Administrator

Administrator

 60 ዘጋቢ ፊልሞች ለተመልካች ይቀርባሉ
  ፌስቲቫሉ በክልል ከተሞችም ይቀጥላል
      በመላው ዓለም ከተሰሩ ምርጥ ዘጋቢ ፊልሞች የተመረጡ 60ዎቹ ለዕይታ የሚቀርቡበት “9ኛው አዲስ ኢንተርናሽናል ዘጋቢ ፊልም ፌስቲቫል” ትላንት በብሄራዊ ሙዚየም የቅርስ ጥናት እና ጥበቃ ባለስልጣን አዳራሽ ተከፈተ፡፡ ፌስቲቫሉ ለአምስት ቀናት እንደሚካሄድ የገለፁት የ“ኢንሺዬቲቭ አፍሪካ” ዋና ዲያሬክተር አቶ ክቡር ገና፤ በቀጣይ ዓመታት ፌስቲቫሉ የራሱን ውድድር አድርጎ ፊልሞችና ፊልም ሰሪዎችን ለመሸለም እንዲሁም ኢትዮጵያዊያን ፊልም ሰሪዎች በዘጋቢ ፊልሞች ስራ የተሻለ ተሳትፎ እንዲኖራቸው እንተጋለን ብለዋል፡፡ ፌስቲቫሉ የተከፈተው በሩት ኢሼል ዳይሬክተርነት በተሰራው “Shoulder Dancing” የተሰኘ ዘጋቢ ፊልም ነው፡፡ እስከ ሰኔ 9 በሚዘልቀው ፌስቲቫል፤ 60 የሚደርሱ ዘጋቢ ፊልሞች ለዕይታ የሚቀርቡ ሲሆን በአዲስ አበባ  በቅርስ ጥናትና ምርምር ማዕከል፤ በሀገር ፍቅር ትንሽዋ አዳራሽ፤ በብሪትሽ ካውንስል እና በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሲዝ ለተመልካቾች ይታያሉ፡፡ የፊልም ፌስቲቫሉ ሰኔ 19 እና 20 ደግሞ በአዳማ፤ ባህርዳር፤ ሃዋሳ እና መቀሌ  ከተሞች እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡
በዘንድሮው ፌስቲቫል በዓለማችን አበይት የመነጋገሪያ አጀንዳዎች ላይ ተመርኩዘው የተሰሩ ዘጋቢ ፊልሞች ተመርጠው መቅረባቸውን በጋዜጣዊ መግለጫው የተናገሩት አቶ ክቡር ገና፤ ከ10 በላይ የፊልም ዳይሬክተሮችን ከተለያዩ አገራት በመጋበዝ በፊልሞቹ ዙሪያ ከተመልካች ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡበት መድረክ መመቻቸቱንም ገልፀዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ከ10ሺ በላይ ታዳሚ የነበረው አዲስ ኢንተርናሽናል ዘጋቢ ፊልም ፌስቲቫል፤ ዘንድሮ ደግሞ በፊልሞቹ ብዛት፤ በሚቀርቡት ዘጋቢ ፊልም ሰሪዎች የብቃት ደረጃና አይነት እንዲሁም በሚያገኘው ተመልካች ብዛት በአፍሪካ ግዙፉ ፌስቲቫል ይሆናል ተብሎ ይገመታል፡፡ በፌስቲቫሉ ላይ ለመሳተፍከመላው ዓለም 500 ፊልሞች አመልክተው እንደነበር የገለፁት አዘጋጆቹ፤ ከግምገማ በኋላ 60 ዘጋቢ ፊልሞች ለዕይታ መመረጣቸውን ጠቁመው “አዲስ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫልን” በአፍሪካ ትልቁ መድረክ ለማድረግ በአበረታች አቅጣጫ ላይ ነን ብለዋል፡፡
ከዘጋቢ ፊልሞቹ ለዕይታ መቅረብ ባሻገር ከመላው ዓለም ከመጡ የፊልም ባለሙያዎች ጋር የጥያቄ እና መልስ እንዲሁም የውይይት መድረኮች ይካሄዳሉ ተብሏል፡፡
ኢትዮጵያውያን ፊልም ሰሪዎች በፌስቲቫሉ ላይ ያላቸው ተሳትፎ አነስተኛ መሆኑን ጠቁመው ዋናው ምክንያትም ዘርፉ ብዙም ንግድ የማይሰራበት በመሆኑ ስለማያበረታታቸው ነው ብለዋል፡፡
በፌስቲቫሉ ከሚቀርቡ ዘጋቢ ፊልሞች መካከል በኢትዮጵያዊያኑ ዳይሬክተሮች ትርሲት አግዝ እና ኃይሉ ከበደ የተሰሩት “የበሬው ውለታ” እና “ትስስር” የሚገኙበት ሲሆን “35 OWS AND A KALASHINIKOV”, “5 MINUTES Of FREEDOM”, “9999”, “At 60 Km/h” የሚሉና ሌሎችም ይታያሉ ተብሏል፡፡

