Administrator

Administrator

አንበሳና ሦስት አሽከሮቹ አነር፣ ተኩላና ቁራ አብረው ይኖሩ ነበር፡፡ አንድ ቀን ምግብ ፍለጋ በመዘዋወር ላይ ሳሉ አንድ ግመል አገኙ፡፡ ግመል ከዚያ ቀደም አይተው አያውቁ ስለነበር፣ ይሄ ምን ይሆን? ሲሉ እርስ በርስ ተጠያየቁ፡፡ ግር ስላላቸው አነር ጠጋ ብሎ ጠየቀው፡፡ ግመል መሆኑን ነገራቸው፡፡ ነጋዴ መንገደኞች በዚህ ጫካ በኩል ይዘውት መጥተው በመካከል እንደተጠፋፉም አስረዳቸው፡፡ አነር፣ ተኩላና ቁራ ባዩትና በሰሙት እየተገረሙ ሄደው ለጌታ አንበሳ ነገሩት፡፡ አንበሳም “ይምጣና ከእኛ ጋር ይኑር፡፡ እኔ እጠብቀዋለሁ፡፡ እንከባከበዋለሁ፡፡ ሂዱና ወደዚሁ አምጡት” ሲል ትዕዛዝ - አከል ሀሳብ አቀረበ፡፡
አሽከሮቹ ሄደው ለግመል ነገሩት፡፡ ግመል በጣም ተደሰተ፡፡ አብሯቸው ለመሄድ ዝግጁ መሆኑንንም ገለጠላቸው፡፡ አሽከሮቹ ግን በሁኔታው አልተደሰቱም፡፡ ምነው ቢሉ… ሌላ ተመጋቢ አፍ ተጨመረ ማለት ነው፡፡ ግመሉ የመጣ ሰሞን ጌታ አንበሳ ድንገተኛ ፍልሚያ ከዝሆን ጋር ገጠመ፡፡ በዚህም ፍልሚያ ክፉኛ ቆሰለ፡፡ ስለዚህም ቁስሉ እስኪሽር ከዋሻ መዋል ጀመረ፡፡ አሽከሮቹም ከየትም ከየትም ብለው እሱን መመገብ ግዴታቸው ሆነ፡፡
አሳዛኙ ነገር ግን የጫካው ታዳኝ ሁሉ ቀስ በቀስ ተመናምኖ እየተሟጠጠ ሄደ፡፡ ውሎ አድሮም ከናካቴው የሚላስ የሚቀመስ ጠፋና አረፈው፡፡ ጌታ አንበሳ “እኔ ሄጄ የሚበላ ልፈልግ እንጂ እንዲህ እየተራብኩ ቁስሌ እንዴት ይድናል?” አለ። አሽከሮቹ “በጭራሽ
አይሆንም! አንተ አርፈህ መተኛት አለብህ፡፡” አሉት፡፡
አንበሳውም፤ “በሉ እንግዲያው ዘወር ዘወር ብላችሁ የሚበላ አምጡልኝ - ወደሌላም ሰፈር ሄዳችሁ ቢሆን ሞክሩ!” አላቸው፡፡
“ኧረ አንተን ብንጠብቅና ብናስታምም ይሻላል ጌታ አንበሳ”
“መጀመሪያ ምግብ ፈልጉ!”
አሽከሮቹ ምግብ ፍለጋ ወጡ፡፡ በየጫካው ሁሉ ዞሩ፡፡ ግን ምንም አጡ፡፡ ተኩላው፤ “እዚህ ምንም የለም እባካችሁ፡፡ ከንቱ ልፋት ነው!” አለ፡፡ ቁራው ቀበል አድርጎ “እውነት ነው እዚህ ምንም ነገር የለም፡፡ ቤት ግን ምን የመሰለ ግመል አለን‘ኮ” አለ፡፡ “እሱንማ እንዳንቋደስ ጌታ አንበሳ ግመሉ እንዳይነካ፤ እኔ አጠብቅልሃለሁ ብዬ ነው ያመጣችሁት ቃል - አባይ መሆን የለብንም ብሎናል‘ኮ፡፡ ስለዚህ ግመሉ በመበላቱ አይስማማም”
“ለማንኛውም ወደቤት እንሂድና ማታችንን እንንገረው፡፡ እኔ ግን ቆይ ታያላችሁ አንድ ዘዴ እዘይዳለሁ!” አለ አነር፡፡ ተያይዘው ወደ ቤት ተመለሱና የሆነውን ሁሉ ለጌታ አንበሳ ነገሩት፡፡ አቶ አንበሳ እጅግ አድርጎ አዘነ፡፡ “ከእንግዲህ እንዴት አድርጌ ቁስሌን ላድነው ነው!” ሲል አማረረ፡፡ አነር ብድግ ብሎ “አንተ ጌታችን በረሃብ ስትሞት ዝም ብዬ አላይም፤ እኔ አድንሃለሁ፡፡” አለ፡፡
“እንዴት?” አለ ጌታ አንበሳ “እኔን ብላኝ” ሲል አነር ራሱን ለጌታው ሊሰዋ አቀረበ፡፡
“በጭራሽ አላደርገውም፡፡ ባለፉት ዓመታት ሁሉ በታማኝነት ያገለገልኩኝ ታዛዤን ንክች አላደርግም!”፡፡
ተኩላ ድንገት ብድግ ብሎ፤“ጌታዬ፤ ከተራብክ በቃ እኔን ብላኝ” ሲል ጥያቄ አቀረበ፡፡ አንበሳም “አንተንማ ልበላ አልችልም፡፡ ለብዙ ዓመታ በቅንነት ስታገለግለኝ የቆየህ ወዳጄ’ኮ ነህ!” አለ፡፡
ቁራም ተራውን ተነስቶ “ጌታ አንበሳ እኔን ብትበላኝ ነው የሚሻለው”አንበሳ ትንሽ ኮስተር እንደማለት ብሎ “ወዳጆቼ ጅል አትሁኑ እንጂ፡፡ አንተንም ቁራን ልበላህ አልችልም፡፡ የብዙ ጊዜ ታማኝ አገልጋዬ ነህ፡፡ በዚያ ላይ እፍኝ የማትሞላ አናሳ ፍጥረት ነህ” ብሎ ተቆጣ፡፡
ግመሉ ያደረጉትን ውይይት ሁሉ ሲያዳምጥ ቆይቶ “እንግዲህ ጌታ አንበሳ ማንኛችንንም የመብላት ፍላጎት የለውም ማለት ነው፡፡” አለ ለራሱ፡፡ “ስለዚህም እኔም እንደሌሎቹ ‘እኔን ብትበላኝስ?’ ብዬ ብጠይቀው ተገቢ ይሆናል፡፡ “ጌታ አንበሳ ሆይ ምናልባት እኔን
ብትበላኝ ሳይሻል ይቀራል?” ሲል ጠየቀ ግመል፡፡“አንተን?” አለ አንበሳ በመደነቅ፡፡


