Administrator

Administrator


        በቢዝነስና ቴክኖሎጂ የትምህርት ዘርፎች ላይ አተኩሮ የሚሰራው ሲልከን ቫሊ ኮሌጅ፤ የመጀመሪያውን የጥናትና ምርምር ጉባኤ፣ ትላንት ካዛንቺስ በሚገኘው ነጋ ሲሳ ቲሞል የኢንተርፕረነር ልማት ኢንስቲትዩት አዳራሽ አካሄደ።
ለጉባኤው ከ30 በላይ የሚሆኑ የጥንት ወረቀቶች ለውድድር ቀርበው የነበረ ሲሆን፤ በዕለቱ የተመረጡት ሰባት የጥናት ወረቀቶች መቅረባቸውን የሲልከን ቬሊ ኮሌጅ ስራ አስኪያጅ አቶ እሱባለው ታሪኩ ተናግረዋል። ጉባኤው በዋናነት አንተርፕረነርሽፕ፣ እንዲሁም ትምህርትና ቴክኖሎጂን ያማከለ ነው ተብሏል።የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ንጉሱ ጥላሁን በቦታው ተገኝተው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፣ ኢንተርፕረነርሽፕ፣ ትምህርትና ቴክኖሎጂ የማይነጣጠሉና ተቆራኝተው ውጤት የሚያመጡ እንደመሆኑ ኮሌጁ በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ አተኩሮ ጉባኤውን ማዘጋጀቱ ትልቅ ተግባር ነው ብለዋል።
ሰባቱም የጥናት ወረቀቶች በአንተርፕረነርሽፕ በትምህርትና በቴክኖሎጂ ዙሪያ ያሉትን ተስፋዎችና ተግዳሮቶች ብሎም የመፍትሄ አቅጣጫዎችን የሚጠቁሙ መሆናቸው ተናግሯል።
ኮሌጁ በዚሁ ዙሪያ ከኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ የተፈራረመ ሲሆን የጥናትና ምርምር ጉባኤውም ከኢኒስቲትዩቱ ጋር በመተባበር መዘጋጀቱ ታውቋል።
ሲልከን ቫሊ ኮሌጅ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የቢዝነስና የቴክኖሎጂ የትምህርት ዘርፎች በማስተርስና በዲግሪ ደረጃ ትምህርትና ስልጠና እየሰጠ የሚገኝ እውቅ  ኮሌጅ ስለመሆኑም ተብራርቷል። በጉባኤው ላይ የተለያዩ ኮሌጆች አመራሮችና ምሁራን እንዲሁም የኢኒስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር፣ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

 ኢቲኬር የግማሽ ቀን አውደ ጥናት በጌትፋም ሆቴል አካሂዷል


      ኢቲኬር የውበት መጠበቂያ ምርቶች ሽያጭ ኃ.የተ.የግ.ማህበር፣ “የቀጥተኛ ሽያጭ ገበያ ሥርዓትና ህገወጥ ፒራሚዳዊ አሰራር ሥልት በኢትዮጵያ የህግ ማዕቀፍ አጠቃላይ ዕይታ” በሚል ርዕስ፣ ባለፈው ሰኞ፣የግማሽ ቀን አውደ ጥናት በጌትፋም ሆቴል አካሂዷል፡፡የአውደ ጥናቱ ዓላማ፣ በቀጥተኛ ሽያጭ ገበያ ሥርዓትና ህገወጥ ፒራሚዳዊ አሰራር ሥልት መካከል ስላሉ ጉልህ ልዩነቶች  ግንዛቤ ለማስጨበጥ ነው ተብሏል፡፡
በአውደ ጥናቱ ላይ የኢቲኬር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ማቲዮስ መባን ጨምሮ የኢኮኖሚና የህግ ባለሙያዎች፣ በርዕሰ ጉዳዮቹ ዙሪያ ጥናታዊ ጽሁፍና ማብራሪያ ለታዳሚዎች ሰጥተዋል፡፡
ኩባንያው ባዘጋጀውና ለግማሽ ቀን በተካሄደው በዚህ አውደ ጥናት ላይ፤ በቀጥተኛ ሽያጭ የገበያ ሥርዓትና ህገወጥ ፒራሚዳዊ አሰራር ስልት መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው፣ የቀጥተኛ ሽያጭና ፒራሚዳዊ አሰራር ሥልት በኢትዮጵያ ህግ እንዴት ይታያል፣ በገበያው የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ምንድን ናቸው፣ እንዲሁም የቀጥተኛ ሽያጭ የገበያ ሥርዓት ለሃገር የሚያበረክተው የኢኮኖሚ ጠቀሜታ--- የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ተዳስሰዋል፡፡ የኢቲኬር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ማቲዮስ መባ ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፍ፣ የቀጥተኛ ሽያጭ የገበያ ሥርዓትና ፒራሚዳዊ አሰራር ስልት ያላቸውን ልዩነቶች በዓለም አቀፍ ተሞክሮ አስደግፈው ያብራሩ ሲሆን፤ የቀጥተኛ ሽያጭ የገበያ ሥርዓት ለአገር  ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን  ጥቅምና ፋይዳ  የራሳቸውን ኩባንያ በማስረጃነት በመጥቀስ አስረድተዋል፡፡
የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ት/ቤት መምህሩ  ዶ/ር ሰለሞን አባይ  በበኩላቸው፤ ሕገወጡ ፒራሚዳዊ የንግድ ስልት፣ የቁማር ዓይነት ባህርይ እንደሚታይበት ጠቁመው፤ ሙሉ ትኩረቱ ሰዎችን ምልመላና ገንዘብ መዋጮ መሰብሰብ ላይ ነው፤ብለዋል።
“በፒራሚዱ ሰንሰለትም ወደ ታች እየተዘረጋ ሲመጣ የላይኛዎቹ እየተደበቁ ይኼዳሉ ያሉት ዶ/ርሰለሞን፤ዚህም ምክንያት አንድ ችግር ቢፈጠር ኃላፊነትን የሚወስድ ተጠያቂ አይኖርም፡፡፡” ብለዋል፡፡
በግንዛቤ ማስጨበጪያ አውደ ጥናቱ ላይ እንደተገለጸው፤የቀጥተኛ ሽያጭ ሥርዓትን የሚከተሉ ድርጅቶች፣ የሚታወቅና በህግ የተመዘገበ አድራሻና የንግድ ፈቃድ ያላቸው ሲሆኑ፤ ለመንግሥትም ተገቢውን ግብር ይከፍላሉ፤ ፒራሚዳዊ አሰራርን የሚከተሉቱ ግን  አድራሻቸው የማይታወቅና ህጋዊ ፈቃድ የሌላቸው በመሆኑ ለመንግሥት ግብር የማይከፍሉና በአየር ላይ የሚንሳፈፉ  ናቸው ተብሏል፡፡የሕግ ባለሙያው አቶ አብዱልራዛቅ ነስሮ፣ በኢትዮጵያ የንግድ ውድድርና እና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ፤ የቀጥተኛ ሽያጭና የገበያ ሥርዓትን በተመለከተ የጠቀሰው ነገር እንደሌለ ጠቁመው፣ በአንጻሩ  ግልፅና የተብራራ ባይሆንም፣ የፒራሚዳዊ አሰራር መጠቀሱን አንስተዋል፡፡ የፒራሚዳዊ አሰራር ግልፅ ሆኖ ቢቀመጥ፣ ከቀጥታ ሽያጭ የንግድ አሰራር ጋር  ያለውን ብዥታ ለማጥራት እንደሚጠቅም ተመልክቷል፡፡ኩባንያው በአውደ ጥናቱ ላይ ያሰራጨው አጭር የቅኝት ጽሁፍ፤”የቀጥተኛ ሽያጭ የገበያ ሥርዓት የሚከተሉ ድርጅቶች፣ ጥራት ያላቸውን  ምርቶች ለገበያ የሚያቀርቡ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ባለው ልምምድ፣ እነዚህ ድርጅቶች የሰዎችን የአኗኗር ዘይቤና ፍላጎቶች ለማሟላት ለፈጠራ ሥራና ለምርምር ከፍተኛ ገንዘብ ይመድባሉ፡፡
በአንጻሩ በፒራሚድ ሥልት የተሰማሩት ደግሞ ምንም ዓይነት ምርት የሌላቸው ወይም ቢኖራቸውም ለይስሙላና የገበያ ዋጋ የሌለው ሲሆን ፤ ዋነኛ ዓላማቸው ከሰዎች የገንዘብ መዋጮን መሰብሰብ ነው፡፡” ይላል፡፡ የቅኝት ጽሁፉ አክሎም፤”የቀጥተኛ ሽያጭ ሥርዓት በአቋራጭና በፍጥነት በአንዴ ሃብት የሚሰበሰብበት ሳይሆን፤ በዚህ የገበያ ሥርዓት ውስጥ ጠንክሮ በመሥራት፣ ብዙ ደንበኞችን በማፍራትና ብዙ ሽያጭ በማስመዝገብ የኮሚሽን ክፍያ የሚገኝበት ነው:: የፒራሚዳዊ አሰራር በአንጻሩ፣ በአንድ ጊዜ የሚከበርበት እንደሆነና ሃብት ለማፍራት ብዙ የገንዘብ መዋጮ የሚያደርጉ ሰዎችን መመልመል የሚያስፈልግበት ነው፡፡፡” ሲል ያብራራል፡፡ኢቲኬር፤ በውበት መጠበቂያ ምርቶች ሽያጭ ላይ የተሰማራ ኩባንያ ሲሆን፤ ለ100 ያህል ቋሚ ሠራተኞች  የሥራ ዕድል የፈጠረና ባለፉት 10 ወራት ለመንግሥት 10 ሚሊዮን ብር  ግብር የከፈለ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ኩባንያው በተጨማሪም፣ ባለፉት አሥር ወራት ወደ 1 ሺህ ለሚደርሱ የምርት አስተዋዋቂዎች 50  ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ክፍያ መክፈሉንና እኒህ የምርት አስተዋዋቂዎች  ፈቃድ አውጥተው ለመንግሥት ግብር እንዲከፍሉ ማድረጉን ለማወቅ ተችሏል፡፡   