 60 ዘጋቢ ፊልሞች ለተመልካች ይቀርባሉ
  ፌስቲቫሉ በክልል ከተሞችም ይቀጥላል
      በመላው ዓለም ከተሰሩ ምርጥ ዘጋቢ ፊልሞች የተመረጡ 60ዎቹ ለዕይታ የሚቀርቡበት “9ኛው አዲስ ኢንተርናሽናል ዘጋቢ ፊልም ፌስቲቫል” ትላንት በብሄራዊ ሙዚየም የቅርስ ጥናት እና ጥበቃ ባለስልጣን አዳራሽ ተከፈተ፡፡ ፌስቲቫሉ ለአምስት ቀናት እንደሚካሄድ የገለፁት የ“ኢንሺዬቲቭ አፍሪካ” ዋና ዲያሬክተር አቶ ክቡር ገና፤ በቀጣይ ዓመታት ፌስቲቫሉ የራሱን ውድድር አድርጎ ፊልሞችና ፊልም ሰሪዎችን ለመሸለም እንዲሁም ኢትዮጵያዊያን ፊልም ሰሪዎች በዘጋቢ ፊልሞች ስራ የተሻለ ተሳትፎ እንዲኖራቸው እንተጋለን ብለዋል፡፡ ፌስቲቫሉ የተከፈተው በሩት ኢሼል ዳይሬክተርነት በተሰራው “Shoulder Dancing” የተሰኘ ዘጋቢ ፊልም ነው፡፡ እስከ ሰኔ 9 በሚዘልቀው ፌስቲቫል፤ 60 የሚደርሱ ዘጋቢ ፊልሞች ለዕይታ የሚቀርቡ ሲሆን በአዲስ አበባ  በቅርስ ጥናትና ምርምር ማዕከል፤ በሀገር ፍቅር ትንሽዋ አዳራሽ፤ በብሪትሽ ካውንስል እና በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሲዝ ለተመልካቾች ይታያሉ፡፡ የፊልም ፌስቲቫሉ ሰኔ 19 እና 20 ደግሞ በአዳማ፤ ባህርዳር፤ ሃዋሳ እና መቀሌ  ከተሞች እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡
በዘንድሮው ፌስቲቫል በዓለማችን አበይት የመነጋገሪያ አጀንዳዎች ላይ ተመርኩዘው የተሰሩ ዘጋቢ ፊልሞች ተመርጠው መቅረባቸውን በጋዜጣዊ መግለጫው የተናገሩት አቶ ክቡር ገና፤ ከ10 በላይ የፊልም ዳይሬክተሮችን ከተለያዩ አገራት በመጋበዝ በፊልሞቹ ዙሪያ ከተመልካች ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡበት መድረክ መመቻቸቱንም ገልፀዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ከ10ሺ በላይ ታዳሚ የነበረው አዲስ ኢንተርናሽናል ዘጋቢ ፊልም ፌስቲቫል፤ ዘንድሮ ደግሞ በፊልሞቹ ብዛት፤ በሚቀርቡት ዘጋቢ ፊልም ሰሪዎች የብቃት ደረጃና አይነት እንዲሁም በሚያገኘው ተመልካች ብዛት በአፍሪካ ግዙፉ ፌስቲቫል ይሆናል ተብሎ ይገመታል፡፡ በፌስቲቫሉ ላይ ለመሳተፍከመላው ዓለም 500 ፊልሞች አመልክተው እንደነበር የገለፁት አዘጋጆቹ፤ ከግምገማ በኋላ 60 ዘጋቢ ፊልሞች ለዕይታ መመረጣቸውን ጠቁመው “አዲስ ኢንተርናሽናል ፊልም ፌስቲቫልን” በአፍሪካ ትልቁ መድረክ ለማድረግ በአበረታች አቅጣጫ ላይ ነን ብለዋል፡፡
ከዘጋቢ ፊልሞቹ ለዕይታ መቅረብ ባሻገር ከመላው ዓለም ከመጡ የፊልም ባለሙያዎች ጋር የጥያቄ እና መልስ እንዲሁም የውይይት መድረኮች ይካሄዳሉ ተብሏል፡፡
ኢትዮጵያውያን ፊልም ሰሪዎች በፌስቲቫሉ ላይ ያላቸው ተሳትፎ አነስተኛ መሆኑን ጠቁመው ዋናው ምክንያትም ዘርፉ ብዙም ንግድ የማይሰራበት በመሆኑ ስለማያበረታታቸው ነው ብለዋል፡፡
በፌስቲቫሉ ከሚቀርቡ ዘጋቢ ፊልሞች መካከል በኢትዮጵያዊያኑ ዳይሬክተሮች ትርሲት አግዝ እና ኃይሉ ከበደ የተሰሩት “የበሬው ውለታ” እና “ትስስር” የሚገኙበት ሲሆን “35 OWS AND A KALASHINIKOV”, “5 MINUTES Of FREEDOM”, “9999”, “At 60 Km/h” የሚሉና ሌሎችም ይታያሉ ተብሏል፡፡