“አዎ እኔን !” አለ አቶ ግመል፡፡“ግመል የጠየቀው ትክክለኛ ጥያቄ ነው!” አለ አነር፡፡“በጣም እንጂ!” አለ ተኩላ፡፡“ከዚህ የበለጠ ልባዊና ዕውነተኛ ጥያቄ ከየትም ሲገኝ አይችልም! ከሆነ እንዲያውም አሁኑኑ መፈፀም ነው ያለበት” አለ ቁራ፡፡ ውሳኔው ፀደቀ፡፡ አንበሳው ግመሉን እንዴት እንደሚበላው ለማሰብ ቀርቶ ዐይኑን እንኳን ሳይጨፍን ሶስቱ አገልጋዮቹ ግመሉን ዘነጣጥለው መሬት ላይ ዘረጉት፡፡ የልባቸው ሞላ፡፡ግን የአንበሳውን ድርሻ ለመውሰድ ያደፈጠ ልቡን ብቻ አምኖ የሚጓዘው በርካታው ክፍል ነው፡፡ የኢትዮጵያን ችግር እንፈታለን ለህዝቡም ፍትህ ርትፅ እናመጣለታለን፣ ዲሞክራሲን እንናጎናጽፈዋለን፣ ባረንጓዴው ዘመቻ አረንጓዴ ተፈጥሮን እናነጥፋለን፣ ፈጣን ልማት እናመጣለን የአፍሪካ የዳቦ ቅርጫትነቷን እናረጋግጣለን፣ ከመከላከል ወደማጥቃት ተሸጋግረናል፣ (ማርሽ ያለውና ማርሽ የሌለው) መልካም አስተዳደር ከልሂቅ እስከደቂቅ እናዳርሳለን፣ አንድም ጥይት የማይተኮስባት ሰላማዊ አገር ይኖረናል፣ በቀን ሶስቴ በልተን የምናድርባት ኢትዮጵያ ትሆናለች ወዘተ ቃል - ይገባል፡፡ ማተብ ይታሰራል! በስራ ትርጓሜው የለም! ባለፈው ዘመን እንደተባለው፡፡ “የምንለውን ብለናል የምናደርገውን
እንጀምር!” ማለት ይከተላል - ቃል ይገባል ቃል ይሻራል፡፡ አደራ ያስቀምጧል መልሰው አደራ ይበሏል! የችግር ቀን አንዱ “ግመል” እዳውን በራሱ ከፍሎ ሌሎች ረሀባቸውን ያስታግሳሉ፡፡ ችግራችንን ፈትተናል ብለው ያምናሉ፡፡ ጉዳዩ ግን ዞሮ ዞሮ “በወተት አምሮት የታመመ፣ ጮጮ ሙሉ ውሃ ግጥም አደረገ!” እንደተባለው ነው፡፡ “በሌላ ወገን ደስ አይበላችሁ ምጣዶች፣ ልንጋግረው ያሰብነውን አገነፋነው!” በሚል ዓይነት ፍልሚያ አንድም ወንዝ መሻገር አይቻልም፡፡ ከቶም የእያሪኮ ጩኸት ነው፡፡ አንድን ሀገራዊ ጉዳይ እነ እገሌን ድል ለመምታት፣ እነ እገሌን “ኩም” ለማድረግ፣ እነ እገሌን “አፍ - ለማስያዝ”፣ እነ እገሌን ገና ሳያቆጠቁጡ ለማስቀረት፣ በሚል ቀመር ከተጓዝን ጊዜያዊ ደስታን ብቻ እንደሚሰጠው የወይን ትፍስህት አላፊ ጠፊ የሞቅታ ጉዞ ይሆናል፡፡