የአትሌት መቶ አለቃ በላይነህ ዴንሳሞን የአትሌቲክስ የህይወት ታሪክ የሚዳስስ ‘የተፈተነ ፅናት’ የተሰኘ መፅሐፍ ዛሬ ምሽት በኃይሌ ግራንድ ሆቴል ተመረቀ፡፡  
አትሌቱ 1000 ካሬ ሜትር ቦታ እንደተበረከተለት  የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሊዳሞ፣ ለአትሌት በላይነህ ዴንሳሞ የ1ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ እንደሚሰጠው ቃል ገብተዋል።

ኢቲኬር የውበት መጠበቂያ ምርቶች ሽያጭ ኃ.የተ.የግ.ማህበር፣ "የቀጥተኛ ሽያጭ ገበያ ሥርዓትና ህገወጥ ፒራሚዳዊ አሰራር ሥልት በኢትዮጵያ የህግ ማዕቀፍ አጠቃላይ ዕይታ" በሚል ርዕስ፣ በዛሬው ዕለት ለግማሽ ቀን የዘለቀ አውደ ጥናት በጌትፋም ሆቴል አካሄደ፡፡

የአውደ ጥናቱ ዓላማ፣ በቀጥተኛ ሽያጭ ገበያ ሥርዓትና ህገወጥ ፒራሚዳዊ አሰራር ሥልት መካከል ስላሉ ጉልህ ልዩነቶች  ግንዛቤ ለማስጨበጥ ነው ተብሏል፡፡

በአውደ ጥናቱ ላይ የኢቲኬር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ማቲዮስ መባን ጨምሮ የኢኮኖሚና የህግ ባለሙያዎች በርዕሰ ጉዳዮቹ ዙሪያ ጥናታዊ ጽሁፍና ማብራሪያ ለታዳሚዎች ሰጥተዋል፡፡

ኩባንያው ባዘጋጀውና ለግማሽ ቀን በተካሄደው በዚህ አውደ ጥናት ላይ፤ በቀጥተኛ ሽያጭ የገበያ ሥርዓትና ህገወጥ ፒራሚዳዊ አሰራር ስልት መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው፣ የቀጥተኛ ሽያጭና ፒራሚዳዊ አሰራር ሥልት በኢትዮጵያ ህግ እንዴት ይታያል፣ በገበያው የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ምንድን ናቸው፣ እንዲሁም የቀጥተኛ ሽያጭ የገበያ ሥርዓት ለሃገር የሚያበረክተው የኢኮኖሚ ጠቀሜታ--- የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ተዳስሰዋል፡፡

የኢቲኬር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ማቲዮስ መባ ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፍ፣ የቀጥተኛ ሽያጭ የገበያ ሥርዓትና ፒራሚዳዊ አሰራር ስልት ያላቸውን ልዩነቶች በዓለም አቀፍ ተሞክሮ አስደግፈው ያብራሩ ሲሆን፤ የቀጥተኛ ሽያጭ የገበያ ሥርዓት ለአገር  ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን  ጥቅምና ፋይዳ  የራሳቸውን ኩባንያ በማስረጃነት በመጥቀስ አስረድተዋል፡፡
በግንዛቤ ማስጨበጪያ አውደ ጥናቱ ላይ እንደተገለጸው፤የቀጥተኛ ሽያጭ ሥርዓትን የሚከተሉ ድርጅቶች የሚታወቅና በህግ የተመዘገበ አድራሻና የንግድ ፈቃድ ያላቸው ሲሆኑ፤ ለመንግሥትም ተገቢውን ግብር ይከፍላሉ፤ ፒራሚዳዊ አሰራርን የሚከተሉቱ ግን  አድራሻቸው የማይታወቅና ህጋዊ ፈቃድ የሌላቸው በመሆኑ ለመንግሥት ግብር የማይከፍሉና በአየር ላይ የሚንቀሳቀሱ ናቸው ተብሏል፡፡