 በዳንኤል ዓለሙ የተዘጋጀው “ይህን ያውቁ ኖሯል?” የተሰኘ የጠቅላላ ዕውቀት መጽሐፍ ሰሞኑን በገበያ ላይ ዋለ፡፡ በአምስት ምዕራፎች የተከፋፈለው መጽሐፉ፤ የዓለም አስደናቂ ሪከርዶች፣ የፖለቲካውና የስፖርቱ ዓለም አስገራሚና አስደናቂ እውነታዎች እንዲሁም በኢትዮጵያ ታሪክ ዙሪያ የሚያጠነጥኑ መረጃዎችን ይዟል፡፡ በ224 ገጾች የተሰናዳው መጽሐፉ፤ በ50 ብር ከ70 ሳ. ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “ፈተናን የማሸነፍ ጥበብ”፣ “ስኬታማ የፍቅር ህይወት”፣“ገንዘብና ጭንቀት”፣ “ራስን የመለወጥ ምስጢር” እና “ይህን ያውቁ ኖሯል? ቁ.1” የሚሉ መጻህፍትን ማሳተሙን ጠቁሟል፡፡
በደራሲ ድርቡ አደራ የተጻፈው “ሌባ ሻይ” ልብ ወለድ መፅሐፍም ለንባብ የበቃው ባሳለፍነው ሣምንት ነው፡፡ በ400 ገጾች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ በ80 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡ ጸሐፊው ቀደም ሲል “ሐምራዊት”፣ ሽንብሩት” እና “ዲና” የሚሉ መጽሐፍትን ማሳተሙ ይታወሳል፡፡
ለአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ስለ ህዋ ሳይንስ ግንዛቤ ለመስጠት ታስቦ የተዘጋጀውና “አስትሮኖሚ ለልጆች” የተሰኘው መጽሐፍም ከሳምንቱ የህትመት ትሩፋቶች አንዱ ሆኗል፡፡ በፊዚክስ የማስተርስ ድግሪ እንዳለው በጠቆመው አክመል ተማም የተሰናዳው መጽሐፉ፤ ዩኒቨርስ፣ጋላክሲዎችና ሶላር ሲስተም በሚሉ ሶስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ የቀረበ ሲሆን በ28 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ የትምህርት ባለሙያው አክመል፤ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ርዕሰ ጉዳይ ለሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችና ለሌሎች “ዩኒቨርስ” የተሰኘ መጽሐፍ አሳትሞ ማቅረቡም ታውቋል፡፡