ከቶውንም በተደጋጋሚ የሚታየውን የቅርብ - ራዕይ ችግር (Myopia) በሩቅ አሳቢ ዕይታ ለመተካት ስራዬ ተብሎ ካልተደከመ ብዙ ፀፀተኛና፣ ብዙ አስተዛዛኝ ሰዎችን በዙሪያ በመሰብሰብ ከንፈርን ከመምጠጥ ያለፈ ትርጉም ያለው ለውጥ አይመጣም፡፡ “እህህ እያሉ ምንቸት ሙሉ ጎመን ይጨርሳሉ” ነውና በታማኝነት በቀረቤታ፣ በ”አብሮኝ ደክሞ የት ላድርሰው” ዓይነት አንድም ሙያውን አጥቶ አንድም ቦታውን ሰቶ ዓይነት የቢሮክራሲ መዋቅር ቅንበባ ለሰው ኃይልም ፍጆታ ለመልካም አስተዳደርም ቀረፃ አመቺ ጥርጊያን አያመጣም፡፡ ከአንድ መስሪያ ቤት ወደሌላው ፕወዛም፣ ጥረዛ፣ ከፌቴ ራቅ ይበልልኝ ለማለት ያህል ካልሆነ “ከመጥበሻው ወደ እሳቴ” ከመሆን አያልፍም፡፡ ከነ ሥነ አዕምሮአዊ አሉተኝነት ከእነብሶት - ምሬቱ ፣ ከእነዳተኝነቱ፣ ከእነነገር ሰሪነቱ፣ ከነመበደል - መገፋቱ የውስጥ አፍራሽ ግብረ - ሃይል የመፍጠርን ያህል ይሆናል፡፡ ጉልቻ መቀያየሩ ቀረና ወጡን መቀያየር እንደማለት ያለ ሀገራዊ ምፀት ወይም ክፍለ - ከተማዊ ስላቅ እንዳይሆን መጠንቀቅ ነበር። ሰሞኑን “ዓለም ባንክን ያመነ ብር ዘገባ” የሚለው
መፈክር እጄ አመድ አፋሽ ነው። የሚሉ ሰራተኞችን ያስዘገነ እንዳይሆን መጠንቀቅ በተገባ ነበር፡፡ የሀገራችን ሰው ተዘጋጅቶ መጠበቅን በየዘመኑ እየዘነጋው ዋናና ትርፉን እየቀላቀለ ለኪሳራ ሲዳረግ በርካታ የለውጥ ወቅቶችን ተሻግሯል፡፡ ካልታዘልኩ አላምንም በሚል
የተጠራጣሪነት መንፈስ ተሸብቦ መመካከር ሲሻው ሳይመካከር፣ መደራጀት ሲያስፈልገው ሳይደራጅ፣ መጠየቅና መሞገት ሲገባው እጁን አጣጥፎ፣ “ወቸ ጉድን”ና “ጉድ-አንድ ሰሞን ነው”ን እያዜመ ኩሬንም ባህርንም እኩል እየዋኘ፣ እየበረደውም እየለበለበውም፤ እኔ
ቀጭኑ አዳሜ ቢተራመስ አይሞቀኝ አይበርደኝ” እያለ በመጨረሻ ለውጡ እንደደራሽ - ውሃ ሲወስደው እዬዬን ባህል ሲያደርገው ይኸው አራት ለውጥ ተቆጠረ፡፡ በእንጉርጉሮው ጠባይ አንፃር የድርጅቱም የግለሰቡም፣ የፓርቲውም ማህበሩም የዜማ ቅኝቱ አንድ መሆኑ
ወይ የያሬድ አገር ያሰኛል፡፡ “ታጥቆ እንዳይጠብቅ ወይኔ ወይኔ እያለ ይኖራል” የሚለው ተረትም የዚሁ ቅኝት አንድ ምት ነው!

እንዴት ሰነበታችሁሳ!
እኔ የምለው… በቃ ዘመኑ እንዲህ ሆነ ማለት ነው እንዴ… በቃ እኮ ሰው አየኝ አላየኝ ማለት መተፋፈር ምናምን ሁሉ ቀረ ማለት ነው? የእውነት እኮ እንደኔ ያለው በጋቢ ላይ ካፖርት መደረብ ‘ፋሺን’ የሚመስለው ‘ፕሪሚቲቭ’ ሰው.፣ ስምንተኛው ሺህ የደረሰ ቢመስለው አይገርምም፡፡ ኧረ እንደውም የእኛ ባስ ስለሚል ስምንተኛው መሆኑ ቀርቶ አስራ ስድስተኛው ሳይሆን አይቀርም፡፡ስሙኝማ… ስንት ነገር አምልጦናልሳ! አንዳንዴ ለአይን ያዝ ሲያደርግ በቦሌ መንገድ ‘ዎክ’ ሳጧጡፍ [ልጄ….ለእኛ ለእኛ ቦሌም ፓሪስም አንድ ናቸው] አንዳንድ ነገር አየት አደርግና ሲገርመኝ ያመሻል፡፡ እንዴ… ሰው እንዴት እንዴት ነው የሚያደርገው!
አንድ ወዳጄ አንድ ቅዳሜ ምሽት ቦሌ አካባቢን ሲያስስ አምሽቶ ኖሮ በማግስቱ ምን አለኝ መሰላችሁ? “የቆመ መኪና ሲመጣ ብቻ እየለየ የሚወዘውዝ መሬት መንቀጥቀጥ አለ እንዴ?” እኔ… በቃ ጭጭ አልኳ፡፡ ተናግሮ ከአናጋሪ ይሰውራችሁ፡፡