ኩባንያው በአውደ ጥናቱ ላይ ያሰራጨው አጭር የቅኝት ጽሁፍ፤"የቀጥተኛ ሽያጭ የገበያ ሥርዓት የሚከተሉ ድርጅቶች ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለገበያ የሚያቀርቡ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ባለው ልምምድ እነዚህ ድርጅቶች የሰዎችን የአኗኗር ዘይቤና ፍላጎቶች ለማሟላት ለፈጠራ ሥራና ለምርምር ከፍተኛ ገንዘብ ይመድባሉ፡፡ በአንጻሩ በፒራሚድ ሥልት የተሰማሩት ደግሞ ምንም ዓይነት ምርት የሌላቸው ወይም ቢኖራቸውም ለይስሙላና የገበያ ዋጋ የሌላቸው ሲሆን ዋነኛ ዓላማቸው ከሰዎች የገንዘብ መዋጮን መሰብሰብ ነው፡፡" ይላል፡፡

የቅኝት ጽሁፉ አክሎም፤"የቀጥተኛ ሽያጭ ሥርዓት በአቋራጭና በፍጥነት በአንዴ ሃብት የሚሰበሰብበት ሳይሆን በዚህ የገበያ ሥርዓት ውስጥ ጠንክሮ በመሥራት፣ ብዙ ደንበኞችን በማፍራትና ብዙ ሽያጭ በማስመዝገብ ኮሚሽን የሚገኝበት ሲሆን፤ የፒራሚዳዊ አሰራር በአንጻሩ፣ በአንድ ጊዜ የሚከበርበት እንደሆነና ሃብት ለማፍራት ብዙ የገንዘብ መዋጮ የሚያደርጉ ሰዎችን መመልመል እንደሚያስፈልግ ይታወቃል፡፡" ሲል ያብራራል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ፣ በተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና በቶም የህክምና መሳሪያዎች ተከላና ጥገና ማዕከል በጋራ የተዘጋጀው ከተማ አቀፍ የህክምና መሳሪያዎችና ዕቃዎች ጥገና ዘመቻ፣ “የህክምና መሳሪያዎችና ዕቃዎች ብክነትን በጋራ እንከላከል!” በሚል መሪ ቃል፣ ዛሬ ሚያዝያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም በተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በይፋ ተከፍቷል።

በፕሮግራሙ ላይ የአዲስ አበባ የምግብ የመድሀኒትና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ታደሰ አጥላባቸው ፣የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ወንድሙ፣ የተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ግሩም ግርማ ፣ የቶም የህክምና መሳሪያዎች ተከላና ጥገና ማዕከል ባለቤትና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቶማስ ገ/መስቀል እና ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ እንግዶች ተገኝተዋል።

ፕሮግራሙን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ግሩም ግርማ፤ ዘመቻው መከፈቱ  ለሀገር የሚያበረክተው አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን ፤ የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ ታደሰ አጥላባቸው በበኩላቸው፣ ይህ ዘመቻ በተለያዩ ምክንያቶች የጥገና አገልግሎት ሳያገኙ ቁጭ ላሉ የህክምና መሳሪያዎች ትልቅ ዕድል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አቶ ታደሰ አክለውም፤ በዚህ ዘመቻ ሁሉም የግልና የመንግስት ጤና ተቋማት ያላቸውን አገልግሎት የማይሰጡ ወይም የተበላሹ የህክምና መሳሪያዎች  ወደ ዘመቻው በማምጣትና እንዲጠገኑ በማድረግ የዘመቻው አካል ከመሆን ባለፈ ያለአግባብ የሚባክኑ ሀብቶችን እንዲታደጉ ጥሪ አቅርበዋል።

 በተመሳሳይ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ወንድሙ ደግሞ  ይህ ዘመቻ ለህክምና አገልግሎት ጥራት የሚኖረው ፋይዳ ትልቅ መሆኑን ጠቁመው፣በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ ሆስፒታሎችና በአስራ አንዱም ክፍለ ከተሞች ስር የሚገኙ ጤና ጣቢያቸው እንደሚሳተፉም ገልፀዋል።

ዘመቻው በአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚካሄድ ሲሆን ከሚያዝያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም  እስከ ሰኔ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ለሁለት ወራት የሚቆይ መሆኑ  በፕሮግራሙ ላይ ተገልጿል።

