በየቀኑ 100 ቢሊዮን ቀይ የደም ሴሎች በሰውነታችን ውስጥ ይፈጠራሉ፡፡
የወንድ ልጅ የዘር ፍሬ በየቀኑ 10 ሚሊዮን አዳዲስ ስፐርሞችን ያመርታል፡፡ ከጠቅላላ የሰውነት ክብደቱም 0.08 ኪ.ግ ይመዝናል፡፡
የሴቶች የእንቁላል ማኮሪያ (Ovary) በአንዴ ግማሽ ሚሊዮን የሚሆኑ የእንቁላል ሴሎች መያዝ ይችላል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 400 የሚሆኑት ብቻ የማፍራት ዕድልን ያገኛሉ፡፡
ልባችን በቀን ውስጥ 100ሺህ ጊዜ ይመታል፡፡
በሰውነታችን ውስጥ ካሉ ጡንቻዎች በሙሉ የምላስ ጡንቻዎቻችን በጣም ጠንካሮች ናቸው፡፡
ልክ እንደ ጣት አሻራ፣  የእያንዳንዱ ሰው የምላስ አሻራም የተለየ ነው፡፡
በጭንቅላታችን ላይ በአማካይ 100ሺህ ፀጉሮች ይገኛሉ፡፡ እያንዳንዱ ፀጉር በየዓመት 5 ኢንች ይረዝማል፡፡

 የታሪክ አፃፃፉ ምን ይመስላል? ደራሲው ታሪኩ የተፈፀመበትን ዘመን የተረዳው እንዴት ነው? መረጃዎቹን ከፖለቲካ፣ ከኢኮኖሚ፣ ከባህል… አንፃር እንዴት ነው የመዘነው? የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ሚዛናዊነት መመዘን ይቻላል፡፡ ማነው መዛኙ ለሚለው ፀሐፊያንም አንባቢያንም ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ታሪከ ፀሐፊ ፖለቲከኛ ሊሆን ይችላል። አንድን ታሪክ ሲጽፍ ምክንያታዊ መሆን ከቻለ ሚዛናዊ ታሪክ ፀሐፊ ነው ሊባል ይችላ

     ላለፉት 10 ዓመታት በየሁለት ሳምንቱ የመፃህፍት ላይ ውይይት ሲያካሂድ የቆየው ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ፤ በገጠመው ውስጣዊ ችግር ምክንያት የተለመደውን መድረክ ማዘጋጀት ካቋረጠ ስድስት ወራት ሆኖታል፡፡ ይህንን ክፍተት ለመሙላት የጀርመን ባህል ማዕከል፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፃሕፍት ኤጀንሲ እና እናት ማስታወቂያ ድርጅት በጋራ በመሆን በወር አንዴ የመፃሕፍት ላይ ውይይት እንደሚያካሂዱ የተገለፀ ሲሆን የመጀመሪያው ዝግጅትም ባለፈው እሁድ በወመዘክር አዳራሽ ተከናውኗል፡፡
ለውይይት የተመረጠው “የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ መንግሥት” በሚል ርዕስ በአምባሳደር ዘውዴ ረታ ተጽፎ ባለፉት ሁለት ዓመታት ሦስት ጊዜ ለመታተም የበቃው መጽሐፍ ሲሆን፤ ለውይይት የመነሻ ሀሳብ ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት አቶ አበባው አያሌው ነበሩ፡፡ የመጽሐፉ ደራሲ አምባሳደር ዘውዴ ረታ ከአገር ውጭ በመሆናቸው በዕለቱ ሊገኙ አልቻሉም፡፡
“የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ መንግሥት ዘመን በአገሪቱ በርካታ ታሪኮች የተከናወኑበት በመሆኑ ልዩ ወቅት ነበር፡፡ ዘመናዊ ለውጥ በአፄ ቴዎድሮስ ዘመን ተጀመረ የሚሉ አሉ፤ በተግባር የታየው ግን በአፄ ኃይለሥለሴ ጊዜ ነው፡፡ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ አወዛጋቢ ንጉሥ ነበሩ፡፡ የሚያደንቋቸው አሉ፡፡ በኋላ በአገሪቱ ለታየው ምስቅልቅል ትልቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል ብለው የሚከሷቸውም አሉ፡፡ በዚህ ዙሪያ ብዙ የተፃፈ ቢሆንም ወደፊትም ብዙ የሚፃፍበት ይመስላል፡፡ አብዮተኞቹ ታሪክ ፀሐፊዎች አፄ ኃይለሥላሴን ሲያጠለሹ፤ በንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ውስጥ ያገለገሉ ታሪክ ፀሐፊዎች ያሞግሷቸዋል፡፡ ሦስተኛው ዓይነት ታሪክ ፀሐፊዎች የውጭ አገር ሰዎች ሲሆኑ የተደረገውን ሐቅ ከማስቀመጥ ውጭ ነገሩ ጥሩ ነው፣ መጥፎ ነው ብለው ትንታኔ ውስጥ አይገቡም፡፡ ከዚህ አንፃር እነዚህ ሚዛናዊ ሆነው ይታያሉ።”
በዚህ መልኩ ገለፃ የጀመሩት አቶ አበባው አያሌው፤ የአምባሳደር ዘውዴ ረታን መጽሐፍ የቃኙት በሰባት መመዘኛዎች እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ደራሲው ለጉዳዩ ያላቸው ቅርበት ምን ይመስላል? የመረጃ ምንጫቸው ምን ነበር? መረጃዎቹስ በመጽሐፉ ውስጥ በምን ያህል ተንፀባርቀዋል? ሚዛናዊነቱ ምን ይመስላል? በመጽሐፉ የተገለፀው ዘመን ታሪክ ምን ያህል ሙሉ ሆኖ ቀርቧል? የታሪክ ሃተታውና የቋንቋ አጠቃቀሙ ምን ይመስላል? መጽሐፉ ምን አዲስ ነገር አሳወቀን?
እነዚህን ጥያቄዎች አንስተው ምላሽ በመስጠት ማብራራት የቀጠሉት የዩኒቨርሲቲው ምሁር፤ የአገርም ሆነ የግለሰቦች ታሪክ በአንድ ሰው ብቻ ተጽፎ እንደማያበቃ ጠቁመው በአፄ ኃይለሥላሴ ዙሪያ 56 ያህል መፃሕፍት መታተማቸውን ገልፀዋል፡፡
ደራሲው ለፃፉበት ርዕሰ ጉዳይ ቅርበት ነበራቸው፡፡ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ሰራተኛ፣ የቤተ መንግሥት ጋዜጠኛና በኋላም የማስታወቂያ ሚኒስቴር ረዳት ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉ  ከመሆኑም ባሻገር በአምባሳደርነትም ተሹመው መስራታቸው የቃል፣ የሰነድና የፎቶግራፍ መረጃዎችን ለማግኘት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳደረገላቸው አቶ አበባው ገልፀዋል፡፡
አምባሳደር ዘውዴ ረታ በአገር ውስጥና በውጭም መረጃዎችን ማግኘታቸው ብቻ ሳይሆን ያገኙትን በጥንቃቄ ማስቀመጥ በመቻላቸው “የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ መንግሥት” በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ በሚገባ ተጠቅመበውበታል፡፡ በአገር ውስጥ ከጽሕፈት ሚኒስቴር ሰነዶችን በቀጥታ አግኝተዋል። በዘመኑ ታላላቅ ባለስልጣናት ከነበሩት መኮንን ሀብተወልድ፣ ወልደጊዮርጊስ ወልደዮሐንስ፣ ይልማ ደሬሳ ከመሳሰሉት ቤተሰቦችም ብዙ መረጃ ሳያኙ አልቀሩም ተብሏል፡፡
