Administrator
የስፖርት ዘርፍ አክሳሪ ሳይሆን አትራፊ ነው - - ጥናት
ስህተት ለመንቀስ ሁሉም ፈጣን ነው...!
“ሳይንስ እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ” ሊካሄድ ነው
ዋልያ መጻሕፍት “ሳይንስ እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ” በሚል ርዕስ ከዘርፉ ምሁራን ጋር የሚደረግ አጓጊ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። በዕለቱ ታዋቂው ኢምሬተስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ “ሳይንስ እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ” በሚለው ርዕስ ላይ ጥልቅ ማብራሪያ የሚሰጡ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና በናሳ ተመራማሪና የዶክትሬት ተማሪ የሆነው አቶ ተስፋዬ ማሞ መኮንን ደግሞ “ፊዚክስ በዕለት ተዕለት ሕይወታችን” በሚል ርዕስ ዙሪያ የዕውቀት ልውውጥ ያደርጋሉ።
ይህ ታላቅ የዕውቀት ማዕድ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሰዓት ከ8፡00 ጀምሮ በ4 ኪሎ ኢክላስ ሕንጻ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት አዳራሽ ይካሄዳል። ሁለቱን ታዋቂ ምሁራን በአንድ መድረክ በማግኘት አዳዲስ ሃሳቦችን ለመረዳት እና ከእለት ተእለት ሕይወት ጋር ለማገናኘት ይህንን ዕድል ይጠቀሙበት።
"ጦቢያ" በአውሮፓ ከተሞች ሥራዎቹን ሊያቀርብ ነው
በነፃ ሀሳብና በሰከነ መንፈስ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን በማድመቅ ላለፉት 14 ዓመታት የብዙዎችን ፍቅር ያተረፈው የ"ጦቢያ" መድረክ፣ በጀርመን መቀመጫውን ባደረገው "Hope for All" ግብረ ሰናይ ድርጅት አዘጋጅነት በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች አጓጊ ዝግጅቶቹን ሊያቀርብ ነው።
በገጣሚ ምስራቅ ተረፈ መስራችነት የሚመራው ይህ መድረክ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ኦገስት 9 በአምስተርዳም፣ ኦገስት 16 በኑረንበርግ፣ ኦገስት 23 ፍራንክፈርት፣ ኦገስት 30 ኮለን እንዲሁም ሴፕቴምበር 5 በሙኒክ ከተሞች ለታዳሚዎች ይደርሳል።
ይህ የኪነጥበብ ጉብኝት ከእጅግ ውብ መዝናኛ ባለፈ በትውልድ ሀገራቸው ለሚገኙ ወጣት ሴት ተማሪዎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ትልቅ የበጎ አድራጎት ዓላማ ሰንቋል። አዘጋጆቹ በአውሮፓ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና የዝግጅቱ ታዳሚዎች እየተዝናኑ ለተቸገሩ ወገኖቻቸው እንዲደርሱ በህብረት እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።