ሁለት ወዳጆች በመንገድ ሲሄዱ አንድ አሮጌ ግድግዳ ላይ የተሰቀለ አንድ ያረጀ የሚመስል ስዕል ያያሉ። ሁለቱም ስዕል አድናቂዎች ነን ይሉ ነበርና ወደዚያ ስዕል ተጠግተው ቆመው ያስተውሉ ጀመር።
አንደኛው - “እንዴት ግሩም አድርጎ ስሎታል! እንደዚህ ያለ የጀምበር ጥልቂያ ስዕል (sun-set) እስከዛሬ አይቼ አላውቅም” አለ።
ሁለተኛው - “ይሄ እኮ ጀምበር ስትጠልቅ የሚያሳይ ስዕል አይደለም። ይሄ ጸሃይ ስትወጣ የሚያሳይ (Sun-rise) የንጋት ጎህ ስዕል ነው” አለው።
አንደኛው- “ምንም አትጠራጠር የጀምበር ጥልቂያ ስዕል ነው”
ሁለተኛው- “ማንም ይመስክር የጸሐይ መውጪያ ስዕል ነው”
 ሙግታቸው በረታ። ተካረሩ። ሙግታቸውን የሰማው ሰው ሁሉ በአቅራቢያቸው እየመጣ ሀሳብ መስጠት ጀመረ።
ከፊሉ - “ይሄ ተጥለግለግ (አመሻሽ) ነው። ፀሐይ አይኖቿን እየጨፈነች እንጂ እየገለጠች አይደለም እያለ ከአንደኛው ጀርባ ቆመ።
ከፊሉ ደግሞ- “በጭራሽ አካባቢዋን ሁሉ እያፈካች ዙሪያ ገባውን ጸዳል ልታለብሰው ተዘጋጅታለች። ሊነጋ ነው” ሲል ከሁለተኛው ጀርባ ቆመ። በመጨረሻ አንድ አረጋዊ የሰፈሩ ነዋሪ የተባሉ መጡ። እሳቸው ይናገሩ ተባለ።
አረጋዊውም- “ስዕሉ የጀምበር ጥልቂያ ማለትም የፀሐይ መግቢያ ይመስለኛል” አሉ፡፡ የተቃራኒው ወገን ህዝብ በማጉረምረም፤ “ምክንያቱን ያስረዱና!” አሏቸው።
አረጋዊውም- “ምክንያቱማ፣ እኔ ሰዓሊውን አውቀዋለሁ። በጭራሽ ጠዋት ጠዋት ከእንቅልፉ አይነሳም። ስለዚህም የንጋት ፀሐይ አይቶ አያውቅም። ካላየ ደግሞ አይስልም”
***
ጊዜው የህማማት ነው። ብዙ ህመም አለ። የሀገራችን የወደፊት እጣ ፈንታ ምን እንደሆነ አለማወቅ  በህዝብ ዘንድ ትልቅ ግርታን ፈጥሯል። ሕዝብ ኢንፎርሜሽን ካላገኘ ውሃ እንደአጣ አትክልት ነው። ይጠወልጋል።  በዚያው መጠን ልቡን ያሸሻል። ሰብአዊ መብቱን መጠየቅ ካልቻለና ካልተከበረለት ህመሙ ይበረታል። ሲቪል ህብረተሰብ መፍጠርም ዘበት ይሆናል። ህመም ሲጎነጎን እምቢተኝነትና አመጻም ይወልዳል። እያንዳንዷ ቀን ትናንሽ ምሬት መጸነሷ መጥፎ ምልኪ ነው! ሕዝብ በሀገር ውስጥ የሚፈጠር የሚደረገውን ሁሉ በዝርዝር ካላወቀ አይረጋጋም። መንግሥትና ሕዝብ ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ይሆናል። መብቶቹ ቢረገጡ ቀና ብሎ “ለምን?” ለማለት ድፍረት አይኖረውም። ድብቅነትን እንደ ዘይቤ ይይዘዋል። ህዝብ ካልተረጋጋ ሀገር ችግር ላይ ናት ማለት ነው። ሰሞኑን ለሚታየው የፖለቲካ ሁኔታ ሁሉ በምክንያትነት የተለያዩ ሀሳቦች ሲሰነዘሩ ከርመዋል። አንዳንዴ ዝርዝሩ ከጥቅሉ ይጋጫል። ተጻራሪ ወገኖች አቋም የሚነጣጠቁ ያህል የአንደኛው አቋም የሌላው የሚመስልበት ጊዜ አለ። በትክክል እነዚህ እነዚህ ጉዳዮች ዋነኛ የልዩነት መንስዔ ናቸው ተብለው ነጥረው የወጡ ናቸው ለማለት አሁንም ያስቸግራል። ነገሩ ይበልጥ እየቀረብነው ስንሄድ ይበልጥ እየተሸሸገ ይሄዳል ለማለት ነው።
“የእንጀራ እናትን እንጀራ፣ ወድቆም አታገኘውም” እንደሚባለው ተረት ሊሆን ይቃጣዋል።
በዚህ ላይ ከባለ ጉዳዩ በላይ በመሃል በመሃል የሚያዶሸድሸው መአት ነው። እንደ ቀንድ አውጣ ከሰንኮፉ ያልወጣ፣ የስልጣን-ጥማቱን ማርኪያ ሊያደርገው ወንዝ አቋርጦ የሚመጣ አለ። “በጠብታ ውሃ ውስጥ ጉማሬ አየሁ” እያለ የሚያጋንን የመኖሩን ያህል “ቢሆን አትጨፍሪ፣ ከጨፈርሽ አታበላሺ” መባል ያለበት አዲስ ዛር በአናቱ የፈላበት አፋሽ-አጎንባሽም ሞልቷል።
Beware of yes- men of Athens
They keep on saying ‘ Yes` ‘ Yes`
Till they put you into a mess
(“እሺ ጌታዬ” ከሚሉ አቴናውያን ተጠንቀቅ
“እሺ እሺ” እያሉ እየገፉህ ትርምስ ውስጥ እንዳትወድቅ) የሚባሉም አይጠፉም። በእነዚህ በእነዚህ ሳቢያ ኢንፎርሜሽን ይበልጥ እየተዥጎረጎረ ይጠራል የተባለው እየጎሸ፣ ተሰማ የተባለው እየተዳፈነ ይሄዳል። ጥርት ያለ ኢንፎርሜሽን ባለመቅረቡ ነገ ሀገሪቱን የሚጠብቃት የጀምበር ጥልቂያ ይሁን የፀሐይ መውጣት ከባቢ አየሯ አጠያያቂ ይሆናል። “በመጨረሻስ ለህዝቡ የሚተርፈው ምንድን ይሆን?” የሚለው ጥያቄ ይበረክታል። ይሄ ደግሞ የሁሉ ነገር ቁልፍ ነው!
ትላንትና ተጠይቀው ወይ ከነአካቴው ያልተመለሱ፣ ወይ በከፊል ብቻ የተመለሱ ዲሞክራሲያዊ ጥያቄዎች “መጨረሻቸው ምን ሊሆን ነው?” ማለት ግድ ይሆናል። የፖለቲካ ክፍፍል ያለነገር አይከሰትምና ስር ነቀልም ይሁን ጠጋኝ ለውጥ በመጣ ጊዜ ነባሮቹንም ሆነ አዲሶቹን ጥያቄዎች ዋነኛው ኢላማ እንኳ ቢስታቸው ፍንጣሪው ሳይመታቸው አይቀርም።
ከቶውንም የእስከዛሬው ዲሞክራሲ ውስጠ-ነገር ሲመረመር ታክሞ ተጠግኖ የሚድን ቁስል ይሆን ይሆን፣ ወይም አንቶኒዮ ግራምሺ እንዳለው፤ “ፓርቲ ሲነቅዝ የሚፈጠር፣ ጨርሶ የማይድንና የሚዛመት የፖለቲካ ደዌ (poltical gangrene) እመሆን ደረጃ ደርሶ ይሆን? መፍትሄውስ በሙሉ ኦፕራሲዮን ቆርጦ መጣል ነው ወይስ ሌላ መላ አለው? ማደንዘዣስ ያሻዋል አያሻውም?... ስለሁሉም ህዝብ ማወቅ ይፈልጋል። የሰማውን መረዳት የራሱ ፋንታ ነው።
እንጂ፤ በእናት- ዓለም ጠኑ ቲያትር እንደተጠቀሰው ዓይነት “ገባው አልገባው አይደለም የፖለቲካ ቁምነገሩ። ተቀበለ አልተቀበለም ነው!” የሚል አስተሳሰብ፤ ለመቼም ለማንም የማይበጅ መሆኑን ልብ ልንል የሚገባን አሁን ነው። 

 የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን እንዲከታተልለት ፍትህ ሚኒስቴር ወክሏል


አሜሪካ ኤምባሲ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት፣ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ የኬኒያ ኤምባሲ ክስ ቀረበባቸው። እነዚህ ተቋማት የተከሰሱት ከአንድ አመት ተኩል በፊት በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ በፀጥታ ሀይሎች ታፍኖ በተወሰደው በአቶ ሳምሶን ተክለሚካኤል ቤተሰቦች ነው፡፡
የአቶ ሳምሶን ተክለሚካኤል ባለቤት ወይዘሮ ሚለን ሀለፎምና ጠበቃቸው ዳባ ጩፋ (ዶ/ር)፣ ሀሙስ ሚያዚያ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ረፋድ ላይ በሳሮማሪያ ሆቴል ለጋዜጠኞ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው ተቋማቱን መክሰሳቸውን ያስታወቁት። ክሱ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ የሰብአዊ መብት ችሎት መቅረቡንም ጠበቃ ዳባ ጩፋ (ዶ/ር) አብራርተዋል። የውጪ ጉዳይ  ሚኒስቴር ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን የክስ መዝገቡ ዘግይቶ የደረሰው በመሆኑ አንብቦ ምላሽ ለመስጠት ጊዜ እንዲሰጠው በጠየቀው መሰረት ፍርድ ቤቱም ለሚያዚያ 13 (ትላንት) ቀጠሮ መስጠቱን የገለጹት ጠበቃው፤ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ጉዳዩን እንዲከታተልለት ፍትህ ሚኒስቴርን መወከሉንም ጠቁመዋል።
ላለፉት 19 ዓመታት በኬኒያ ናይሮቢ ነዋሪነቱን አድርጎ በጋዝ ንግድ ላይ በመሰማራት ሲሰራ የነበረው አቶ ሳምሶን እስካሁን በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ ልጆቹና ቤተሰቡ እንደማያውቁና ከዛሬ ነገ ይመጣል እያሉ በመጠበቅ በስቃይ ላይ መሆናቸውን የገለጹት ባለቤቱ ወ/ሮ ሚለን ሀለፎም፤ ባለቤቴ ከመያዙ በፊት ከወንጀል ነጻ የሚል ሰርትፍኬት ያለው፣ እጅግ ደግና ለተቸገረ ቀድሞ ደራሽ እንጂ የባህሪም ሆነ የሰብዕና ችግር  ያለበት አይደለም ብለዋል።
“ወንጀል ሰርቶም ከሆነ በ48 ሰዓት ውስጥ ፍ/ቤት መቅረብ ሲገባው እስካሁን በምን ሁኔታ ላይ  እንዳለ አለማወቃችን ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ነው” ብለዋል።
የታሳሪው ቤተሰቦች በኬኒያ ኤምባሲ በኢትዮጵያ፣ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴርና በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በኩል ጉዳዩ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈታ ብዙ ርቀት መጓዛቸውን የገለጹት ጠበቃው፣ ሆኖም እስካሁን የተገኘ ውጤት አለመኖሩን አብራርተዋል። የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያና የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በ3 ወር ውስጥ እናስለቅቀዋለን ብለው መግለጫ ቢያወጡም ጠብ ያለ ነገር አለመኖሩን የገለጹት ጠበቃ ዳባ ጩፋ (ዶ/ር) ደንበኛቸው ከተያዘበት ጊዜ ጀምሮ የተያዘበት ምክንያት ሳይገለጽ፣ በ48 ሰዓት ፍ/ቤት ሳይቀርብ ከልጆቹ፣ ከጠበቃውና ከሀኪሙ ጋር የመገናኘት መብቱ ተጥሶ እየተጉላላ መሆኑ በእጅጉ እንዳሳዘናቸውና ይህንን ክስ በተቋማቱ ላይ ለመመስረት እንደተገደዱ አብራርተዋል።
 የቀረበውም ክስ ከላይ በተዘረዘሩት የሰብአዊ መብት  ጥሰቶች የተነሳ ከመደበኛው ክርክር ከፍ ያለና “ስልተ-ሙግት” እንደሆነ ያስረዱት የአቶ ሳምሶን ጠበቃ፤ ይህ ሁሉ ችግር የተፈጠረው በኢትዮጵያ የኬኒያ ኤምባሲ  ድክመት እንደሆነም አብራተዋል።
“ምንም እንኳን የኢትዮጵያ መንግስት ሊረዳን ቢሞክርም የእስከዛሬ እንቅስቃሴው  ውጤት ስላላመጣ አሁን ተጨማሪና ከእስከዛሬው ጠንከር ያለ እንቅስቃሴ አድርጎ ባለቤቴ ያለበትን ሁኔታ ያሳውቀኝ” ያሉት ወ/ሮ ሚለን፤ “ወንጀልም ሰርቶ ከሆነ ክስ ተመስርቶበትና  ፍርድ ቤት ቀርቦ ቅጣት ይቀጣ፤ ያለጥፋቱም ከሆነ የታሰረው በነጻ ይለቀቅልኝ፤ ይህን ለመጠየቅና ለመማጸን ከኢትዮጵያ መንግስት ውጪ የማንኳኳው በር የለም” ሲሉ ተማጽነዋል።
አቶ ሳምሶን ተክለሚካኤል በኬንያ ናይሮቢ ባለፉት 19 ዓመታ በጋዝ ንግድ ላይ ተሰማርተው ከኬንያ ጋዝ በማምጣት ኢትዮጵያ ውስጥ በማከፋፈል ስራ ላይ የቆዩ መሆናቸው የተብራራ ሲሆን ከአንድ አመት ተኩል በፊት በናይሮቢ ውስጥ በጸጥታ ሀይሎች ታፍነው  በመኪና ሲወሰዱ የሚያሳይ ቪዲዮ ከታየ በኋላ በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ እንደማይታወቅ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተጠቁሟል።

በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ካርቱምን ለቀው እየወጡ ነው
አገራት ዜጎቻቸውን ከመዲናዋ ለማስወጣት እየሞከሩ ነው