“የቃል መረጃም በብዛት ተጠቅመዋል፡፡ ይህ በጥንቃቄ መታየት ያለበት ነው፡፡ ምስክርነቱን የሰጠው ሰው ማነው? የፖለቲካ አመለካከቱ፣ ዕውቀቱ … መጠየቅና መጣራት አለበት። የቃል ምስክርነት እውነታነቱ ሌላ ማመሳከሪያ ካልተገኘለት ለዘመን ፍርድ ክፍት ተደርጎ የሚተው ነው” ያሉት አቶ አበባው፤ በተመሳሳይ በዚህ መልኩ ጥያቄ አስነስቶ እስካሁንም እያነጋገረ  ነው በማለት “ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ” የተሰኘውን መጽሐፍ በምሳሌነት ጠቅሰዋል፡፡
የቃልና የሰነድ መረጃዎች በስፋት ጥቅም ላይ ውለውበታል የተባለው “የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ መንግሥት” መጽሐፍ፤ በማጣቀሻነት የተጠቀማቸው መፃሕፍት ቁጥር ትንሽ እንደሆኑና የመረጃ አገላለጽ ችግር እንደሚታይበት ተጠቁሟል፡፡ የመረጃ ምንጩ ሰውም ይሁን ሰነድ የት እንደሚገኝ መገለጽ አለበት። በመጽሐፉ ላይ አባሪ ማኖር ገጽ ያበዛል ተብሎ ከተፈራ መረጃዎች ከየትኛው ሰነድ እንደተወሰዱ በግርጌ ማስታወሻ ቢገለጽ ጥሩ ነበር፡፡ ምክንያቱም ደራሲው ያገኘውን ምንጭ አንባቢያንም እንዲደርሱበት ያግዛል ተብሏል፡፡ መጽሐፉ በርካታ ፎቶግራፎችን ቢይዝም “የኤርትራ ጉዳይ” ከሚለው መጽሐፋቸው ጋር ሲነፃፀር ይኸኛው መጽሐፍ የያዛቸው ፎቶግራፎች ቁጥራቸው ማነሱም ተገልጿል፡፡
“የታሪክ ጠላት ፖለቲካ ነው፡፡ ፖለቲካ ታሪክን ወደራሱ ፍላጎት ይዞት ይሄዳል፡፡ ከዚህ አንፃር አምባሳደር ዘውዴ ረታ በመጽሐፋቸው ምን ያህል ሚዛናዊ መሆን ችለዋል?” ያሉት ምሁሩ፤ ደራሲው በአንዳንድ ቦታ ኃይለሥላሴን ከብዙ ነገሮች ነፃ ሲያደርጓቸው ይታያል፡፡ የታሪክ ፀሐፊ አይበይንም። ፍርዱን ለአንባቢያን ነው መተው ያለበት፡፡ እንዲህም ሆኖ መጽሐፉ ባነሳው ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ በአገር ውስጥ የነበረውን ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፍ ሁኔታና ተጽዕኖንም እያመሳከረ ታሪኩን ሚዛናዊ ለማድረግ ሞክሯል ተብሏል፡፡
ከ1923-1948 ዓ.ም ያለውን ዘመን ማዕከል አድርጎ የተዘጋጀው የአምባሳደር ዘውዴ ረታ መጽሐፍ፤ የ25 ዓመታቱን ታሪክ በምን ያህል መጠን ሙሉ አድርጎ አቀረበ? ለሚለውም ጥያቄ የአምስቱ ዓመት የአርበኞች ተጋድሎ ታሪክ አለመፃፉ (ደራሲውም ይህንን በመጽሐፉ መግቢያ አንስተውታል)፤ አፄ ኃይሥላሴ በስደት በእንግሊዝ በነበሩበት ጊዜ አኗኗራቸው ምን ይመስል እንደነበር አለመገለፁ፤ ከድል በኋላ አርበኞች፣ ባንዳዎች፣ ስደተኞች፣ ምሁራን በውስጣቸው የነበረው ትግል ምን እንደነበር አለመብራራቱ፤ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት አውሮፓውያን ለስደተኛ መንግሥታት ዕውቅና ሲሰጡ ኢትዮጵያ ዕድሉ ስለመነፈጓ በስፋት አለመፃፉ … የመሳሰሉት የመጽሐፉን ሙሉእነት ጥያቄ ውስጥ ያስገባዋል ብለዋል - አቶ አበባው፡፡