እና… ይኸውላችሁ ግርም የሚል ዘመን ነው፤ድሮ ድሮ “ሎሚ ብወረውር…” ተብሎ ነበር አሉ፤ ነገርዬው የሚያልቀው፡፡ የዘንድሮ ሰው… ልጄ ሎሚ የሚያክል ድንጋይ ይወረውር እንደሁ እንጂ … ብቻ አለመያዝ ነው፡፡ አሀ…‘ፋይል ለመክፈት’ ስንት ጣጣ አለ፡፡
አለላችሁ …. አንዳንዱ ሲያምጥ ከርሞ አንድ ቡና በወተት በትልቅ ብርጭቆና ዳበስ ዳበስ አርጎ ወፈር ያለ የልጅ ምሳ ሊሆን የሚል ቦምቦሊኖ ይጋብዛል፡፡ [ነገርዬዋ ማመልከቻ ቢጤ መሆኗ ነው] ታዲያ ልክ ሻኛው የሚገላበጥ የሀረር ሰንጋ የጣለላት ይመስል (ለነገሩ ዘንድሮ አይሞከረም!) “እንዴት ነው ታዲያ… ይመችሻል!” ይልላችኋል፡፡ ኧረ!... በቦምቦሊኖ ተመቸ! የእንትን ሰፈር ልጆች ቢሆኑ ኖሮ የዚህ ዓይነቱን ስልቻ ሙሉ ቦምቦሊኖ አሸክመው “በቀረበህ መንገድ ወደ ኬንያ…ወይ ኡጋዳ ተሰደድ…” ነበር የሚሉት፡፡
በስዋሂሊኛ ‘ይመችሻል!’ ምን እንደሆነ ስለማያውቅ አርፎ ይቀመት ነበር፡፡ ደግሞ ሌላው አለላችሁ… ተንከርፍፈህ ኑር ተብሎ ርግማን የተጣለበት የሚመስል፡፡ ጧት ይጠብቅና ከኮልፌ ኮከብ ጽባህ ቢሆን እኳን ይሸኛል፡፡ የትምህርት ሰዓት ሲያቅ ደግሞ
ቤት ይመልሳል፡፡ ምን አለፋችሁ እግሩ ስር ጎማ አልተገጠመም እንጂ ሶስት ቁጥር ታርጋ ካቻማሊ በሉት፡፡

አንድ ወዳጄ “እንዲህ ዓይነቱን…. እስኩል ባስ በለው” ነው ያለኝ፡፡ስሙኝማ ደግሞ አለላችሁ… ግርም የሚል ፍጡር፡፡ ፊልም የለ ትያትር የለ ሙዚቃ
የለ… የፈረደባትን ከጎኑ አድርጎ ድፍን አዲስ አበባን በእግር ሲያካልል ይውልላችኋል፡፡ በቃ “በእግር መጓዝ ጤንነት ነው…” እያለ ፀሀይ የለ፣ ቁር የለ ብቻውን የከተማውን ማስተር ፕላን ሲከልል የሚውል ነው የሚመስለው፡፡ የምር ግን… አንዳንዴ በቃ ነጩ ባንዲራ ቀረ እንጂ የሰላምም ተጓዥ ይመስላል፡፡ ‘ዎክ’ ሌላ ‘መንክራተት’ ሌላ፡፡እኔ የምለው … ነገርዬው ሁሉ እንደ ድሮ የተመለሰባቸው ቦታዎች አሉ እንዴ!
የመሀል አራዳ ውስጥ አዋቂዎች ሲነግሩኝ እዚያ አካባቢ “ትዝ አለኝ የጥንቱ” ዓይነት ጨዋታ አለ አለ፡፡ የት መሰላችሁ? አውቶብስ ፌርማታ፡፡ አንዳንዱ ቀኑን ሙሉ አውቶብስ ፌርማታ አይጠፋም አሉ፡፡ ምን አለፋችሁ… በቃ ሽፍቱ ያደረሰ ትኬት ቆራጭ ይመስል አላፊ አግዳሚውን ሲያይ ይውላል፡፡ እኔ’ኮ ሲኒማ ኢትዮጵያ አጠገበ ያለ ሁሉ ሰው አውቶብስ ጠባቂ ይመስለኝ ነበር፡፡ ለካስ ሌላም ጨዋታ አለ፡፡