የገጣሚ ደምሰው መርሻ በሙዚቃ የተቀናበሩ የግጥም ሥራዎች “ያልታየው ተውኔት” በሚል ርዕስ በሲዲ የተዘጋጀ ሲሆን የፊታችን ረቡዕ ከ11 ሰዓት ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ይመረቃል፡፡
17 ግጥሞችን ታዋቂው ሙዚቀኛ ጆርጋ መስፍን ያቀናበረለት ሲሆን 1 ግጥም ደግሞ በጥላሁን ጊዮርጊስ (ፒጁ) መቀናበሩን ገጣሚው ጠቅሶ፣ኤርምያስ ዳኜ የሁሉንም ሚክሲንግ እንደሰራለት ተናግሯል፡፡
የሲዲውን ሽፋን ሰዓሊ ዳንኤል ታዬ ሰርቶልኛል ብሏል- ገጣሚው፡፡   
በሒልተን ሆቴል በሚካሄደው የግጥም ሲዲ የምረቃ ሥነሥርዓት ላይ አንጋፋው ሃያሲ አብደላ እዝራ በግጥሞቹ ላይ ሒሳዊ ዳሰሳ የሚያቀርብ ሲሆን ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም፣ አርቲስት ፈለቀ አበበና ሌሎችም ለታዳሚያን የግጥም ሥራዎችን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ ደምሰው መርሻ በተለያዩ የጥበብ መድረኮች ላይ ግጥሞቹን አዘውትሮ በማቅረብ የሚታወቅ ተወዳጅ ገጣሚ ሲሆን የ“ግጥም በጃዝ” ቡድንም አባል ነው፡፡

Saturday, 13 June 2015 15:31

የፍቅር ጥግ

ልክ ነገ እንደሌሌ ያህል አፍቅር፡፡ ነገ ከመጣ ደግሞ እንደገና አፍቅር፡፡
ማክስ ሉሳዶ
መልካም ትዳር የደግነት ውድድር ነው፡፡
ዲያኔ ሳውዬር
ደስተኛ ትዳር ሁልጊዜ አጭር የሚመስል ረዥም ጭውውት ነው፡፡
አንድሬ ማውሮይስ
በጋብቻ ውስጥ ደስታን ማግኘት ሙሉ በሙሉ የዕድል ጉዳይ ነው፡፡
ጄን ኦዩስተን
(Pride & Prejudice)
“ፍቅር”፤ አንድ ሰው መጥቶ ትርጉም እስኪሰጠው ድረስ ተራ ቃል ነው፡፡
ያልታወቀ ደራሲ
አንዱ ጉንጭ ይሰጣል፤ ሌላው ይስማል፡፡ አንዱ ገንዘብ ይሰጣል፤ ሌላው ያጠፋል፡፡
ጆርጅ በርናርድ ሾው
ጋብቻ ግራ የሚያጋባ ነው፡፡ ባለቤታቸውን (ግማሽ ጐናቸውን) እንዲቆጣጠሩ ህጋዊ መብት ለግለሰቦች የሚሰጥ ዓይነት ፈቃድ ነው፡፡
ጄስ ሲ ስኮት
ሁሉም ጋብቻዎች ትዳሮች መንግስተ ሰማያት ነው ይላሉ፡፡ ግን እኮ ነጐድጓድና መብረቅም የሚፈጠሩት እዚያው ነው፡፡
ክሊንት ኢስትውድ
ሰዎች በትዳር የሚዘልቁት ስለፈለጉ እንጂ በሮች ቁልፍ ስለሆኑባቸው አይደለም፡፡
ፖል ኒውማን
ማንም ሴት፤ እናቱን የሚጠላ ወንድ ፈጽሞ ማግባት እንደሌለባት በደንብ አውቃለሁ፡፡
ማርታ ጌልሆርን
ትዳር የተሃድሶ ትምህርት ቤት አይደለም፡፡
ኦን ላንደርስ
ደስተኛ ወንድ የወደዳትን ሴት ያገባል፡፡ የበለጠ  ደስተኛ ወንድ ደግሞ ያገባትን ሴት ይወዳል፡፡
ሱዛን ዳግላስ
የደስታን በሮች የሚከፍተው እናት ቁልፍ ፍቅር ነው፡፡
ኦሊቨር ዌንዴል ሆልሜስ
ትዳር ደስተኛ አያደርግህም፤ አንተ ነህ ትዳርህን ደስተኛ የምታደርገው፡፡
Drs. Les and Leslie Parrott 