በሱዳን ባለፈው ቅዳሜ በአገሪቱ መደበኛ ጦር ሰራዊት እና በፈጥኖ ደራሽ ልዩ ሃይሉ መካከል የተቀሰቀሰው ግጭት እስከ ሳምንቱ መጨረሻ ድረስ ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ጦርነቱን ሽሽት  መዲናዋን ለቀው  እየወጡ ነው ተብሏል፡፡   
ባለፈው ረቡዕ ጠዋት ሰዎች በመኪናና በእግራቸውም ጭምር ካርቱምን ለቀው ሲወጡ ማየታቸውን  እማኞች ለቢቢሲ ተናግረዋል፡፡ ውጊያው ተባብሶ መቀጠሉን ተከትሎ፣ በርካታ አገራት ዜጎቻቸውን ከካርቱም ለማስወጣት እየሞከሩ ሲሆን በተፋፋመው ጦርነት ሳቢያ አብዛኞቹ አልተሳካላቸውም ተብሏል፡፡
የሱዳን መደበኛ ጦር ሰራዊትና የፈጥኖ ደራሽ ልዩ ሃይሉ ባለፈው ማክሰኞ ከ12 ሰዓት ጀምሮ ለ24 ሰዓታት የሚዘልቅ ተኩስ የማቆም ስምምነት ላይ ደርሰው እንደነበር ቢነገርም፤ ስምምነቱ ወዲያውኑ መክሸፉ ታውቋል፡፡ባለፈው ረቡዕ ቃላቸውን ለቢቢሲ የሰጡ ነዋሪዎች፤ በዕለቱ በካርቱም የጦር ማዘዣ ጣቢያና አየር ማረፊያ አቅራቢያ ጨምሮ በመኖሪያ መንደሮች የተኩስ ድምፅ ሲሰማ እንደነበር ተናግረዋል፡፡መቀመጫውን በካርቱም ያደረገው ጋዜጠኛ መሃመድ አላሚን ለቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ሬዲዮ እንደገለፀው፤ ተኩስ የማቆም ስምምነት ላይ ተደርሷል ቢባልም፤ የጥይት ድምፅ አልቆመም ብሏል፡፡
“በጣም አሰቃቂ ነው - እነዚህ ተፋላሚ ቡድኖች በየቦታው ዝም ብለው ነው የሚተኩሱት፡፡” ሲል አላሚን ተናግሯል፡፡ “እኔ ራሴ በመቶዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ወደ አጎራባች አገራት ለመሸሽ ከካርቱም ለቀው ሲወጡ አይቻለሁ፡፡” ብሏል፡፡
አንዳንዶች ምን እየተካሄደ እንዳለ እንኳን አያውቁም - ሌሎች ደግሞ ቁጣቸውን በሁለቱም ተፋላሚዎች ላይ ይሰነዝራሉ፤ ተብሏል፡፡  
“ዜጎች በመሰረቱ ይሄ ጦርነት እነሱ ላይ ያነጣጠረ አድርገው ነው የሚያስቡት፡፡ በመንገድ ላይ ያገኘኋቸው ሰዎች የነገሩኝ ይሄንን ነው” ብሏል፤ ጋዜጠኛ መሃመድ አላሚን፡፡ ተኩስ የማቆም ስምምነቱን ለመተግበር ያለው አንድ ችግር፤ በከተማዋ ተበታትኖ የሚገኘው ተዋጊ ሃይል ሊሆን እንደሚችልም ግምቱን ሰንዝሯል፡፡
“በእነዚህ ወታደሮች መካከል ያለመናበብ ዓይነት ነገር ይታያል - እየተዋጉ ያሉት በተለያዩ አካባቢዎች፣ በተለያዩ ቦታዎች ነው-የግንኙነት ክፍተት ባለበት ሁኔታ…” ብሏል፡፡
ነዋሪዎች ካርቱምን ለቀው መውጣት የጀመሩት ባለፈው ረቡዕ ማለዳ ተኩስ የማቆም ስምምነቱ ከሽፎ ውጊያው ከቀጠለ በኋላ መሆኑን የዘገበው ቢቢሲ፤ በጦር ሰራዊቱ ማዘዣ አቅራቢያ የተከሰተውን ፍንዳታ ተከትሎ፤ ካርቱም በወፍራም ጥቁር ጭስ ተጠቅልላ እንደነበር አስታውሷል፡፡
የዓይን እማኞች እንደተናገሩት፤ ከባድ መሳሪያ የታጠቁ የፈጥኖ ደራሽ ልዩ ሃይል ተዋጊዎች በፒክ አፕ ተሽከርካሪዎች ከተማዋን ሲቃኙ፤ ለጦር ሰራዊቱ ታማኝ የሆኑ ተዋጊ ጀቶች በልዩ ሃይሉ እንደተያዙ የታመነባቸው ዒላማዎች ላይ ጥቃት ሲሰነዝሩ ነበር፡፡
አንድ መዲናዋን ለቆ እየወጣ የነበረ ሱዳናዊ ለቢቢሲ እንደተናገረው፤ የፈጥኖ ደራሽ ልዩ ሃይል በከተማዋ ዙሪያ ባሉ መንገዶች የፍተሻ ጣቢያ ያቋቋሙ ሲሆን የልዩ ሃይሉ ተዋጊዎች ዘረፋ ፈፅመውበታል-ሞባይል ስልኩንና ጥቂት ገንዘብ በመንጠቅ።
በመዲናዋ አንዳንድ አካባቢዎችም ዘረፋዎች መፈፀማቸው ተነግሯል፡፡ ባለፈው ማክሰኞ የልዩ ሃይሉ አባላት በየቤቱ እየዞሩ ውሃና ምግብ ሲጠይቁ እንደነበር የካርቱም 2 አካባቢ ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል፡፡
ውጊያው እየተባባሰ መምጣቱን ተከትሎ፣ በርካት አገራት ዜጎቻቸውን ከአገሪቱ ለማስወጣት ዝግጅት መጀመራቸውን አስታውቀዋል።ጃፓን፤ የመከላከያ ሃይሏ የኤምባሲ ሠራተኞችን ጨምሮ 60 የሚደርሱ የጃፓን ዜጎችን እንዴት ከሱዳን እንደሚያስወጣ እያሰበበት መሆኑን ተናግራለች- ለዚህም የጦር አውሮፕላን በተጠንቀቅ ላይ መሆኑን በመግለፅ፡፡
የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስቴርጎሜና ታክስ፤ መንግስታቸው 210 ያህል ዜጎቹን ከሱዳን ማስወጣት ይቻል እንደሆነ በመገምገም ላይ እንደሚገኝ ለፓርላማ ተናግረዋል፡፡ህንድም በሱዳን የሚገኙ ዜጎቿን ደህንነት ለማረጋገጥ ከሌሎች አገራትና ዓለማቀፍ ድርጅቶች ጋር ቅንጅት እየፈጠረች መሆኑን አስታውቃለች፡፡
በካርቱም የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በበኩሉ፤ በመዲናዋ ባለው አስጊ የጸጥታ ሁኔታ የተነሳ ዜጎቹን የማስወጣት እቅድ እንደሌለው አስታውቋል፡፡
እስከ ትላንት ድረስ በዘለቀው የሱዳን ውጊያ 300 በላይ ሰዎች መሞታቸውንና በሺዎች የሚቆጠሩ ጉዳት እንደደረሰባቸው የዓለም ጤና ድርጅትና የሱዳን ዶክተሮች ህብረት አስታውቀዋል፡፡
በመዲናዋ ካርቱም የሚገኙ አብዛኞቹ ሆስፒታሎች በደረሰባቸው የከባድ መሳሪያ ጥቃት ወይም ዘረፋ ሳቢያ ዝግ ሲሆኑ ክፍት የሆኑትም ቢሆኑ በአቅርቦት እጥረት የተነሳ የተሟላ አገልግሎት እየሰጡ አይደለም ተብሏል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ባለፈው ረቡዕ ሚያዝያ 11 ቀን 2015 ዓ.ም ከአምስት  ቀናት በፊት በሱዳን የተከሰተውን ጦርነት ለማርገብና ሁለቱን ጄነራሎች ለማደራደር ካርቱም ይገባሉ ተብለው የነበሩት የሦስት አገራት መሪዎች ጉዟቸውን መሰረዛቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ የካርቱም ጉዟቸውን የሰረዙት የሦስቱ አገራት መሪዎች የሱዳን ጎረቤት የሆኑት የኬንያ፤ የደቡብ ሱዳንና የጅቡቲ መሪዎች ናቸው፡፡የባለፈው ማክሰኞ የ24 ሰዓት ተኩስ የማቆም ስምምነት ተግባራዊ ቢደረግ ኖሮ፤ የሦስቱ አገራት መሪዎች፤  የሱዳን የጦር ሃይል አዛዥ ጄነራል አብደል ፈታህ አል ቡርሃን እና የፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ አዛዥ መሃመድ ሃምዳን ዳጋሎን ለማደራደር ወደ ሱዳን እንዲገቡ ምቹ ሁኔታን ይፈጥር ነበር ተብሏል፡፡    ቀደም ሲል የግብፅ ፕሬዚዳንት አብደል ፈታህ አል-ሲሲ ከደቡብ  ሱዳን ጋር በመሆን የአገሪቱን ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ ልዩ ሃይል አባላቱን ለማደራደር ጥያቄ ማቅረባቸውን ባወጡት መግለጫ አስታውቀው ነበር፡፡
እስካሁን ድረስ ምዕራባውያን፤ የአረብ አገራትና የአፍሪካ ህብረት ሁለቱ ተፋላሚዎች ልዩነቶቻቸውን በንግግር እንዲፈቱ ተደጋጋሚ ጥሪ ቢያቀርቡም ውጊያው ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
የአፍሪካ ህብረት፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፤ አሜሪካና ብሪቴይን ያደረጓቸው የሽምግልና ጥረቶች ያልተሳኩ ሲሆን ሱዳን ወደ እርስ በርስ ጦርነት ልትገባ ትችላለች የሚለው ስጋት እያየለ መጥቷል፡፡
ሁለቱ ጄነራሎች እንዴት ወደ ግጭት ገቡ?
ከሁለት ዓመት በፊት በሱዳን ውስጥ መፈንቅለ መንግስት ከተካሄደ በኋላ የጦር ጄነራሎች ሉዓላዊ ምክር ቤት የሚባል አቋቁመው አገሪቱን ሲመሩ ቆይተዋል - ሁለቱ ጄነራሎች፡፡ አርኤስኤፍ የተባለው ፈጥኖ ደራሽ ሚሊሻ በጄነራል ሞሃመድ ሐምዳን ዳጋሎ የሚመራ ሲሆን  ጄነራሉ የሉአላዊ ምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዚዳንትም ናቸው፡፡ የሉአላዊ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት የሆኑት ጄነራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን ደግሞ የአገሪቱን ጦር ሃይል ይመራሉ፡፡
ሱዳንን ወደ ሲቪል መንግስት ለማሸጋገር የቀረበው ዕቅድ፤ የፈጥኖ ደራሽ ሃይሉን ከአገሪቱ ጦር ሰራዊት ጋር በማዋሃድ የጊዜ ሰሌዳ ዙሪያ ከስምምነት ላይ ሳይደረስበት ቆይቷል፡፡ አርኤስኤፍ ውህደቱ በአስር ዓመት ጊዜ ውስጥ እንዲፈፀም የሚፈልግ ሲሆን የአገሪቱ ሰራዊት ግን በሁለት ዓመታት ውስጥ ተግባራዊ እንዲሆን ይፈልጋል። የግጭታቸው መንስኤና ጦር ያማዘዛቸውም ይኼው ጉዳይ ነው፡፡ ጄነራል ቡርሃን በሚቋቋመው ሲቪል መንግስት ውስጥ የሚመሰረተውን የተዋሃደ የአገሪቱን ጦር ማን መምራት አለበት በሚለው ጥያቄ ዙሪያ የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት ከጄነራል ዳጋሎ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልፀው ነበር፡፡ ሆኖም ከንግግሩ በፊት በሁለቱ ቡድኖች መካከል ግጭት ተከሰተ - ባለፈው ቅዳሜ፡፡  የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት፤ አሁን ሁለቱ ጄነራሎች አንጃ ፈጥረው የሥልጣን ሽሚያ ውጊያ ውስጥ ገብተዋል። የማናቸውም ማሸነፍ ደግሞ ለሱዳን ህዝብ ፋይዳ የለውም ተብሏል፡፡
 ለምን ቢሉ? የሱዳን ህዝብ የሚፈልገው ወታደራዊ አስተዳደር ሳይሆን በህዝብ የተመረጠ የሲቪል አስተዳደር ነውና፡፡ በተደጋጋሚ አደባባይ እየወጣ ሲጠይቅ የነበረውም ወታደሩ ለሲቪል አስተዳደር ሥልጣኑን እንዲያስረክብ ነው፡፡