ስሙኝማ የአንዳንዱ አራድነት ግርም የሚል ነው፡፡ [አንድ ጊዜ በዚህ ቢለኝ በዚያ የሆነ… ጥሬ ነገር የሆንኩበት ወዳጄ “አንተ ሰውዬ… አራድነትህን ሸጠህ በላኸው እንዴ!” ብሎኛል፡፡ እኔ የምለው ‘አራድነት’ ለ‘ፕራይቬታይዜሽን’ የሚቀርበው መቼ ነው? አንተ እንትና… ላንተ አራድነት የሚወጣው ጨረታ አይደለም ሶስቴ አሥራ ሶስቴ ነበር የሚሰረዘው! የእውነት ላንተ የሆነ ኤን.ጂ.ኦ በጣሳ የአራድነት እርዳታ ቢሰፍርልህ ይሻላል፡፡]እናላችሁ አንዳንዱ ኮተቤ አካባቢ ቆሞ “ስድስት ቁጥር አለፈች እንዴ?” ይላል፡፡ [ኧረ! ብልጥ ተሁኖ ልብ ውልቅ! ‘አይ የእንትን ሊዎንቺና ነች ያመለጠችህ’ ማለት ነበር፡፡]ስሙኝማ… ሴቶች ሰብሰብ ያሉበት አካባቢ ሲደርሱ የሚሸልሉ ወንዶች አይጥሟችሁም? በቃ… እኮ አሪፍ አክተሮች ናቸው፡፡ አረማመድ እግር ስር ስፕሪንግ የተገጠመ ነው የሚመስለው፡፡ አንዳንዱ ግንባሩን ከስክሶ እንዴት እንደሚኮሳተር!...
ብቻ ማን እንደሚነግራቸው እንጃ አንዳንዶች ሴቶች ኮስታራ ወንድ ይመቻቸዋል የሚል ፈሊጥ አላቸው፡፡ [ይኸው እኛ ስንት ዘመን ስንኮሳተር እንኳን ልንመቻቸው… መንገድ ተሻግረው ነው የሚያልፉት፡፡ እኔ እንደውም አንዳንዴ ኮስተር ብዬ ሸለልኩ ስል ለልጆቻቸው እየጠቆሙ “አያ ጅቦ መጣ…” ሳይሏቸው አይቀሩም፡፡]ስሙኝማ አንድ ነገሩ ሁሉ አልሆነ ያለው ወንደላጤም አለ አሉ፡፡ ምን አለ መሰላችሁ?
“ገንዘባችሁ ሁሉ አለቀ በሻይ ትዳሩን ሳናየው ዓለምን ሳናይ!”ታዲያ እኛ ከለከልን! አይ ሸጋው ወንደላጤ… አንተ ታዲያ ዘላለምክን የሰው ሆድ በስሙኒ ሻይ የምታነፍረው…የሻይ ቅጠል እርሻ የለህ፡፡ አንተ የዘጋኸውን እንጀራህን የምን “አላሳዝንም ወይ…” ነው፡፡ ገና በጠዋቱ በሻይ ላይ ሙጭጭ ያልከው በኋላ እኮ “ዋናው ነገር ፍቅሩ ነው…” እያልክ ቦምቦሊኖ አብረን እንግመጥ ከማለት አትመለስም!
ልጄ ድሮ ድሮ… ስንት ጣጣ ነበር፡፡ አንዷን እሺ ከማሰኘት የዓለም ባንክ ብድር ማስፈቀድ ይቀል ነበር - የምር፡፡ ያኔ እኮ… የወንዱም ሽለላ አሪፍ ነበር፡፡ ፀጉር ኖራቸውም ልኖራቸውም መሀል ላይ መከፈሏ አይቀርም፡፡ ካስፈለገም የሆነ ወፈር ያለ የእንግሊዝኛ ልብ ወለድ ይያዛል፡፡ አሀ… እንግሊዘኛ የሚያውቅ ‘አለመታወቂያ እንዲያልፍ’ ይፈቀድለታላ፡፡ ስሙኝማ… አንድ ወዳጄ መሀል ላይ ፀጉራቸውን የሚከፍሉ ሰዎችን ምን ትላቸው መሰላችሁ? “ሹል ቴክስ፡፡”ደግሞ አለላችሁ ብልጥነት ሞልቶ ይተርፈውና በብልጢኛ “ስምሽ መቅደላዊት
አይደለም?” ሲል ይጠይቃል፡፡ አጅሪትም “አይ አይደለም ፎዚያ ነው” ትለዋች፡፡ እሱ ምን ይላል መሰላችሁ? “አይ… ብዙም አልራቅሁም፡፡” ከዛ በብልጢኛ አሳሳቅ ይስቅና “ያው … መቼም ሞትና ትውውቅ አንድ ቀን ነው…” ይልና ብቻ ምን ለፋችሁበሴኮንድ ዘጠኝ ቃላት ይናገራል፡፡እኔ የምለው… አንዳንዶቻችሁ “እምቢ” ስትባሉ ድርቅና ነው እንዴ! በቃ ችክክ የሚል አለላችሁ፡፡ ነጋ ጠባ ከርቀት ይከተላታል፡፡ ምን አለፋችሁ ክላሺንኮቭ ቀረች እንጂ አንጋች ነው የሚመስለው፡፡በዛ ሰሞን እኔና ጓደኛዬ አንድ ሚኒ ባስ ውስጥ ሆነን… በቃ
“ፍቅር የተራበ” ዓይነት ድራማ ስናይ ነበር፡፡ አይተዋወቁም፡፡ ወንድዬው… ታዲያ በቃ የህይወት ታሪኩን ይዘረዝርላታል፡፡

እሷ ሆዬ… በተመስጦ ሳይሆን በመገረም ነበር የምታየው፡፡ አለ አይደለም… በሆዷ “ሰው እንዲህ ሞዛዛ ሆኖ ይፈጠራል?” የምትል ነው የሚመስለው፡፡እናላች…ኮሚክ ዘመን ሆኗል፡፡ አንዳንዱ የማያውቃትን “ሹራቡ ያምርብሽ…”
ይላል፡፡ “ፒንክ ቀለም እወዳለሁ፡፡” ኧረ! ታዲያ ጨርቅ ተራ አትሄድም! አይ ሽጋው ወንደላጤ… ገንዘቤ ሁሉ በሻይ አለቀ አለ! እንትን ሰፈር ብትሄድ ምን የመሰለ በሶ አለ መሰለህ፡፡ አሀ… የላጥካትን ጨጓራ ራስህ ጠግናታ! ስሙኝማ… እስቲ ቦሌ ሄጄ አስራ ዘጠኝ ቁጥርን ልጠብቅ፡፡ ማን ያውቃል…
‘ፒንክ’ ሹራብ ይመጣ ይሆናል!