  ለደራሲው 10ኛው መጽሐፉ ነው
   “ዴርቶጋዳ” በተሰኘው የመጀመሪያ ልብ ወለድ መፅሃፉ ከፍተኛ ተነባቢነትና ዕውቅናን የተቀዳጀው ወጣቱ ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ፤ “ሜሎስ” የተሰኘ አዲስ ልብ ወለድ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ ያበቃ ሲሆን 10ኛ መጽሃፉ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል፡፡ በ280 ገፆች የተቀነበበውን መጽሐፍ፤የዲዛይንና ህትመት ሥራ ያከናወነው ራሱ ደራሲው ያቋቋመው ዴርቶጋዳ ማተሚያ ድርጅት ነው፡፡ “ሜሎስ” በ60 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
ይስማዕከ ከዚህ ቀደም “የወንድ ምጥ”፣ “ዴርቶጋዳ”፣ “የቀንድ አውጣ ኑሮ”፣ “ራማቶሓራ”፣ “ተልሚድ”፣ “ተከርቸም”፣ “ዣንቶዣራ”፣ “ክቡር ድንጋይ” እና “ዮራቶራድ” የተባሉ መጽሐፍትን ያሳተመ ሲሆን  አብዛኞቹም በከፍተኛ ቅጂ በመሸጥ ለአሳታሚውም ሆነ ለጸሃፊው ዳጎስ ያለ ገቢ ማስገኘታቸው ይታወቃል፡፡ በተለይ “ዴርቶጋዳ” በጠቅላላው ወደ 200ሺ የሚጠጉ ቅጂዎች በመታተም በኢትዮጵያ የሥነጽሁፍ ህትመት ታሪክ አዲስ ሪከርድ ማስመዝገቡን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ አንዳንድ የሥነጽሁፍ ባለሙያዎችና ሃያሲያን፣ ደራሲው ከመጀመሪያው ሥራው በኋላ ያወጣቸው ተከታታይ  መጻህፍት እያሽቆለቆሉ መምጣታቸውን ቢናገሩም እስካሁን በሥራዎቹ ላይ የሰላ ሂስ የሰነዘረ ወይም ሂሳዊ ጽሁፍ ያቀረበ የለም፡፡

  - አንድ ደብዳቤው ከ3 አመታት በፊት 3ሚ ዶላር ተሽጧል
   ታዋቂው የፊዚክስ ሊቅ አልበርት አንስታይን በተለያዩ ጊዜያት የጻፋቸው ደብዳቤዎች በቀጣዩ ሳምንት ሎሳንጀለስ ውስጥ ለጨረታ እንደሚቀርቡና ከ1 ሚሊዮን ዶላር በላይ ይሸጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዘ ቴሌግራፍ ዘገበ፡፡
ለጨረታ የሚቀርቡት ደብዳቤዎች በአንስታይን የእጅ ጽሁፍ የተጻፉና በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ እንደሆኑ የጠቆመው ዘገባው፣ ከደብዳቤዎቹ መካከልም አንስታይን ለልጆቹና ሃንስ እና ኤድዋርድ እንዲሁም ለቀድሞ የትዳር አጋሩ ሜሊቫ ማሪክ የጻፋቸው ይገኙበታል ብሏል፡፡
አልበርት አንስታይን በደብዳቤዎቹ ፈጣሪን፣ ፖለቲካን፣ ታሪክን፣ ሳይንስንና ሌሎች ጉዳዮቹን የተመለከቱ ሃሳቦቹን እንዳንጸባረቀና የሳይንቲስቱን የአመለካከት ጥልቀት የሚያሳዩ አስገራሚ ሰነዶች እንደሆኑ፣ ጨረታውን ያዘጋጀው የሎሳንጀለስ አጫራች ኩባንያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ጆሴፍ ማዳሌና ተናግረዋል፡፡
አንስታይን ሃይማኖትን በተመለከተ የጻፈውና ጎድ ሌተር በመባል የሚታወቀው ደብዳቤ እ.ኤ.አ በ2012 ለጨረታ ቀርቦ በ3 ሚሊዮን ዶላር መሸጡንም ዘገባው አስታውሷል፡፡