“ማንኛውም ሰው ንጹህ ውሃ በነጻ መውሰድ ይችላል” ይላል የሆቴሉ የውሃ ቧንቧ  ላይ ተለጥፎ ያየነው ማስታወቂያ ። ሆቴሉ በራሱ ወጪ አስቆፍሮ ያወጣውንና ለሆቴሉ አገልግሎት የሚጠቀምበትን የከርሠ ምድር ውሃ የአካባቢው ማህበረሰብ ለ 24 ሰዓት እንዲጠቀምበት ፈቅዷል ።በደቡብ አፍሪካ በስደት  የቆዩት ወ/ሮ ህይወት አየለ እና በባለቤታቸው አቶ ዳግማዊ መኮንን  የተገነባው ግዙፉ  ስቴይ ኢዚ ፕላስ ሆቴል ለእንጦጦ ቅርብ በሆነ አካባቢ ተገንብቷል ።
ስቴይ ኢዚ ፕላስ ሆቴል 103 የመኝታ  ክፍሎች፣ ከ15 እስከ 1,500 ሰዎችን  ማስተናገድ የሚችሉ  ስድስት የስብስባና፣ የሰርግ አዳራሾች እንዲሁም የኪነጥበብ  እና ሌሎች ዝግጅቶች የሚሆኑ ሰፋፊና ምቹ  አዳራሾች  አሉት።
ከእንጦጦ ፓርክና  ቦታኒክ ጋርደን  ለሚመጡ ጉብኚዎች እንዲሁም በእንጦጦ እና ሱልልታ  የሩጫ ልምምድ  ለሚያደርጉ አትሌቶች   በቅርብ የሚገኝ ደረጃውን የጠበቀ  ሆቴል እንደሆነ የተነገረለት ይኸው ሆቴል በግልና በቡድን ለሚመጡ የአገር ውስጥና የውጭ አገር አትሌቶች  ምቹና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችል ሆኖ መዘጋጀቱም ተጠቁሟል ።
ሆቴሉ   በሰዓት ከ30,000 ሺ ዳቦ በላይ ማምረት የሚችል ዘመናዊ ማሽን ያሉት ሲሆን ለአካባቢው ማህበረሰብ ዳቦ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ መዘጋጀቱም ተነግሯል ።   ከ 250  በላይ  ለሚሆኑ ዜጎችም  የስራ ዕድል መፍጠር ችሏል። ከመሀል ከተማ  ፒያሳ በመኪና  አስር ደቂቃ ብቻ የሚወስድ ሲሆን  ፀጥ ያለ እና ነፋሻማ  ስፍራ ላይ የሚገኝ ሆቴል  ነው።ሆቴሉ  በአጠቃላይ  የያዘው  ስፍራ  2,250 ሜትር ስኩዬር ሲሆን  በ1,700  ሰኩዬር  ላይ ሆቴሉ ተገንብቷል።
 የኤሌትሪክ መኪና ይዘው ለሚመጡ  ደንበኞቹ   ኤሌትሪክ ቻርጅ  ማድረጊያ  ቦታ ያለው ሲሆን  በቅርቡ በሚጠናቀቁት የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ  ሰፖርት መስሪያ ጂም ፣የሴትና የወንድ ለየብቻ (በFloor)  ሳውና  እና ስቲም ባዝ  ፣ መዋኛ ገንዳ፣የዮጋ አዳራሽ በተጨማሪም  የባህል  ሬስቶራንትና   የሙዚቃ አዳራሽ  ይኖረዋል። በተጨማሪም እስቴ ኢዚ ፕላስ ሆቴል የከርሰ ምድር ውሃ ያለው ሲሆን በሰከንድ አምስት ሊትር ውሃ ማመንጨት የሚችል ሲሆን ለማህበረሰቡ ለ24 ሰዓት በነፃ እየሰጠ ማህበረሰባዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ የሚገኝ ሆቴል ነው፡፡
ስቴይ ኢዚ ፕላስ ሆቴል ከእዚህ በፊት 22 አካባቢ በነበረው ሆቴሉ አማካኝነት በበርካታ የበጎ አዶራጎት ስራውች ላይም በመሣተፍ ሀላፊነቱን ሲወጣ ቆይቷል።

በጥንት ጊዜ ነው፡፡ አንድ ንጉስ  ቋጥኝ ድንጋይ ሆን ብሎ  ዋናው መንገድ ላይ ያስቀምጣል፤መንገዱን ዘግቶ ማለት ነው፡፡ ከዚያም ተደብቆ በዚያ ከሚያልፉ ሰዎች መካከል  ያንን ቋጥኝ  ከመንገዱ ላይ ማን እንደሚያነሳው  በጉጉት መመልከት ይጀምራል፡፡
 መጀመሪያ ላይ  ለንጉሱ ቅርብ የሆኑ ሃብታም ነጋዴዎችና ባለሟሎች መጡ፡፡ ነገር ግን ያ መንገዱን  የዘጋው  ቋጥኝ ድንጋይ ፈጽሞ አላሳሰባቸውም፡፡ ከአነ መኖሩም ትዝ ያላቸው አይመስሉም፡፡ በራሳቸው ወሬ በእጅጉ ተጠምደው ድንጋዩን ታከው  አለፉት፡፡
በዚያ መንገድ ያለፉ በርካታ ሰዎች ግን፤ “ለምን ንጉሱ ይሄን  ቋጥኝ ድንጋይ አያስነሳውም?!” ብለው በእጅጉ  አማረሩ፡፡
አንዳቸውም ግን በግልም ሆነ ተባብረው ያንን ድንጋይ ከጎዳናው ላይ ለማንሳት አልሞከሩም፡፡ አማረው ብቻ ነው የሄዱት፡፡
በመጨረሻ ግን አትክልት  የተሸከመ አንድ ገበሬ መጣ፡፡ መንገድ ዘግቶ የተቀመጠውን  ቋጥኝ ድንጋይ እንደተመለከተም፣ የተሸከመውን አትክልት ከራሱ ላይ አውርዶ መሬት  አስቀመጠና፣ከቋጥኙ ጋር ብቻውን ይታገል ገባ፡፡ ረዥም ጊዜ ወሰደበት፡፡ ከብዙ ልፋትና ድካም በኋላም ተሳካለት፡፡ ድንጋዩን ከመንገዱ  ላይ ገፍቶ ገፍቶ ዳር ላይ ማድረግ ቻለ፡፡
ከዚያም  መሬት ላይ ያስቀመጠውን አትክልት አንስቶ ሊሸከም ሲል፣ ቋጥኙ ድንጋይ ተቀምጦ የነበረበት ቦታ ላይ አንድ ቦርሳ  ተቀምጦ ተመለከተ፡፡ ቦርሳው በብዙ ወርቆች የተሞላ ነበር፡፡ ገበሬው ደነገጠም፤ ተገረመም፡፡  ዙሪያ ገባውን ቃኘና፣ ቦርሳውን ልውሰድ አልውሰድ በሚል ሃሳብ ለአፍታ ተጨነቀ፡፡
ወዲያው ግን የንጉሱ መልዕክት የሰፈረበት  ብጫቂ ወረቀት እዛው ቦርሳው ውስጥ አገኘ፡፡ “ይህን ቦርሳ፤ ቋጥኙን ከመንገድ ላይ   ያነሳ  ሰው ይውሰደው፤ ሽልማቱ ነው” ይላል፤የንጉሱ ማስታወሻ፡፡
ሁሌም በመንገዳችን ላይ  የሚገጥሙን ፈተናዎችና መሰናክሎች፣ ህይወታችንን ለማሻሻል የሚጠቅሙን መልካም ዕድሎችና አጋጣሚዎች  ናቸው፡፡ ሰነፎች በገጠሟቸው ፈተናዎችና መሰናክሎች ሲያማርሩና ሲያለቃቅሱ፤ ጎበዞች ግን  ችግሮችና ፈተናዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር ስኬት ይቀዳጁበታል፡፡

Page 7 of 646