Saturday, 16 December 2023 20:44

እኛማ እንቆጥራለን

እኛማ እንቆጥራለን
ዛሬም ሙሉ ሳቅክን
ያልተሸራረፈ ሙሉ ፈገግታህን
እንዳቀፍን አለን በየምላዳችን የነገ ሰብልህን..
አሴ ኩራ ኩራ፣ ባለህበት ኩራ፣
ብርሃን ያዘምራል፣ ያሳብህ ተራራ..
ዓመቱማ ያልፋል ወደ ፊት ገፍትሮን
ዘመኑ ቢሸብት፣
አይረሴ ራዕይ፣ ነጭ ፀጉር የለው
ከቶ መች ይረሳል
ህልምህ የወይን ጠጅ፣ ሲነጋ ይበስላል
የነበረህና የነበረን ሀሳብ፣ እያደር ይጠራል፡፡
ስምህ ማዘርዘሩ፣ መንፈስህ መብቀሉ
እምነት ፍልስፍና ውልና ፈትሉ
ዕውቀትና ትጋት ብርሃን ፊደሉ
ሩቅ እንዳሰብነው ሩቅ ነው ገድሉ
ዛሬም አለ ቃሉ፣
ያውም በርቶ ፈክቶ፣ እስከ ማዕዜኑ፡፡
አውቃለሁ ታውቃለህ
የመከረኛ አገር መከሯ እስኪገባ
መከራ መብዛቱ
እውን ቢሆን እንኳ
ራዕይህ አለ ምስክር ይቆማል፤ ቀኑ ለመንጋቱ
አይቆምም ጉዟችን ባይቆምም ስጋቱ....
አይደለም ራእይ ብሳና- ዛፍ ግንድ
ሽበት አይወርሰውም የዕድሜ ዘመን ግርድ
አይረሴ ራዕይ የቸገንክበትን
የፍል ዕውቀት እርሻ የዓለም አሂዶህን
ታያለህ ማሳውን፡፡
አሴ ኩራ ኩራ
ብርሃን ያዘምራል ያሳብህ ተራራ....
የራዕይ ተራራ....
ነቢይ መኮንን

በአፍሪካ ትልቁ የፓን አፍሪካ የሙዚቃ ሽልማት ሥነ ሥርዓት ኮራ ሽልማት ላይ (KORA AWARDS, THE BIGGEST PAN AFRICAN
MUSIC AWARDS CEREMONY) አምስት ኢትዮጵያዊያን ሙዚቀኞች በአምስት ዘርፍ እጩሆነው ተመርጠዋል፡፡ አምስቱም እጩዎች ከአርባ
ሌሎች ተፎካካሪዎቻቸው ጋር በሕዝብ በሚሰጥድምጽ እንደሚፎካከሩ በ KORA AWARDS የፌስቡክ ገጻቸው ይፋ አድርገዋል፡፡
1. በ BEST GROUP- AFRICANURBAN MUSIC ምርጥ 40ዎች ውስጥ የገቡትኢትዮጵያዊያን እጩ ጃኖ ባንዶች (JANO BAND)
ናቸው፡፡ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት ድምጽእንድትሰጧቸው በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ VOTEHERE :HTTPS://WWW.KORAAWARDS.
COM/TOP40
2.በBEST ARTIST TRADITIONALMUSIC ምርጥ 40ዎች ውስጥ የገባውኢትዮጵያዊያዊ እጩ አስቻለው ፈጠነ(ASCHALEWU FETENE ) በእናትዋ ጎንደርእና በካሲናው ጎጃም ነው፡፡ ከታች ባለው ሊንክበመግባት ድምጽ እንድትሰጡት በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ V OTE H ERE : H TTPS://WWW.KORAAWARDS.COM/TOP403. በ BEST MALE ARTIST-RAP MUSIC ምርጥ40ዎች ውስጥ የገቡት ኢትዮጵያዊ እጩ ልጅሚካኤል (LIJ MICHAEL) ነው፡፡ከታች ባለው ሊንክ በመግባት ድምጽ እንድትሰጡት በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
VOTE HERE : HTTPS://WWW.KORAAWARDS.COM/TOP404.በ BEST COLLABORATION OF THEYEAR ምርጥ 40ዎች ውስጥ የገቡት ኢትዮጵያዊያንእጩ ጆሲ ሮያል (JESSE ROYAL) ናቸው፡፡ ከታችባለው ሊንክ በመግባት ድምጽ እንድትሰጧቸው በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ VOTE HERE:HT TPS://W W W.KOR AAWARDS.COM/TOP405.በ BEST FEMALE AFRICAN URBAN
MUSIC ምርጥ 40ዎች ውስጥ የገባችው ኢትዮጵያዊት እጩ ሔዋን ገብረወልድ (HEWANGEBREWOLD) ናት፡፡ ከታች ባለው ሊንክ
በመግባት ድምጽ እንድትሰጧት በአክብሮትእንጠይቃለን፡፡ VOTE HERE : HTTPS://WWW.KORAAWARDS.COM/TOP40