 የዚምባቡዌው ፕሬዚደንት ሮበርት ሙጋቤ፤ የእንጀራ ልጅ ረስል ጎሬራዛ ባለፈው የካቲት በመዲናዋ ሃራሬ ማንነቱ ያልተገለጸን ግለሰብ በመኪናው ውስጥ ገድሏል በሚል ተከሶ ፍርድ ቤት መቅረቡንና ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ 800 ዶላር እንዲከፍል እንደተፈረደበት ቢቢሲ ዘገበ፡፡
የቀዳማዊት እመቤት ግሬስ ሙጋቤ የበኸር ልጅ የሆነው የ31 አመቱ ጎሬራዛ፣ በሃራሬ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርቦ ድርጊቱን መፈጸሙን በማመን እንደተጸጸተ ገልጾ፣ ይቅርታ እንዲደረግለት ጠይቋል። ፍርድ ቤቱም የመንጃ ፈቃዱን ነጥቆ እስር ቤት ሊወረውረው ቢያስብም፣ መጸጸቱን አይቶ በገንዘብ ቅጣት ብቻ እንዳለፈው አስታውቋል፡፡
ግለሰቡ በእስር አለመቀጣቱ በርካታ የመዲናዋ ነዋሪዎችን እንዳስደነገጠ የገለጸው ዘገባው፣ በተመሳሳይ ወንጀል የተከሰሱ ሌሎች ወንጀለኞች በሁለት አመታት እስር እንደተቀጡ አስታውሷል፡፡
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ማስተላለፉን ተከትሎ የእስር ቤቱ ሃላፊዎች ተከሳሹን በደንቡ መሰረት ከፍርድ ቤቱ ወደ ነበረበት እስር ቤት በመውሰድ የተቀጣውን የገንዘብ ቅጣት ከከፈለ በኋላ እንዲለቀቅ ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ፣ የመንግስት የደህንነት አካላት ሊከላከሏቸው እንደሞከሩም ዘገባው አክሎ ገልጧል።

 - በእስር ቤቱ የ150 አመት ታሪክ ሲያመልጡ የመጀመሪያዎቹ ናቸው
  - ድንበር አቋርጠው ወደ ካናዳ ሳይገቡ አልቀሩም ተብሏል
     የኒውዮርክ አገረ ገዢ አንድሪው ኮሞ ባለፈው አርብ ሌሊት ዳኔሞራ በተባለችው ከተማ ከሚገኝ እስር ቤት ያመለጡትን ሁለት ነፍሰ ገዳዮች በተመለከተ መረጃ ለሰጣት ሰው፣ ግዛቲቱ 100 ሺህ ዶላር ወሮታ እንደምትከፍል ማስታወቃቸውን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
ሪቻርድ ማት እና ዴቪድ ስዊት የተባሉት እነዚህ አደገኛ ነፍሰ ገዳዮች ከፍተኛ ጥበቃ በሚደረግለት በዚህ እስር ቤት የ150 አመታት ታሪክ አምልጠው መጥፋት የቻሉ የመጀመሪያዎቹ ታራሚዎች ናቸው ያለው ዘገባው፤የታሰሩበትን ክፍል የብረት ግድግዳ በመቁረጥ በፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች ውስጥ ለውስጥ ሾልከው እንዳመለጡ ገልጧል፡፡
“እነዚህ ነፍሰ በላዎች አሁንም የከፋ ወንጀል ከመፈጸም ወደኋላ የማይሉ ናቸው” ብለዋል፤አገረ ገዢው አንድሪው ኮሞ፣ ምናልባትም እስረኞቹ ድንበር አቋርጠው ወደ ካናዳ ሳይገቡ እንዳልቀሩ ግምታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ሁለቱ እስረኞች ማምለጣቸውን ተከትሎ፣ ፖሊስ በአካባቢው የሚገኙ ጎዳናዎችን ዝግ አድርጎ ጉዳዩን በጥብቅ መመርመሩንና  በግዛቲቱ የሚደረገው የደህንነት ፍተሻና ፍለጋ በከፍተኛ ሁኔታ ተጧጡፎ መቀጠሉን የገለጸው ዘገባው፣ ከ200 በላይ ፖሊሶችም በአነፍናፊ ውሾችና በአየር ላይ አሰሳ በታገዘ እስረኞቹን የማደን ስራ መጠመዳቸውን አስረድቷል፡፡
ሪቻርድ ማት አንድን ግለሰብ በማገትና በመግደል ወንጀል ተከሶ የ25 አመታት የእስር ቅጣት ላይ እንደነበርና፣ ዴቪድ ስዊትም አንድን የፖሊስ ሃላፊ በመግደሉ የእድሜ ልክ እስር ፍርደኛ እንደነበር ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