መጽሐፉ በታሪክ አተራረክና በቋንቋ አጠቃቀሙ የተሳካለት መሆኑን የመሰከሩት አቶ አበባው  መጽሐፉ ምን አዲስ ነገር አሳየን? ለሚለውም “ትኩረት ያልተሰጣቸው ጥቃቅን ነገሮችን አሳይቶናል፡፡ ማን ምን ብሎ ጠይቆ፤ ማን ምን ብሎ መለሰ የሚለውን ሁሉ እናይበታለን። የ1923ቱ ሕገ መንግሥት ሊፀድቅ በሂደት ላይ እያለ በዘመኑ ምሁራንና ባለስልጣናት መሐል የተደረገውን ሰፊ ክርክር አቅርቦልናል (የሞኝ ዘመን መጽሐፍ ሆኖ ነው እንጂ በህገ መንግሥቱ ዙሪያ የቀረበው ርዕስ ብቻ አንድ መጽሐፍ ይወጣው ነበር)፡፡ በሊግ ኦፍ ኔሽን የተደረገውን ክርክር በተመለከተ በአገር ውስጥና በውጭ አገራት ሰዎች ዘንድ ያለው አመለካከት ምን ይመስል እንደነበር በስፋት ገልጿል፡፡ ስለ መኮንን ሀብተወልድ፣ ወልደጊዮርጊስ ወልደዮሐንስ፣ ይልማ ደሬሳ ካሁን ቀደም የማናውቃቸውን አዳዲስ መረጃዎች ሰጥቶናል፡፡ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዲፕሎማሲያዊ ክህሎት ምን ያህል ውጤታማ (በባሩድ ሳይታጠኑ በንግግርና ውይይት በማሳመን) መሆናቸውን አይተንበታል፡፡ መጨረሻ ላይም የንጉሠ ነገሥቱ ምኞት፣ የምሁራኑ ፍላጎትና የባለሥልጣናቱ መሻት መለያየቱንና ሁሉም ብቻውን መቆሙን አመላክቶናል፡፡” ብለዋል፡፡
አቶ አበባው መጽሐፉን አስቃኝተው ከጨረሱ በኋላ ከተሰብሳቢዎች የተለያዩ አስተያየትና ጥያቄዎች ቀርበዋል፡፡ አምባሳደር ዘውዴ ረታ አንዳንዴ በሚጽፉት ስሜታዊ ገለፃ ፀሐፊ ትዕዛዛትን ይመስላሉ፡፡ በዚህ ላይ የምትለን ነገር አለ? ደራሲው የታሪክ ሰው አይደሉም፤ አምባሳደር (ዲፕሎማት) ናቸው የሚሉ ክርክሮች አሉ፡፡ ማረፊያው የቱ ነው? ታሪክን ፖለቲካ ስለሚጎትተው ታሪክ ፀሐፊ ሚዛናዊ እንዲሆን እንዴት ይጠበቃል? ታሪክ ፀሐፊ ይመዘናል ከተባለ፤ መዛኙ ማነው? ታሪክ ፀሐፊው ላይ የቀረበው አድናቆትና ነቀፌታን ለመዳኘት ዲስፕሊኑ ከየት ነው የሚገኘው?
ለቀረበላቸው ጥያቄዎች መልስ የሰጡት አቶ አበባው አያሌው፤ “የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ መንግሥት” የተሰኘው መጽሐፍ የንጉሡ ታሪክ ላይ ትኩረት ቢያደርግም አምባሳደር ዘውዴ ረታ ጸሐፊ ትዕዛዝ አይደሉም ብለዋል፡፡ በተፈጥሮም የተገኘ ይሁን በልምድ አተራረክና አቀራረቡ ጥሩ የሆነ መጽሐፍ አቅርበውልናል፡፡ ታሪክን ማንም ይጽፈዋል። ፀሐፊዎቹም ህዝባዊና ሙያዊ ተብለው በሁለት ይከፈላሉ፡፡ ተነባቢነት ያላቸው አብዛኞቹ የታሪክ መፃሕፍት የተፃፉት በጋዜጠኞች ነው፡፡ አምባሳደር ዘውዴ ረታ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ስለሰሩ የታሪክ መጽሐፉ ለመፃፍ ችለዋል፡፡
“በታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ሚዛናዊነት መኖሩን የምናረጋግጠው ደራሲው ምን መረጃ አገኘ? መረጃውን እንዴት አቀረበው? አተረጓጎሙስ እንዴት ነው? የሚሉትን ጥያቄዎችን በማንሳት፤ ጥያቄዎቹ የሚተነተኑበትን ሂደት ተከትሎ በመመርመር ነው። የታሪክ አፃፃፉ ምን ይመስላል? ደራሲው ታሪኩ የተፈፀመበትን ዘመን የተረዳው እንዴት ነው? መረጃዎቹን ከፖለቲካ፣ ከኢኮኖሚ፣ ከባህል… አንፃር እንዴት ነው የመዘነው? የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ሚዛናዊነት መመዘን ይቻላል፡፡ ማነው መዛኙ ለሚለው ፀሐፊያንም አንባቢያንም ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ታሪከ ፀሐፊ ፖለቲከኛ ሊሆን ይችላል። አንድን ታሪክ ሲጽፍ ምክንያታዊ መሆን ከቻለ ሚዛናዊ ታሪክ ፀሐፊ ነው ሊባል ይችላል” በማለት አቶ አበባው ማብራሪያቸውን ቋጭተዋል፡፡      

ከወር በፊት በጋለሪያ ቶሞካ በተከፈተው “ውስጣዊ ግለትና እንፋሎት” የተሰኘ የስዕል ትርዒት ላይ ነገ ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ በቶሞካ ውይይት እንደሚካሄድ ዳይሬክተሩ ጋዜጠኛ ነብዩ ግርማ ገልጿል፡፡ የወጣት አሸናፊ ማስቲካ ስራዎችን በ14ኛው ዙር የስዕል ትርዒቱ ለእይታ ያቀረበው ጋለሪው፤ ሳር ቤት ካናዳ ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኘው ጋለሪያ ቶሞካ በርካታ የስዕል አፍቃሪያን፣ ሰዓሊያን፣ ጋዜጠኞችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በሚገኙበት ከ35 በላይ በሚሆኑ የወጣቱ ሰዓሊ ስራዎች፣ የአሳሳል ዘይቤና በስዕል ፍልስፍናው ዙሪያ ሰፊ ውይይት እንደሚካሄድ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Saturday, 02 May 2015 12:35

የሰዓሊያን ጥግ

  ፎቶግራፍን አታነሳውም፤ ትፈጥረዋለህ እንጂ፡፡         ቶማስ ሜርቶን
ለማየት ስል ዓይኖቼን እጨፍናለሁ፡፡
ፖል ጋውጉይን
እንደ ስሜቶች ሁሉ ቀለማትም የህይወት ነፀብራቅ ናቸው፡፡     ጃኒሴ ግሊናዌይ
ቀለማትና እኔ አንድ ነን፡፡ ሰዓሊ ነኝ፡፡
ፖል ክሊ
ሰዓሊ ጥሩ ነገር የሚሰራው እየሰራ ያለውን የማያውቅ ከሆነ ብቻ ነው፡፡
ኤድጋር ዴጋስ
የሰዓሊ ሥራ ሁልጊዜም ምስጢሩን ጥልቅ ማድረግ ነው፡፡
ፍራንሲስ ቤከን
ለመሳል ዓይኖችህን መጨፈንና ማዜም አለብህ፡፡
ፓብሎ ፒካሶ
በስዕልና በግጥም ሰስብዕና ሁሉም ነገር ነው፡
ገተ
ማንኛውም ጅል ስዕል መስራት ይችላል፤ ለመሸጥ ግን ብልህ ሰው ይፈልጋል፡፡
ሳሙኤል በትለር
መጀመሪያ ደንስ፤ በኋላ አስብ፡፡
ሳሙኤል ቤኬት
ነገሮችን የምስለው እንደማያቸው ሳይሆን እንደማስባቸው ነው፡፡     ፓብሎ ፒካሶ
ቀለማት የተፈጥሮ ፈገግታዎች ናቸው፡፡
ሊይግ ሃንት
ሰው ሁሉ ስዕልን ለመረዳት ይፈልጋል፡፡ ለምንድን ነው የአዕዋፋትን ዝማሬ የመረዳት ሙከራ የሌለው?
ፓብሎ ፒካሶ
የራሴ ስዕሎች ባለቤት አይደለሁም፤ ምክንያቱም የፒካሶ ኦሪጂናል ስዕል ብዙ ሺ ዶላሮች ያወጣል ይሄ ከአቅሜ በላይ የሆነ ቅንጦት ነው፡፡
ፓብሎ ፒካሶ

Saturday, 02 May 2015 12:22

የየአገሩ አባባል

ጥበብ አልባ ዕውቀት በአሸዋ ላይ እንዳለ ውሃ ነው፡፡
የጊኒያውያን አባባል
ሞኝ ያወራል፤ ብልህ ያደምጣል፡፡
የኢትዮጵያውያን አባባል
ጥበብ በአንድ ጀንበር አይመጣም፡፡
የሶማሊያውን አባባል
በቀውስ ሰዓት ብልህ ድልድይ ሲገነባ፣ ሞኝ ግድብ ይገነባል፡፡
የናይጄሪያውያን አባባል
በኩራት ከተሞላህ ለጥበብ ቦታ የለህም፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
ብልህ ሰው ሁልጊዜ መላ አያጣም፡፡
የታንዛንያውያን አባባል
ማንም ብልህ ሆኖ አልተወለደም፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
ትልቅ ወንበር ንጉስ አያደርግም፡፡
የሱዳናውያን አባባል
የአንበጣዎች ጠብ ለቁራ ፌሽታው ነው፡፡
የሌሴቶ አባባል
ደጋግሞ በመሞከር ጦጣ ከዛፍ መዝለል ትማራለች፡፡
የቡጋንዳ አባባል
ምክር እንግዳ ነው፤ የሚቀበለው ካገኘ ሌቱን ያድራል፡፡ ያለበለዚያ የዚያኑ ዕለት ይመለሰል፡፡
የማላጋሲ አባባል
መጓዝ መማር ነው፡፡
የኬንያውያን አባባል
ባለሙያዎች ባሉበት የተማሪዎች እጥረት አይኖርም፡፡
የስዋሂሊ አባባል
ወተትና ማር ቀለማቸው ይለያያል፤ ነገር ግን አንድ ቤት ተጋርተው በሰላም  ይኖራሉ፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
መግባባት ሳይኖር ሰላም ሊኖር አይችልም፡፡
የሴኔጋሎች አባባል
እየመራሁ ነው ብሎ የሚያስብና ተከታይ የሌለው ሰው የእግር ጉዞ እያደረገ ነው፡፡
የማላዊያኖች አባባል

 በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (ኢቢኤስ) ቴሌቪዥን “የጆርዳና ኩሽና ሾው”    አዘጋጅ ጆርዳና ከብዶም የተፃፈው “የጆርዳና የምግብ አዘገጃጀት” የተሰኘ መፅሀፍ ሰሞኑን ለገበያ ቀርቦ እየተነበበ ይገኛል፡፡ መፅሐፉ ከመቶ በላይ የውጭ ምግቦች አዘገጃጀትን የያዘ ሲሆን ኢትዮጵያዊያን ከተለመደው የአመጋገብ ስርዓታቸው ወጣ ብለው እንደ ፓስታ፣ ፒዛ ያሉ የውጭ ምግቦችን በኩሽናቸው በቀላሉ አዘጋጅተው መመገብ እንዲችሉ ያግዛል ተብሏል፡፡ በኢቢኤስ ቲቪ “ጆርዳና ኩሽና ሾው” እውቅናን ያተረፈችው ባለሙያዋ፤ቦሌ ሩዋንዳ ኤምባሲ አካባቢ “ጆርዳናስ ኪችን ሬስቶራንት” የተሰኘ ምግብ ቤት ከፍታ የውጭ አገር ምግቦችን እያሰናዳች እንደምትሸጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡

 በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (ኢቢኤስ) ቴሌቪዥን “የጆርዳና ኩሽና ሾው”    አዘጋጅ ጆርዳና ከብዶም የተፃፈው “የጆርዳና የምግብ አዘገጃጀት” የተሰኘ መፅሀፍ ሰሞኑን ለገበያ ቀርቦ እየተነበበ ይገኛል፡፡ መፅሐፉ ከመቶ በላይ የውጭ ምግቦች አዘገጃጀትን የያዘ ሲሆን ኢትዮጵያዊያን ከተለመደው የአመጋገብ ስርዓታቸው ወጣ ብለው እንደ ፓስታ፣ ፒዛ ያሉ የውጭ ምግቦችን በኩሽናቸው በቀላሉ አዘጋጅተው መመገብ እንዲችሉ ያግዛል ተብሏል፡፡ በኢቢኤስ ቲቪ “ጆርዳና ኩሽና ሾው” እውቅናን ያተረፈችው ባለሙያዋ፤ቦሌ ሩዋንዳ ኤምባሲ አካባቢ “ጆርዳናስ ኪችን ሬስቶራንት” የተሰኘ ምግብ ቤት ከፍታ የውጭ አገር ምግቦችን እያሰናዳች እንደምትሸጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ማልድ የትምህርት ድጋፍ ኃ.የተ.የግ.ማ ባቀራረቡ የተለየ የልጆችን የንባብን ባህል የሚያዳብር፣ ከመጽሐፍ ጋር የተያያዘ የወላጆች ቀን “Book and fun Kids day” /የህፃናት የንባብና የትምህርታዊ ጨዋታ ቀን/ የፊታችን ማክሰኞ በትሮፒካል ጋርደን መናፈሻ ከ4-11 ሰዓት ድረስ ማዘጋጀቱን ገለፁ፡፡
ከ4-14 ዓመት ላሉ ልጆች በተዘጋጀው በዚህ የልጆች ቀን፤ ወላጆች አስተማሪዎች እንዲሁም ትላልቆች ለልጆች መጽሐፍት ያነባሉ፡፡ ጸሐፊያን በዚሁ ቀን መጽሐፍ የማሳተምን ሂደት ለልጆች ያስረዳሉ፣ የተለያዩ ጨዋታዎችም ይኖራሉ፡፡ ማልድ በ21ኛው ክ/ዘመን ልጆች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ወላጆች ልጆቻቸውን እንዴት ማሳደግ እንደሚገባቸው ይመክራል ተብሏል፡፡
ማልድ የትምህርት ድጋፍ ሰጪ አስተማሪዎችን በማሰልጠን፣ እንዲሁም ልጆችን ለክፍለዘመኑ ብቁ እንዲሆኑ የሚያግዙ በጥበብና በፈጠራ የተሞሉ ስልጠናዎችን በመስጠት ይታወቃል፡፡

 የዋይት ሃውስ ባለስልጣናት ለሳምንታት በየዕለቱ መክረዋል

   ለጊዜው ማንነታቸው በውል ያልታወቀ የኢንተርኔት አጭበርባሪዎች የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማን ኢሜይል በህገ-ወጥ መንገድ ሰብረው በመግባት፣ መረጃዎችን ማግኘት እንደቻሉ መረጋገጡን ስካይ ኒውስ ባለፈው ሰኞ ዘገበ፡፡
የዋይትሃውስ የደህንነት ሃላፊዎች ቻይናውያን አልያም ሩስያውያን ሳይሆኑ ሲሉ የጠረጠሯቸው እነዚህ የኢንተርኔት አጭበርባሪዎች፣ የይለፍ ቁልፉን ሰብረው በመግባት ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለሌሎች ሰዎችና ድርጅቶች የላኳቸውንና ከሌሎች የተላኩላቸውን የኢሜል መልእክቶች ማግኜት መቻላቸው ተረጋግጧል፡፡ድርጊቱ የተፈጸመው ከሳምንታት በፊት ቢሆንም፣ የዋይት ሃውስ ባለስልጣናት ጉዳዩን ሸፋፍነውት እንደቆዩ የጠቆመው ዘገባው፣የአጭበርባሪዎቹ ጉዳይ አሳሳቢ መሆኑን የሚያመለክተው ባለስልጣናቱ ላለፉት ሳምንታት በየዕለቱ እየተሰበሰቡ በጉዳዩ ዙሪያ ሲመክሩ መቆየታቸው ነው ብሏል ዘገባው፡
ሩስያውያን የኢንተርኔት አጭበርባሪዎች የኦባማን የኢሜል መልዕክቶች ለማግኘት የቻሉት፣ ባለፈው አመት በዋይት ሃውስ የሴኪውሪቲ ሲስተም ላይ በደረሰው ቀውስ ያገኙትን ክፍተት በመጠቀም ነው ተብሎ እንደሚገመት የገለጸው ዘገባው፣ ይሄም ሆኖ ግን አጭበርባሪዎቹ ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግለትን የኦባማ  የብላክቤሪ ስልክ መልዕክቶች ማግኘት እንዳልቻሉ አክሎ ገልጧል፡፡