እውቁ የትምህርት ባለሙያና የ95 ዓመት የእድሜ ባለፀጋው ዶ/ር አክሊሉ ሀብቴ ምስጋና ቀረበላቸው፡፡ የምስጋናና የእውቅና መርሃ ግብሩ
ባለፈው ማክሰኞ ታህሳስ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ጦር ሀይሎች አካባቢ በሚገኘው “ሊባዊ ኢንተርናሽና” ት/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥየተካሄደ ሲሆን የምስጋና መርሃ ግብሩበለባዊ አለም አቀፍ ት/ቤትና በተወዳጅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን አማካኝነት የተሰናዳ ነው፡፡
በእለቱ ልዩ ልዩ ኪነጥበባዊ መሰናዶዎች የቀረቡ ሲሆን ዶክተር አክሊሉ በስፍራው ተገኝተው ለለባዊ ት/ቤት መምህራንናተማሪዎች ልምዳቸውን በማካፈል እውቀትና ልምድ እንዲቀስሙ አድርገዋል፡፡ ዶ/ር አክሊሉ ሀብቴ በሀገራችን ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ሲጀመር ከመጀመሪያዎቹ ምሩቃን
መካከል አንዱ ሲሆኑ ዩኒቨርስቲውንም በፕሬዚዳንትነትና በመምህርነት አገልግለዋል፡፡ ዶክተሩ በሀገራችን የትምህር ዘርፍ ላይ የጎላ ሚና ከማከናወናቸውም በተጨማሪ በአለም ባንክ ውስጥም በትምህርት ዘርፍ ላይ ያገለገሉና የቀዳማዊ ሀይስላሴ ዩኒቨርስቲን(የአሁኑን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን) ታሪክ በ600 ገፅ በመጽሀፍ በማሳተምና ታሪክ በመሰነድ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል፡፡
 እኒህ የ95 ዓመት የእድሜ ባለፀጋ ለረጅም ዓመታት መኖሪያቸውን በሀገረ አሜሪካ ያደረጉ ሲሆን አልፎ አልፎ ወደ ሃገራቸው ኢትዮጵያ ብቅ እያሉ
ይመለሳሉም ተብሏል፡፡ የማክሰኞ እለቱ የምስጋናና የእውቅና መርሃ ግብርም ከአሜሪካ ተመልሰው ሀገራቸው በነበሩበትአጋጣሚ የተሰናዳና በአካል የታደሙበት ነውም ተብሏል፡፡ በእለቱ በርካታ እንግዶች የለባዊ እንተርናሽናል አካዳሚ ሀላፊዎች ተማሪዎችና መምህራን በታደሙበትዶ/ር አክሊሉ ሀብቴ ምስጋናና እውቅና ተሰጥቷቸው ተመስግነዋል፡፡

 32ኛው የአውደፋጎስ የመፅሀፍ ውይይት ክበብ “አደፍርስ ልቦለድ በሙዚቃ መንፈስ መፅሀፍነቱ ሲዳሰስ” በሚል ርእስ ነገ ታህሳስ7 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ቤተ መፃህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ (ወ መዘክር) እደሚካሄድ አዘጋጆቹአስታወቁ፡፡ የውይይቱን የመነሻ ሀሳብ ከላይ በተገለፀው ርዕስ የምታቀርበው ትሬዛ ዮሴፍ ስትሆን ፍላጎት ያለውና የስነ ፅሁፍ ወዳጅ የሆነ በውይይቱ ላይ እንዲታደምና እውቀት
እንዲቀስም አዘጋጆቹ ጋብዘዋል፡፡

ፈተናውን ማለፍ ያልቻሉ መቋቋሚያ ተሰጥቷቸው ከስራ ይሰናበታሉ ተብሏል

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስሩ ለሚገኙትና አዲስ የመዋቅራዊ ማሻሻያ አደረጃጀት ጥናት ባደረጉ ተቋማት ውስጥ ለሚገኙ ሁሉም ሠራተኞችና የስራ ኃላፊዎች የብቃት መመዘኛ ፈተና ሊሰጥ ነው ተባለ። ፈተናውን ያላለፉ ሰራተኞች መቋቋሚያ ተሰጥቷቸው ከስራ ይሰናበታሉ ተብሏል።
ከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ዘርፎች ለሰራኞቹ የብቃት ምዘና ፈተናውን የሚሰጥ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር የብቃት ምዘና ፈተናውን የሚወስዱት የቤቶች ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት፣ የስራ ኢንተርፕራይዝ ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት፣ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ጽ/ቤት፣ ህብረት ስራ ጽቤት የመሬት ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት መሆናቸውም ታውቋል። የብቃት ምዘና ፈተናው የሚሰጠው በክፍለ ከተሞቹና በከተማ አስተዳደሩ ስር ባሉ መዋቅሮች እንደሆነም ታውቋል።
የብቃት ምዘና ፈተናውን የወሰዱ ሠራተኞች ፈተናውን ማለፍ ካልቻሉ ሁለት የውሳኔ አማራጮች የቀረቡ ሲሆን፤ አንደኛው አማራጭ ሰራተኛ ድልድሉ ከመደረጉ በፊት አጭር ስልጠና ተሰጥቷቸው ፈተናውን በድጋሚ እንዲወስዱ የሚደረግ ሲሆን ሌላኛው አማራጭ ደግሞ ወደ ሌላ ተቋም ተዛውረው ባላቸው የትምህርት ዝግጅትና በነበራቸው ደመወዝ እንዲመደቡ ይደርጋል ተብሏል። ከእነዚህ ውጪ የሆኑት ደግሞ የማቋቋሚያ ድጋፍ ተደርጎላቸው ከሥራ እንደሚሰናበቱ ተነግሯል። ከስራ እንዲሰናበቱ ያደርጋል ተብሏል። በሃላፊነት ደረጃ ላይ ተመድበው ሲሰሩ የነበሩና የብቃት ምዘና ፈተናውን ማለፍ ያልቻሉ ሠራተኞች ደግሞ ከነበሩበት የስራ መደብና ደመወዝ ዝቅ እንደሚሉ ተገልጿል።የብቃት ምዘና ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ሜያቸው ለጡረታ የደረሱና ጡረታ መውጣት የሚፈልጉ ሠራተኞች በፍቃደኝነት የጡረታ መብታቸውን ማስከበር እንደሚችሉም ታውቋል።
የአስተዳደሩ ሰራተኞች በከተማ አስተዳደሩ ተግባራዊ ሊደረግ ስለተዘጋጀው የብቃት ምዘና ፈተና የሚያውቁት ነገር እንደሌለና ዱብዕዳ እደሆነባቸው ምንጮች ጠቁመዋል። ፈተናው በቀጣዮቹ ሳምንታት ውስጥ እንደሚደረግና መጪው ጥር ወር በፊት እንደሚጠናቀቅ ታውቋል። የኢትዮጵያ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ መርሻል ብርሃኑ ጁላ ሰሞኑን ለፋና ቴሌቪዥን በሰጡት ቃለ-መጠይቅ የድሮን ጥቃቱን አስመልክተው
ሲናገሩ “ድሮን እኮ የተሰራው ለጦርነት ነው፣ለውጊያ ነው የገዛነው ልንዋጋበት ነው እንጂ ድሮን አለን እያልን በሚዲያ ልንገልጸው አይደለም የጦር መሳሪያ ነው ልክ እንደክላሹ ክላሽ የአቅሙን ይሰራል ሌላውም የአቅሙን ይሰራል፣ ድሮንም የራሱን ስራ ይሰራል፡፡ ድሮን እኛ የምንጠቀመው ለስብስብ ዓላማ ነው፡፡ ለወታደራዊ ስብብ ኢላማ የሚባል ነገር አለ፡፡ ስብስብ ኢላማ ማለት የጠላት ጠንካራ ቋጠሮ ማለት ነው፡፡ የጽንፈኛ
ስብስብ ስናገኝ በድሮን እንመታለን”ብለዋል፡፡

•  በትግራይ የተከሰተው ድርቅ ከ77ቱ የከፋ ነው ተባለ  

•  25 ህፃናትን ጨምሮ 400 ሰዎች በረሃብ   ሞተዋል  

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ በክልሉ   ከ2 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ለረሃብ መጋለጡን ያስታወቀ ሲሆን፤ እስካሁንም 23 ህጻናትን ጨምሮ 400 ሰዎች በረሃብ መሞታቸውን ጠቁሟል፡፡

በክልሉ ያጋጠመውን የድርቅ አደጋ ለመከላከል ያለመ፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ  22 አባላት ያሉት "አፋጣኝ ምላሽ ለትግራይ" የተሰኘ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እንቅስቃሴ መጀመሩም ተነግሯል፡፡

የ"አፈጣኝ ምላሽ ለትግራይ" ግብረ ሃይል ሰብሳቢ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ   በዛሬው ዕለት  ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ በአሁኑ ሰአት ለረሃብ አደጋ የተጋለጠውን ከ2 ሚሊዮን በላይ ትግራዋይ ህይወት ለመታደግ በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኝ የክልሉ ተወላጅና ወዳጅ እንዲረባረብ ጥሪ አቅርበዋል።  “ሰብዓዊነት የሚሰማው ሁሉ” የእርዳታ እጁን እንዲዘረጋም ጠይቀዋል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የአደጋ መከላከያና ዝግጁነት ኮሚሽን ኮሚሽነር ገብረሕይወት ገ/እግዚአብሔር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ድርቁ በአምስት የትግራይ ክልል ዞኖች ተከስቷል ብለዋል።


“በትግራይ የከፋው ድርቅ የተከሰተው በ1951 እና በ1977 ነበር፤ አሁን ያጋጠመን ከዚያም በላይ ነው፤ በዚህ ድርቅ ምክንያት 2 ሚሊዮን ሕዝብ ተርቧል። 400 የሚሆኑ ሰዎች ባለፈው ወር ብቻ  በረሃብ ምክንያት ሕይወታቸው አልፏል” ብለዋል፤ ኮሚሽነሩ፡፡

የ"አፈጣኝ ምላሽ ለትግራይ" ግብረ ሃይል ድጋፍ ማሰባሰቢያ የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች የሚከተሉር ናቸው፡-

* አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ፡-00112180095-49

* ወጋገን ባንክ፡- 1001077411101

* የኢትዮጵያ  ንግድ ባንክ፡- 1000592420809

”አርቲስት ሀናን እንደምትጠቅመን አምነንበታል” -ድርጅቱ-

አርቲስት ሀናን ታሪክ፤ ድሪመር ፉድ ማኑፋክቸሪንግ ከተሰኘ ታዋቂና ግዙፍ የቻይና ኩባንያ ጋር የብራንድ አምባሳደር ለመሆን በዛሬው ዕለት በስካይላይት ሆቴል  ከስምምነት ላይ የደረሰች  ሲሆን፤ ለድርጅቱ የሁለት ዓመት የብራንድ አምባሳደር ለመሆን 10 ሚሊዮን ብር ተከፍሏታል፡፡

ኩባንያው በኢትዮጵያ ውስጥ በከፍተኛ ኢንቨስትመንት የምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ያቋቋመ ሲሆን ፤ ‹‹ኤስ›› በሚል ብራንድ ያልተለመዱና አዳዲስ የታሸጉ የኬክ ወይንም የጫፋጭ ምግቦችን እያመረተ በመላው አገሪቱ እያከፋፈለ እንደሚገኝ ተጠቅሷል፡፡



ድርጅቱ ይህንን ‹‹ኤስ›› የተሰኘ ብራንድ ምርቶቹን በስፋት ለማስተዋወቅና ስርጭቱን ለማሳደግ የአንድ አመት የኮርፖሬት ብራንድ ፕሮሞሽን እቅድ ማውጣቱን ገልጿል፡፡ በዚህ እቅዱ ውስጥም ታዋቂዋን አርቲስት ሀናን ታሪክን ማካተቱን አስረድቷል፡፡

 ‹‹የኤስን ብራንድ ፕሮሞሽን ውጤታማና ስኬታማ ለማድረግ አርቲስት ሀናን እንደምትጠቅመን አምነንበታል›› ብሏል፤ ድርጅቱ በሰጠው መግለጫ፡፡

የቴሌግራም ቻናልችንን  በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas