Administrator

Administrator

አንድ ንጉሥ የመሞቻቸው ሰዓት ሲደርስ ሁለት ወንዶች ልጆቻቸውንና አንዲት ሴት ልጃቸውን ጠርተው፤ “ልጆቼ፤ እንግዲህ ዕድሜዬ እየገፋ፣ ጉልበቴ እየላመ፣ አቅሜም እየደከመ የመጣበት ሰዓት ነውና ከመንግሥቴ የት የቱን መውረስ እንደምትመርጡ ሀሳብ እንድትሰጡኝ እፈልጋለሁ” አሉ፡፡
ታላቅ ወንድም ምንም ሀሳብ ሳይሰጥ ዝም አለ፡፡
ሁለተኛው ወንድም፤
“አባቴ ሆይ! እርስዎ ራስዎ ይሄን ለትልቁ፣ ይሄን ለትንሿ፣ ይሄን ለትንሹ አውርሻለሁ ቢሉን አይሻልም ወይ?” ሲል ሃሳቡን አቀረበ፡፡
ሴቷ ልጅ ደግሞ፤
“አባቴ ሆይ! እኔ የምመኘውንና የማስበውን ብናገር፣ ሌሎቹም የሚያስቡትን ባውቅ በጣም ደስ ይለኛል፡፡ ስለሆነም አባቴ ያሉትን እደግፋለሁ” አለች፡፡
ንጉሡም፤
“አያችሁ ልጆቼ፤ አሁን ከተናገራችሁት የተረዳሁት ሦስት ነገር ነው፡፡
ከመጀመሪያው ልጄ - ዝምታን አየሁ፡፡
ከሁለተኛው ልጄ - ኃላፊነትን ለሌሎች መጣልን አየሁ፡፡
ከሦስተኛው ልጄ - በራስ መተማመንን ነው ያነበብኩት፡፡
በእርግጥ ያየሁዋቸው ሦስት ነገሮች የየራሳቸው ዋጋ አላቸው፡፡ ዝምታ ወቅቱን ከጠበቀ ዋና  ነገር ነው፡፡ ኃላፊነትን ለሌሎች መስጠት አቅምን ከማወቅና የሌሎችን ዋጋ ከማወቅ የመነጨ ከሆነ እጅግ ጠቃሚ እሴት ያለው ነው! በመጨረሻም በራስ መተማመን ከሁሉም የላቀ እሴት ነው፡፡ ያለራስ መተማማመን፤ መንግሥቴን ወዴትም ልታዘልቁት አትችሉም፡፡ በራስ መተማመን የሚመጣው ዕውቀት ሲኖር ነው፡፡ ዕውቀት የሚመጣው ለመማር ፈቃደኛ ከመሆን፣ ከልምድ ራስን ከማሻሻል፤ ሁልጊዜ ለለውጥ ዝግጁ ከመሆን ነው፡፡ እነዚህን ሁሉ አጢኜና መርምሬ ሳስተውል፣ መንግሥቴን መውረስ ያለባት ሴቷ ልጄ ናት” ሲሉ ደመደሙ፡፡
***
የአንድ ህብረተሰብ ዋና ኃይል ልበ - ሙሉነትና በራስ መተማመን ነው! የሀገራችንን የህብረተሰብ አወቃቀር ስናስተውል፤ በተለይ አሁን በደረስንበት የዕድገት ደረጃ፤ የሴቶችን ከባድ ሚና፣ ከባድ ጫና እና ከባድ የሀገር እናትነት ስሜት ማጤን አይሳነንም፡፡ ከተረቶቻችን፣ ከምሳሌዎቻችንና ከጥቅሶቻችን በሰፊው እንደምንረዳው፤ የሴትን የበታችነት አጠንክረው የሚያሰምሩ ቃለ - ኃይሎች እንዳሉ አይካድም፡፡
“በለው በለው ሲል ነው የወንድ አብነቱ
ሴትም ትዋጋለች ከረጋ መሬቱ”
የሚለውን አንድ ምሣሌ ብናይ እንኳ፣ ጉዳችንን በቀላሉ ይነግረናል፡፡ “ለፍታ ለፍታ ሴት ወለደች”ን ስናይ፣ ከንቀታችን ሶስት አራት እጥፍ የሴቶች ጫንቃ ላይ እያሳረፍን እንደከረምን ለማወቅ አያዳግትም፡፡ “ምን ሴት ብታውቅ በወንድ ያልቅ” የሚለውን አደገኛ ካንሠር አከል በሽታ ማስወገድ ይገባናል!! ሴቶችን የረሳ፣ ሴቶችን የናቀ፣ ሴቶችን ተሳታፊ ያላደረገ ሥርዓት ይዞ የትም አያደርስም፡፡ “እንስራዋን ጥላ ወንዝ ወረደች” የሚለው ተረትም አሁንም በሴት ጫንቃ ላይ የተንተራሰ ይሁን እንጂ ቁምነገሩን አንስተውም፡፡
ሀገራችን በተለያዩ የሥራና የህይወት ዘርፎች ያለ ሴት በሣልና ጠንካራ ተሳትፎ ካለመችበት ልትደርስ አትችልም፡፡ ከዚህ አንፃር ሴቷን የለውጥ መዘውር ለማድረግ ለአፍታም ሳንታክት ማሰብና ተግባራዊ ማድረግ ወሳኝ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በመፈክር ላይ በመንጠልጠልና በቀለም በማድመቅ ብቻ የትም እንዳልደረስን አይተነዋል፡፡ በሌላ በኩል ራሳቸውን ለትግል ያበቁ፣ የታገሉና ያሸነፉ ሴት ፋና - አብሪዎች፣ ለድል የበቁት አደራጅተው እንደሆነ እናውቃለን፡፡  በተለያዩ የሙያ ዘርፎች፣ በንግድና ኢንዱስትሪ እንዲሁም በባህላዊ ትሥሥር ዙሪያ ገፍተው ብቅ ብቅ ያሉቱ ምን ያህል ለውጥ ማምጣት እንደቻሉ እያየን ነው፡፡ ገና ግን ብዙ ማደግ፣ በየዘርፉ ብዙ መብቀል፣ ብዙ ማፍራት፣ ብዙ ማልማት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ሌላውም የህብረተሰብ ክፍል እንቅስቃሴያቸውን ከአንጀቱ ማገዝና ማጐልበት፣ ትልቅ አስተዋፅዖ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በሙያና በብዙሃን ማህበራት፣ በቤተሰብና በግል ህይወት ውስጥ ሚናቸውን ማረጋገጥ ቁልፍ ጉዳይ ነው፡፡ ብርቱ ጉዞ ይጠብቀናል፡፡ በህብረተሰባችን ውስጥ ሁሉም ቦታ ቦታ እንዳለው አንርሣ! “ቦታ ቦታችሁ ግቡ ቢባል አሎሎ ወደ ጅረት፣ ኩበት ወደ አክንባሎ” የሚባለውም በየቦታው ሁሉም ባለዕሴት መሆኑን ሲነቁጥ ነው!  


  “ ቅ/ ሲኖዶሱ በአድባራት ሓላፊዎች ላይ ያሳለፈው ውሳኔ
          ሕገ መንግሥቱን የሚፃረር ነው ”   /ፓትርያርኩ/
     የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ፣ ‹‹የቤተ ክርስቲያን አባቶችና ቤተ ክርስቲያን ዕውቅና በሰጠችው ማኅበር ላይ ተገቢ ያልኾነ ቃል ተናግረዋል›› ባላቸው አንዳንድ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራት አስተዳዳሪዎች ላይ ያሳለፈው ውሳኔ አፈጻጸም ‹‹ሕገ መንግሥቱንና ሰብአዊ መብትን የሚፃረር ነው›› በሚል ፓትርያርኩ ማገዳቸው ተገለጸ፡፡
ፓትርያርኩ ባለፈው ኅዳር 30 ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በጻፉት ደብዳቤ ‹‹አፈጻጸሙ እንዲቆይ›› በማለት ያገዱት የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትና በጠቅላይ ቤተ ክህነት በተካሔዱ ጉባኤዎች÷ ‹‹ተገቢ ያልኾነ ቃል ተናግረዋል፤ ይህም አነጋገር ጉባኤውን ቅር አሰኝቷል፤›› ያላቸው የአድባራት አስተዳዳሪዎች፤ቀኖናዊ ምክርና ተግሣጽ እንዲሰጣቸው በአንድ ድምፅ ተስማምቶ ያሳለፈው እንደነበር ተጠቅሷል፡፡
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ በመንበረ ፓትርያርክና በጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሾች በተካሔዱት ስብሰባዎች የቤተ ክርስቲያኒቱን መልካም አስተዳደርና ወቅታዊ ችግሮች የተመለከቱ የጉባኤተኞች አስተያየቶችና ሐሳቦች መቅረባቸውን በደብዳቤያቸው ያስታወሱት ፓትርያርኩ፤ ተሰብሳቢዎቹ ሐሳባቸውንና አስተያየታቸውን በግልጽ መናገራቸውና አሉ የተባሉ ችግሮች መፍትሔ እንዲያገኙ መጠየቃቸው ‹‹በዓለም አቀፍ ደረጃም ኾነ በሀገራችን ለሕዝብ የተፈቀደ ዴሞክራሲያዊ መብት መኾኑ አያጠያይቅም›› ብለዋል፡፡ ሐሳባቸውንና አስተያየታቸውን በግልጽ ያቀረቡ ሰዎችን መገሠጽና መውቀስም ሕገ መንግሥቱን እንደሚፃረር ጠቁመዋል፡፡
ጉባኤዎቹ በቤተ ክርስቲያን ጠሪነት የተካሔዱ እንደነበሩና ተሰብሳቢዎቹም የቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት፣ አገልጋዮችና ሠራተኞች መኾናቸውን ፓትርያርኩ ጠቅሰው÷ የጎደለው እንዲሟላ የጠመመው እንዲቃና ያላቸውን አስተያየት በማቅረባቸው ተግሣጽና ማስጠንቀቂያ እንዲሰጣቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳለፈው ውሳኔ ‹‹የስብሰባ ነፃነትንና መብትን ነፍጎ ሐቁ እንዳይነገር›› የሚከለክልና ውጤቱም ‹‹ጊዜ ያለፈበትን አፈና በማንገሥ ችግሮች ተባብሰው እንዲቀጥሉ የሚያደርግ ነው›› ብለዋል፡፡ “በውይይቱ ወቅት ‹‹የዳኅፀ ልሳን ወለምታ›› አጋጥሞም ከኾነ በወቅቱ ማብራሪያና ማስተካከያ ይሰጥበታል እንጂ እንደ ከባድ ጥፋት ተቆጥሮ ሰዎች ሊገሠጹበትና ሊወቀሱበት አይገባም፤ ሕግም አይፈቅድም፡፡” ሲሉ ገልጸዋል - በደብዳቤያቸው፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ‹‹ተገቢ ያልኾነ ቃል ተናግረዋል›› ያላቸው አንዳንድ የአድባራት አስተዳዳሪዎች በጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል ቀርበው ቀኖናዊ ምክርና ተግሣጽ እንዲሰጣቸው ያሳለፈው ውሳኔ ‹‹ሕግንና ሰብአዊ መብትን የሚፃረር›› ብቻ ሳይኾን ‹‹ትልቁን ጉባኤ በታሪክና በሕግ ዐዋቂዎች ዘንድ ግምት ውስጥ የሚጥለው እንዳይኾን አቡነ ማትያስ አስጠንቅቀው፡፡ ቅዱስ ሲኖዶሱ ጉዳዩን እንደገና በጥልቀትና ከሕግ አንጻር ፈትሾ እንዲያጤነው በማለት አፈጻጸሙ እንዲቆይ አስታውቀዋል፡፡
በሕገ ቤተክርስትያን ት/ሲኖዶሱ በሙሉ ድምፅ ተስማምቶ ያሳለፈውን ውሳኔ ፓትርያርኩ የማገድ ሥልጣን እንደሌላቸው ያመለክታል፡፡ ሕገ መንግሥቱ ከተጠቀሰበት አግባብ አኳያም፣ “ቤተ ክርስቲያናችን በቂ ሕግጋት አሏት፤ እነዚህ ሕግጋት ማዕከሉ ተጠብቆ ሊሠራባቸው ይገባል፤” ሲልም ቅ/ሲኖዶሱ አሳስቧል፡፡
ባለፈው መስከረም መጨረሻ “የቤተ ክርስቲንን አስተዳደራዊ አስተሳሰብ ማበልጸግ” በሚል መርሕ በተካሔደው ስብሰባ አንዳንድ የአድባራት አስተዳዳሪዎች፤ ‹‹ፈጣሪ የለም ይላል፤ አሸባሪና አክራሪ ነው፤›› በማለት ቤተ ክርስቲያኗ ዕውቅና የሰጠችውን ማኅበረ ቅዱሳንን ከዓለም አቀፍ ጽንፈኞች ጋራ እያመሳሰሉ መወንጀላቸው ተገቢ እንዳልኾነና የማኅበሩ አገልግሎት ለቤተ ክርስቲያን አስፈላጊ እንደኾነ ቅዱስ ሲኖዶሱ አረጋግጧል፡፡
‹‹ቆራጣ ደብዳቤ ይበቃዋል፤ ከመንግሥት ጋራ በመተባበር እስከ ጫፍ አድርሱልን፤ በቶሎ ቁረጡት›› እያሉ መጠየቅ፤ ሊቃነ ጳጳሳቱንም “ከፈለጉ ቆባቸውን አስቀምጠው ወደዚያው ይግቡ” እያሉ መዝለፋቸውስ በምን መመዘኛ ነው ዴሞክራሲያዊና ሕገ መንግሥታዊ የሚኾነው በማለት የሚገልጹ የስብሰባው ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ ፓትርያርኩ የውሳኔውን አፈጻጸም ማገዳቸው፣ አድሏዊ እንደሚያደርጋቸውና በካህናቱና በምእመናኑ ዘንድ መንፈሳዊ አባትነታቸውንና ታማኝነታቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባው እንደሚኾን ጠቁመዋል፡፡

ኤልጂ ኩባንያ በኦሮሚያ ክልል ሰንዳፋ አካባቢ ለሚገኘው ሙዳ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የተለያዩ የትምህርት መርጃ መሳርያዎች ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ፡፡
ኤልጂ ከወርልድ ቱጌዘር፣ መንግስታዊ ያልሆነ ዓለም አቀፍ የልማትና የግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር እ.ኤ.አ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በሰንዳፋ አካባቢ ዱግዴራ በተሰኘ መንደር የማህበረሰብ ልማት ፕሮጀክት በመተግበር ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል፡፡ ፕሮጀክቱ “ኤልጂ ሆፕ ቪሌጅ” የሚል መጠሪያ ያለው ሲሆን የመንደሩ ነዋሪዎች እራሳቸውን ለዘለቄታው እንዲችሉ በእርሻና በእንስሳት እርባታ ስልጠናና ድጋፍ የሚያገኙበት ነው ተብሏል፡፡
ኤልጂ ግብርና ላይ ከሚያደርገው ድጋፍ በተጨማሪ የተለያዩ የልማት ስራዎችን በማስፋፋት በአካባቢው ለሚገኙ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ የቆየ ሲሆን በሰንዳፋ ወረዳ ለሚገኙ አራት ት/ቤቶች ከማስፋፊያ ግንባታዎች ጀምሮ እስከ ትምህርት መርጃ መሳሪያዎች ድረስ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ኤልጂ በስሩ በሚገኘው ኢኖቴክ ኩባንያ አማካኝነት ላለፉት ወራት ለሙዳ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ድጋፍ ሲያደርግ የቆየ ሲሆን አሁን ደግሞ ት/ቤቱን በማደስ እንዲሁም ለተማሪዎች ቦርሳ፣ የመማሪያ መፃህፍት፣ የመማሪያ ዴስኮች፣ ወንበሮችና ጥቁር ሰሌዳዎችን ባለፈው ሕዳር ወር መጨረሻ በት/ቤቱ በተሰናዳው ዝግጅት አበርክቷል፡፡
ት/ቤቱ ከከተማ ባለው ርቀት የተነሳ በአዲስ መልክ ለመገንባትና በተፈለገው መልኩ ለትምህርት አመቺ ለማድረግ አስቸጋሪ ቢሆንም የመማሪያ ክፍሎቹን ባሉበት በማደስ፣ የቀድሞዎቹን አሮጌና ለመማር ማስተማር አመቺ ያልነበሩትን ክፍሎች የተሻለ ብርሃን እንዲያገኙ፣ እንዲሁም የክፍሎቹ ወለሎችና ግድግዳዎች እንዲፀዱ ተደርጓል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የተማሪዎች መፀዳጃ በመማሪያ ክፍሎቹ አቅራቢያ እንዲሆን በማድረግ ከዚህ ቀደም ተማሪዎች መፀዳጃ ለማግኘት እስከ 10 ደቂቃ ይወስድባቸው የነበረውን የእግር ጉዞ አስቀርቷል ተብሏል፡፡

Saturday, 13 December 2014 11:24

የሀገሩን ሰርዶ በሀገሩ በሬ

በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ማህበራት ከማህበራዊ ህይወት ጅማሮ አንስቶ የሚሰፈር ዕድሜ አላቸው:: በመሆኑም ሰዎች ከአንድ በላይ ሆነው መኖር ከጀመሩበት ጊዜ እስካሁን ድረስ ህልውናቸው ጉልህ ሆኖ ይታያል፡፡ ዓይነታቸውና ቅርፃቸውም እንደ ዕድሜያቸው ሁሉ ለአሀዝ አዳጋች ነው፡፡ለዚህ ጽሁፍ ዓላማ ሲባል ሊቃኙ የታሰቡት በሰዎች የማህበራዊ ህይወት ውስጥ አይነተኛ ድርሻ ያላቸው ማህበራትን ነው፡፡ እነዚህ ማህበራት እንደ እድር፣ ዕቁብ፣ ደቦ፣ አፎሻ፣ ጅጌ፣ ወዘተ በመባል ይታወቃሉ፡፡ እነዚህና መሠል ማህበራት የሰዎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሰርዶ ከሥሩ በመመንገል የማህበራዊ ህይወታችን በሬዎች ለመሆናቸው የሚከራከር ቢኖር አንድም ጣዕማቸውን ያልቀመሰ አልያም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ አቀፍ ማህበራዊ ትሥሥር የከነፈ ሊሆን ይችላል፡፡
የሁላችንም የህይወት ተሞክሮ ከተለያዩ የባለሙያዎች ጥናቶች ጋር ተዳምሮ የሚያሳየን ዕውነታ - ዕድሮችና ማህበራት የሰዎችን የመረዳዳት፣ የመተጋገዝ፣ አብሮ የመስራት፣ አብሮ የማዘን፣ አብሮ የመደሰት፣ ወዘተ እሴት እያጎሉ ዘመናትን መሻገራቸውን ነው፡፡
አዎ! በርግጥም ማህበራቱ በዕለት ተዕለት የማህበራዊ ህይወታችን ጉልህ ድርሻን ይጫወታሉ፡፡ ከዚህም አልፎ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተወሰኑት በማህበረ-ኢኮኖሚያዊ ልማት /socio-economic/ ዘንድ አንቱ የተባለ አስተዋጽዖ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ለምሳሌ በኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር፣ በአካባቢ ንፅህናና ጥበቃ፣ በግጭት አፈታት፣ በህፃናት አስተዳደግ፣ ወዘተ ሚዛን የሚደፋ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ ለአብነት ያህል በኢየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት ድጋፍና እገዛ አማካኝነት ወደ አርባ የሚጠጉ ማህበራት ባለፉት ሁለት ዓመታት የሚከተሉትን ተግባራት አከናውነዋል፡፡
ሁለት ሽህ አምስት መቶ ያህል አስዳጊዎች የተለያዩ የንግድ ሥራ ክህሎት ሥልጠና በመስጠትና ከፊል ብድር ድጎማ በማቅረብ የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ህይዎት እንዲያሻሽሉ አግዘዋል፤
አምስት ሺህ ለሚደርሱ ህፃናት የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ደግፈዋል፤
ሁለት ሺህ ያህል አሳዳጊዎቻቸውን ያጡና ተጋላጭ ህፃናት የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ አድርገዋል፤
አንድ መቶ ስልሳ አምስት መደበኛ ትምህርት ቤት መግባት ያልቻሉ ህፃናትን የአማራጭ መሠረታዊ ትምህርት ተጠቃሚ አድርገዋል፤
የከፍተኛ ትምህርት ዕድል ላላገኙ ሰባ ስድስት ህፃናት አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ የከፍተኛ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ አድርገዋል፤
ከአምስት መቶ በላይ የቤተሰብ አባላት የሚኖሩባቸውን ሃምሳ ሁለት ቤቶች አስጠግነዋል፤
በከፍተኛ ችግር ላይ ለነበሩ ሁለት ሺህ አምስት መቶ ያህል ህፃናት የአልባሳትና መሰል ድጋፎችን አድርገዋል፤
በተጨማሪም ለስድስት መቶ ያህል ሥራ አልባ ወጣቶች የተለያዩ የሙያ ሥልጠናዎችና የመሥሪያ ካፒታል ብድር በማገዝ ወደ ሥራ አሰማርተዋል፤
ይህንና መሠል ተግራባትን ያከናወኑ ማህበራት የነበሩ፣ ያሉና ምናልባትም የሚኖሩ ማህበራት ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥ ዕድሮች፣ የእድር ህብረቶች፣ የአንድ አካባቢ ተወላጆች ማህበር፣ የተወሰነ ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር፣ የመንግሥት ሠራተኞች በራሳቸው አነሳሽነት ለሌሎች ድጋፍ ለማድረግ የተቋቋሙ ማህራት፣ ወዘተ ይገኙበታል፡፡
እነዚህ ማህበራት በውስጣቸው የተሰባሰቡ በርካታ አባላት ያሏቸው ሲሆን በህብረተሰቡ ዘንድ በጣም ተቀባይነት ያላቸው፣ በመተማመንና በመተሳሰብ የሚሰሩ፣ የማህበረሰብ ጥቅምን የሚያስቀድሙ፣ ዲሞክራሲያዊነት - ግልፅነት - ተጠያቂነትን ያሰፈኑ፣ የሚያገለግሉትን የማህበረሰብ ክፍል ለማገልገል ቆርጠው የተነሱና በትትርና የሚሰሩ ማህበራት ናቸው፡፡ እንዲያው ባጠቃላይ ማህበራቱ ተገቢው እገዛ ቢደረግላቸው የሀገራችንን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሰርዶ ሲቻል የመመንገል አልያም የማጠውለግ ትልቅ አቅም ያላቸው የማህበረሰብ እንቁ ሀብት ናቸው፡፡
ይሁን እንጂ የሚመለከታቸው አካላት በተለይም መንግሥት፣ ለጋሽ ድርጅቶች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ ራሱ ማህበረሰቡ ማህበራቱን በሚፈለገውም ሆነ በሚጠበቀው መጠን ሲጠቀሙባቸው አይታዩም፡፡ ኢየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት የእነዚህ የማህበረሰቡ ምስርት ተቋማትን ልማታዊ አስተዋፅኦ አበክሮ በመገንዘብ በተለይም ካለፉት 15 ዓመታት ጀምሮ በማህበራት ዙሪያ በሥፋት በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በላይ ጋይንት፣ አውራ አምባ፣ ባህር ዳር፣ ደ/ማርቆስ፣ አዲስ አበባ፣ ደ/ብርሃን፣ ደ/ሲና፣ ቢሾፍቱ፣ አዳማ፣ ድሬዳዋ፣ ሶማሌ ክልል ሽንሌ ዞን፣ መልካጀብዱ፣ ሻሸመኔ፣ አጄ፣ሃዋሳ፣ ቡታጂራ፣ እምድብር፣ ወልቂጤና ጅማ ከሚገኙ ከ140 ያህል የማህበረሰብ ምስርት ተቋማት/ ማህበራት ጋር እየሰራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የማህበራቱን ነባራዊ አቅም በማጎልበት ማህበራቱ ለየማህበረሰባቸው ከሚሰጡት ማህበራዊ አገልግሎቶች በተጨማሪ በማህበረሰቡ ውስጥ ተንሰራፍቶ የሚገኘውን የህፃናት፣ የወጣቶችና ሴቶች ችግር መፍታት እንዲችሉ ተደርጓል፡፡የኢየሩሳሌም ህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት የማህበራት ልማት / CBOs Development/ ተሞክሮ እንደሚያሳየው፣ የማህበራቱን አቅም በተለይ ፕሮጀክት የመፈፀም፣ ሂሳብ አያያዝና የአካባቢ ሃብት አጠቃቀም ስልትና መሰል ዘመናዊ አሰራሮች ረገድ የማህበራቱን አቅም በማጎልበት ማህበራቱ በፍትሃዊነት፤ ባነሰ ዋጋ፣ በተደራሽነት፣ ወዘተ በርካታ ችግር ፈቺና ልማታዊ ሥራዎችን እንዲሰሩ ማድረግ ይቻላል፡፡
አዎ! በመላ ሀገራችን ያሉ የህብረተሰቡ የሆኑ ማህበራትን በተቀናጀ መልክ ለልማት ማንቀሳቀስ ቢቻል የማይረታ የችግር ሰርዶ አይኖርም፡፡ እነዚህ በርካታ ቁጥር ያላቸው ማህበራት በትንሽ ሀገር በቀል ዕገዛ፣ በሀገርኛ መንገድ፣ ሀገራዊ ችግሮችን የመፍታት ዕምቅ ችሎታና ሀይል አላቸው፡፡ ስለሆነም የኢየሩሳሌም ህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅትና የሌሎችንም ጥቂት ተሞክሮዎች መነሻ በማድረግ የተቀናጀ ድጋፍና እገዛ በማድረግና እንዲሁም ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ማህበሮቻችንን ለማህበረሰቡ ፋይዳ እንጠቀም!!
ተስፋዬ ይሁኔ

Saturday, 13 December 2014 11:13

የትራንስፖርት ገጠመኝ

ወያላው    ተሳፋሪ! ተሳፋሪ!
አዲስ አባ በፈሪ

አባት    ምን ማለቱ ይሆን?
ልጠይቅ ምስጢሩን…
ደገመ አሁንም አምርሮ፣
ማንን ፈርቶ ቃል ጨምሮ፡፡
ምን ማለቱ እንደሆን ልጠይቀው ብዬ፣
ጠጋ እያልኩ እየፈራሁ እቃዬን አዝዬ፡፡

ወያላው    ግቡ! ግቡ! ፋዘር መኪናው ፈሪ ነው፣
ሰውም እየበዛ ሲሄድ ቀስ ብሎ ነው፡፡
አትጠራጠሩ በልኩ ይጭናል፣
ሹፌሩ ፈሪ ነው ቀስ ብሎ ይነዳል፡፡
መንገድ ላይ መንከርፈፍ ሁሌ ልማዱ ነው፣
ምናልባት - ምናልባት ነገ ቢገባ ነው፡፡

አባት       ስለዚህ ብሎ… ብዙ ሳያወራ፣
ካፉ ላይ ቀማሁት ይሄን ወሮበላ፡፡
ምን ማለትህ ይሆን? ግራ ገባኝ ባክህ፣
ማከላከልህ ነው ቋንቋ ማሳመርህ፡፡
ዞር በል ከበሩ - ሰው እጠይቃለሁ፣
ከአንተ ጋር ሳወራ - ጊዜ አቃጥያለሁ፡፡

ወያላፋዘር ይቅርቦ ለርሶ አዝኜ ነው፣
መኪናው ቀርፋፋ ነገ ቢደርስ ነው፡፡

አባትምን ታዝንልኛለህ - የትስ ታውቀኛለህ?
በጣም ነው የማዝነው ለካስ ደላላ ነህ፡፡

ወያላይኸው ሚኒባሱ - ፋዘር በዚሂዱ፣
ስለ ንግግሬ ብዙ አይናደዱ፡፡
ወዲያው ይደርሳሉ ካሰቡበት ቦታ፣

አባትብሎ ሳይጨርስ ይሄንን ወስላታ፣
በለው! በለው! አለኝ ወኔዬ መጣና፡፡
እሱ መቼ ፈርቶ ማንንስ አክብሮ፣
መለፍለፍ ቀጥሏል መሬት አቀርቅሮ፡፡

አሠለፈች አበበ ደሳለኝ
አዳማ (ናዝሬት)

Saturday, 13 December 2014 11:11

እስቲ ይሞክሩት

በዓለም ላይ ለመምህራን ከፍተኛ ደሞዝ የምትከፍል አገር ማናት?
በዓለም ላይ ከፍተኛ ዕዳ ያለባት አገርስ?
ከፍተኛ ቁጥር ያለው የጦር ሰራዊት ያላት አገር የትኛዋ ናት?
ብዙ ቢሊዬነሮች ያሉባቸው የዓለማችን ሦስት ከተሞች የትኞቹ ናቸው?
ሦስቱ የዓለማችን እጅግ     ሃብታም አገሮች እነማን     ናቸው?
============    
መልስ
1    ስዊዘርላንድ (በዓመት 68ሺ ዶላር) ኔዘርላንድ፣ ጀርመንና ቤልጂየም ይከተላሉ፡፡
2    አሜሪካ (15,940,978 ዶላር) እንግሊዝ፣ ጀርመንና ፈረንሳይ ይከተላሉ
3   ቻይና (2,285,000) ግብፅ በ10ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡
4   ሞስኮ (84)፣ ኒውዮርክ (62) እና ሆንግኮንግ (43)
5   ኳታር፣ ሉክሰምበርግ እና ሲንጋፖር (አሜሪካ በ6ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች)

የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈፃሚዎች በተለያዩ አዕምሮአዊ የጤና ችግሮች የተጠቁ ናቸው (የስነ ልቦና ባለሙያ)
ህጉ በአስገድዶ ደፋሪዎች ላይ ያስቀመጠው ቅጣት ለወንጀሉ ተመጣጣኝ አይደለም (የህግ ባለሙያ)

አየር ጤና አካባቢ ከሚገኘው ት/ቤቷ ወጥታ ወደ ቤቷ ለመሄድ በተሳፈረችበት ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ በነበሩ አምስት ወንዶች ታፍና ተወስዳ በደረሰባት የአስገድዶ መድፈር ጥቃት ህይወቷ ያለፈው የአስራ አምስት ዓመቷ ታዳጊ ሃና ላላንጎ ጉዳይ ከተማችንን ሲንጣት ሰንብቷል፡፡ ታዳጊዋ ታፍና ከተወሰደችበት መስከረም 21 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት የቡድን አስገድዶ መድፈር ጥቃታ ተፈፅሞባት፣ ጦር ኃይሎች ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን አካባቢ ተጥላ መገኘቷ መገቡ ይታወሳል፡፡
የህክምና እርዳታ አግኝታ ህይወቷ እንዲተርፍ የተደረገው ሙከራም የተፈፀመባት የአስገድዶ መድፈር ጥቃት እጅግ ከባድ በመሆኑና በስለት በመወጋቷ ሳቢያ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ ይሄ ክፉ ዜና ከተሰማበት ጊዜ አንስቶ ድርጊቱም በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል፡፡ በታዳጊዋ ላይ ይህንን አሰቃቂ ወንጀል ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ አምስት ወጣቶችም በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው፣ ጉዳያቸው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍ/ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎታ በዝግ እየታየ ይገኛል፡፡
የሟቿን ታዳጊ ጉዳይ መነሻ በማድረግ ለአስገድዶ መድፈር ወንጀል የሚያነሳሱ አፈንጋጭ የወሲብ ባህሪያትን ምንነትና የሚያስከትሏቸውን የጤና ቀውሶች እንዲሁም ለወንጀሉ የተቀመጠውን ቅጣት አስመልክቶ ከባለሙያዎች ያገኘነውን ማብራሪያና መረጃ የአዲስ አድማስ
ጋዜጠኛ መታሰቢያ ካሳዬ እንደሚከተለው አጠናቅራዋለች፡፡


አስገድዶ መድፈር ከስነ ልቦና
ቀውስ አንፃር
መደበኛ ከሆኑትና ከተለመዱት ወሲባዊ ድርጊቶች በተለየ መንገድ ወሲብን የመከወን ፍላጎት ያላቸው ሰዎች፣ ለአፈንጋጭ ወሲባዊ ባህርይ የተጋለጡ ናቸው ተብሎ ይታመናል፡፡ ከእነዚህም መካከል አስገድዶ መድፈር፣ የቡድን ተራክቦ፣ ግብረ ሰዶማዊነት፣ ሌሎች ወሲብን ሲፈፅሙ በማየት መርካት፣ ግለ ወሲብና በሰዎች  ስቃይ እርካታን ማግኘት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የአስገድዶ መድፈርና በቡድን የሚደረጉ ተራክቦዎች በአብዛኛው የሚፈፀሙት በአልኮልና በተለያዩ የአደንዛዥ እፆች ራስን ስቶ አዕምሮ በአግባቡ እንዳያስብ በማድረግ ነው ይላሉ - ባለሙያዎች፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአፈንጋጭ ወሲባዊ ባህርያት አመላካች የሆኑ ድርጊቶች በአገራችን እየተለመዱ መምጣታቸውን የጠቆሙት የሥነ ልቦና ባለሙያው ዶክተር አንተነህ ተስፋው፤ በተለይ ዕድሜያቸው ከ16-25 ዓመት በሚሆናቸው ወጣቶች ላይ ድርጊቱ በስፋት እየታየ መሆኑ በጥናት መረጋገጡን ገልጸዋል፡
ከቴክኖሎጂው እድገትና ወሲባዊ ፊልሞች እንደ አሸን ከመፍላታቸው ጋር ተያይዞ አስገድዶ መድፈር፣ የቡድን ወሲብና ግብረሰዶማዊነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፉ መምጣታቸውንም ዶክተሩ ተናግረዋል፡፡
ከአፈንጋጭ ወሲባዊ ባህርያት አንዱ የሆነው አስገድዶ መድፈር የአዕምሮአዊ ጤና ቀውስ ውጤት ነው፡፡ ለአፈንጋጭ ወሲባዊ ባህርያት አጋላጭ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል ዋንኞቹ፡-
ከአስተዳደግ ጋር በተያያዘ የሚከሰቱ ስነልቦናዊ ችግሮች
አዕምሮ ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች
የሆርሞኖችና ኬሚካሎች መዛባት
የኒውሮኖች ጉዳት ናቸው፡፡
ከአስተዳደግ ጋር በተያያዘ የሚከሰቱ የስነ ልቦና ችግሮች
ችግሩ በአብዛኛው ከአስተዳደጋችን ጋር ተያይዞ የሚከሰት ነው፡፡ ለራስ የሚሰጥ አነስተኛ ግምትና በልጅነት ዕድሜ ለወሲባዊ ጥቃት ተጋላጭ መሆን ለአፈንጋጭ የወሲብ ባህርይ ሊዳርግ ይችላል፡፡
አዕምሮ ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች
በአዕምሮአችን ላይ በበሽታም ሆነ በተለያዩ ምክንያቶች አካላዊ ጉዳቶች ሊደርሱ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ጉዳቶች ደግሞ የአዕምሮአችንን የወሲብ ክፍል ሊጎዱትና በዚያም ሳቢያ በወሲባዊ ባህርያችን ላይ ተፅዕኖ በመፍጠር ለአፈንጋጭ የወሲብ ባህርይ ሊያጋልጡን ይችላሉ፡፡
የሆርሞኖችና የአዕምሮ ኬሚካሎች መጠን መዛባት
አንድሮጅንና ኤስትሮጅን የተባሉት በሰውነታችን ውስጥ የሚገኙት ሆርሞኖች ወሲባዊ ፍላጐትና ስሜታችንን ለመቆጣጠር የማረዱን ናቸው፡፡ የእነዚህ ሆርሞኖች መዛባት በወሲባዊ ባህርያችን ላይ የሚያስከትሉት ተፅእኖ ቀላል አይደለም፡፡
 የኒውሮኖች ጉዳት
የአዕምሮ ሴሎች እርስ በርስ እንዲተሳሰሩና መልእክት እንዲለዋወጡ የሚያደርጉ የአዕምሮአችን መረቦች በተለያየ ምክንያት ጉዳት በሚደርስባቸው ጊዜ አፈንጋጭ ለሆነ ወሲባዊ ባህርይ ሊያጋልጡን ይችላሉ፡፡
በአጠቃላይ ለአፈንጋጭ ወሲባዊ ባህርይ ልንጋለጥ የምንችለው በተለያዩ ውስጣዊና ውጫዊ ምክንያቶች ሲሆን ችግሩ በወቅቱ ታውቆ የባለሙያ እገዛ ካላገኘ በጊዜ ብዛት አፈንጋጭ የወሲብ ባህርይው ሙሉ በሙሉ የግለሰቡን አዕምሮ በመግዛት በራስ መተማመን የሌለውና ወሲባዊ እሳቤውን ለመቆጣጠር የማይችል ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡ የችግሩ ተጠቂ የሆነ ሰው ለራሱ ያለው ግምት እጅግ አነስተኛ ስለሚሆን ራሱን ከማህበረሰቡ ያገላል፡፡ ራሱን ለማጥፋትም ይፈልጋል፡፡ ይህ ከመሆኑ በፊት የችግሩ ተጠቂዎች የስነልቡና ባለሙያዎች ጋር ወይንም የስነ አዕምሮ ሐኪሞች ዘንድ በመሄድ ለችግራቸው መፍትሄ መሻት ይኖርባቸዋል፡፡
የአስገድዶ መድፈር ድርጊት የተፈፀመባት (የተፈፀመበት) ሰው ብቻ ሳይሆን የፈፀመው ግለሰብም ጭምር የህክምና እርዳታ ሊያገኝ የሚችልበት መንገድ መመቻቸት ይኖርበታል ያሉት የስነልቡና ባለሙያው ዶክተር አንተነህ፤ ይህ አሰራር በሌሎች አገራት የተለመደ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
አስገድዶ መድፈርና ህጋዊ ተጠያቂነቱ
በ15 ዓመቷ ታዳጊ ወጣት ላይ የተፈፀመው የቡድን አስገድዶ መድፈር ወንጀል ያስቆጣቸው የከተማዋ ነዋሪዎች የድርጊቱ ፈፃሚዎች በአፋጣኝ ተይዘው ለድርጊታቸው ተመጣጣኝ የሆነና ሌሎችን ሊያስተምር የሚችል (መቀጣጫ የሚሆን) ፍርድ እንዲሰጣቸው ሲጠይቁ ሰንብተዋል፡፡ የወንጀሉ ፈፃሚዎች በሞት እንዲቀጡ አሊያም የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲወሰንባቸው የጠየቁም በርካቶች ናቸው፡፡ ለመሆኑ የወንጀለኛ መቅጫ ህጉ ለዚህ መሰሉ ድርጊት የሚሰጠው የቅጣት ውሳኔ እምን ድረስ ነው? የህግ ባለሙያው አቶ ዳዊት ታዬ ለዚህ ማብራሪያ አላቸው፡፡
የኢትዮጵያ ወንጀለኛ መቅጫ ህግ፤ የአስገድዶ መድፈርን ወንጀል እስከ አስር አመት ሊደርስ በሚችል ቅጣት የሚያስቀጣ ወንጀል አድርጐ አስቀምጦታል፡፡
ድርጊቱ የተፈፀመው አስራ አምስት ዓመት ባልሞላት ሴት ልጅ ላይና በብዙ ሰዎች ተባባሪነት ከሆነ ቅጣቱ እስከ አስራ አምስት አመት ሊደርስ እንደሚችል ይገልፃል፡፡ ድርጊቱ ሞትን የሚያስከትል ሲሆን ደግሞ ቅጣቱ ከፍ ሊል ይችላል፡፡ ሆኖም በአስገድዶ መድፈር ላይ ተፈፃሚ የሚሆኑ የቅጣት ህጐች ደፋሪዎች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ለማድረግ የሚያስችል አቅም ያላቸው ናቸው ብሎ ለመናገር እንደማያስችሉ አቶ ዳዊት ይናገራሉ፡፡
“ህጉ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመ ሰው ወንጀሉን የፈፀመባትን ሴት ያገባ እንደሆነ ክሱ ቀሪ ሊሆን እንደሚችል ያስቀምጣል፤ ይህም የድርጊቱ ፈፃሚዎች ጋብቻ በመፈፀም ከተጠያቂነት ነፃ ሊሆኑ እንደሚችሉ ስለሚያስቡ ድርጊቱን ከመፈፀም ወደ ኋላ አይሉም፤ ምክንያቱም ወንጀሉን በጋብቻው ካስቀሩ በኋላ ጋብቻውን ደግሞ በቀላሉ ሊተውት ይችላሉና” ሲሉ አስረድተዋል አቶ ዳዊት፡፡
ተጎጂውን ለአካል ጉዳት፣ ለስነ ልቦና ቀውስና ባስ ሲልም ለህልፈት የሚዳርገውን ይህን ፆታዊ ጥቃት ለመከላከልና ከነአካቴውም ለማጥፋት የሁሉንም የጋራ ህብረትና ጥረት ይጠይቃል፡፡
 ጉዳዩ ጊዜ የሚሰጥና ለነገ በይደር የሚተው አይደለም፡፡ ግለሰቦች፣ ቤተሰብ፣ ጎረቤት፣ ማህበረሰብ፣ ፖሊስ (መንግስት)፣ መምህራንና የሥነ ልቦና ባለሙያዎች እንዲሁም የፆታ እኩልነት ተሟጋቾች ዛሬውኑ አገራዊ እንቅስቃሴ መጀመር ይኖርባቸዋል፡፡ ነገ በሃና ላይ ከተፈፀመው ጥቃት የከፋ በሌሎች ላይ ላለመፈፀሙ ምንም ማረጋገጫ እንደሌለን መዘንጋት የለብንም እሳቱን ለማጥፋት ከመረባረብ ቃጠሎ እንዳይነሳ መከላከል የተሻለ አማራጭ ነው፡፡

“አሜሪካ ፆታዊ ጥቃቶችን አጥብቃ ትቃወማለች”
አገራቸው በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ፆታዊ ጥቃቶችን አጥብቃ እንደምትቃወምና የሴቶችን አቅም በመገንባትና በማሳደግ ረገድ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በህብረት እንደምትሰራ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ፓትሪሺያ ኤም ሃስላክ ገለፁ፡፡ ከህዳር 16 ጀምሮ እስከ ታህሳስ 1 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ በዘለቀው የነጭ ሪባን ቀን፤ በኤምባሲው በተዘጋጁ የተለያዩ ፕሮግራሞች ላይ ከተሳተፉት የአሜሪካ አምባሳደር ጋር የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ መታሰቢያ ካሳዬ የአፍታ ቆይታ አድርጋለች፡፡

አምባሳደር በመሆን ተሹመው ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣትዎ በፊት ስለ ኢትዮጵያ ያውቁ ነበር?
በ1980ዎቹ በኢትዮጵያ በተከሰተው ረሃብና የድህነት ችግር ላይ ከአሜሪካ መንግስት ጋር እሰራ ነበር፡፡ በ2010 አለም አቀፍ የድህነት መዋጋትና የምግብ ዋስትና (አሁን Future Initative እየተባለ የሚጠራውን) ድርጅት ወክዬ ወደ ኢትዮጵያ መጥቻለሁ፡፡
አሁን ሲመጡ ምን ለውጥ አዩ?
ብዙ ለውጦች አሉ፡፡ አገሪቱ እያደገች በመሄድ ላይ መሆኗንም ለማየት ችያለሁ፡፡
ፆታዊ ጥቃትን አስመልክቶ ሰሞኑን በተዘጋጁ የተለያዩ ፕሮግራሞች ላይ ተሳታፊ ነበሩ፡፡ ከተደራራቢ የሥራ ኃላፊነትዎ አንፃር ይህን እንዴት ተወጡት?
በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን አገሬ አጥብቃ ትቃወማለች፡፡ ለዚህም ነው በፀረ ፆታዊ ጥቃትና ሴቶችን በማብቃት ሥራ ላይ ትኩረት ሰጥተን የምንሰራው፡፡ ይህ የነጭ ሪባን ቀን ደግሞ ለፆታዊ ጥቃቶች ያለንን ተቃውሞ የምናሰማበት ስለሆነ ነው በኤምባሲው በተዘጋጁ ፕሮግራሞች ላይ ሁሉ ተሳታፊ የሆንኩት፡፡ በግሌ ደግሞ ከመሃከለኛው ህዝብ ጋር መሆን ደስታን ይሰጠኛል፡፡ ለሰዎች ድጋፍና ተስፋን ከሚሰጡ ድርጅቶች ጋር አብሮ መስራት እወዳለሁ፡፡ እንዲህ አይነት ቦታዎች ላይ መገኘትም የሚሰጠኝ ደስታ በቀላሉ የሚገመት አይደለም፡፡
በቅርቡ በቡድን በተደረገባት የአስገድዶ መድፈር ጥቃት ህይወቷ ያለፈው ታዳጊ ወጣት ሃና ላላንጐ ጉዳይ በአገሪቱ አነጋጋሪ አጀንዳ ሆኖ ሰንብቷል፡፡ ጉዳዩ በማህበረሰቡ ዘንድ ቁጣን የቀሰቀሰ ቢሆንም አንዳንድ ወገኖች መንግሥት ስለ ጉዳዩ ብዙም ያለው ነገር የለም በማለት ይተቻሉ፡፡ በእናንተ አገር እንዲህ አይነት ጉዳይ ሲያጋጥም የመንግስት ሚና ምንድነው?
የሃና ጉዳይ በኢትዮጵያ ብቻ የተከሰተ ወይንም የሚከሰት ብቻ አይደለም፡፡ በመላው ዓለም የሚከሰትና የተከሰተም ጉዳይ ነው፡፡ ይህንን ለማስቀረት ዋንኛው መፍትሄ ህብረተሰቡን ማስተማር ነው፡፡ ሁሉም ዜጋ ለጉዳዩ ያገባኛል ማለት መቻል አለበት፡፡ ሃላፊነት መውሰድ ይኖርበታል፡፡ ባል ሚስቱን ሲደበድብ ወይም ጐረምሳው ወጣቷን ሲመታ አይቶ በዝምታ ማለፍ አግባብ አይደለም፡፡ ሁሉም ሰው እንዲህ አይነት ፆታዊ ጥቃቶች ሲፈፀሙ ሲያይ ለማስቆም ጥረት ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ይህ ከሁሉም ዜጋ የሚጠበቅ ሃላፊነት ነው፡፡ ሴቶች በራሳቸው ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን ለማስቆም የሚያስችል አቅም እንዲኖራቸው ለማድረግም ጥረት እናደርጋለን፡፡ በፆታዊ ጥቃቶች ላይ መንግስታችሁ ጥብቅ አቋም እንዳለው አውቃለሁ፡፡ የአስራ ስድስት ቀናቱን የነጭ ሪባን ቀን በማስተባበር እየሰራ የነበረው የሴቶች ጉዳይ ሚኒስቴር ነው፡፡ እናም መንግሥታችሁ በዚህ ጉዳይ ላይ ቁርጠኛ ነው፡፡
የሁለት ሴት ልጆች እናት ነዎት፡፡ አንደኛዋ ልጅዎ በጋዜጠኝነት ሙያ ውስጥ ተሰማርታለች፡፡ የት ነው የምትሰራው? ለጋዜጠኝነት ሙያ ያለዎት ስሜትስ ምን ይመስላል?
ሁለት ሴት ልጆች አሉኝ፡፡ አንዷ ከጥቂት ቀናት በፊት ወደ ኢትዮጵያ መጥታ ለሁለት ሳምንታት ቆይታ ሄዳለች፡፡ ለጋዜጠኝነት ፍቅር አላት፡፡ ከኒውዮርክ ዩኒቨርስቲ ስኩል ኦፍ ጆርናሊዝም ዲግሪዋን ወስዳለች፡፡ በአሁኑ ወቅት ለቢቢሲ ትራቭል እንዲሁም፣ ለኒውዮርክ ታይምስና ለሌሎች መፅሄቶች ትሰራለች፡፡ ለሙያው ጥሩ ስሜት አለኝ፡፡   

Saturday, 13 December 2014 10:51

የግጥም ጥግ

መቼ ነው ያለሁት?
ዛሬ ነግቶ መሽቶ ቀኑን አልፈውና፣
ሌላው ቀን ሲተካ ሲሆን ትናንትና፣
ይኸው እኖራለሁ አለሁ እኮ ዛሬ፣
ደግሞም ለዓመታት  ተስፋ አለኝ መኖሬ፣
    እያልሁ አስብና፣
    ሞቴን እረሳና፣
    እቅዴን አውጥቼ፣
    ምኞቴን አስፍቼ፣
ደጉን ተመኝቼ፣
ክፉውን ዘንግቼ፣
ሞትን ተሸክሜ ግን እየረሳሁት፣
ጎንበስ ቀና እያልሁ ይኸውና አለሁት፡፡
ምንም ባላውቀውም ቀኑን መሻገሬ፣
የነገን እንጃ እንጂ አለሁ ግን ለዛሬ፡፡
ሞት ትዝ ቢልም፣ ከራርሞ ከራርሞ …
    ከስንት ቀን አንዴ፣
መች ተስፋ ቆርጬ፣ ሰብዓዊ ፍጡር…
        ሰው አይደለሁ እንዴ!
ሃሳብ አይገባኝም፣ ባስብስ ምን ልሆን …
           ከቶ የማይቀረውን፣
ስለዚህ ማሰብስ፣ ዛሬን እንጂ ኑሮን …
    ፋታ የማይሰጠውን፡፡
ግን ታዲያ! …
    ማለፌን ሳስታውስ እንደገና ደግሞ፣
    ከውጥኔ በፊት ሞት ሲመጣ ቀድሞ፣
        ድንገት ፀጥ እልና፣
        ክልትው እለውና፣
        ሁሉም ይቀርና፣
        ጣጣዬ  ያከትምና፣
        ክርችም ብሎ ቁልፉ፣
        ይዘጋል ምዕራፉ፡፡
ቀነ - ሞታችንን እኔም ሆንኩ ሌላው …
          ጨርሰን አናውቀው፣
ስለዚህ ነው ሰዎች፣ “መቼ ነው ያለሁት?”
    ብዬ የምጠይቀው፡፡
                  * * *
አምሳሉ ጌታሁን ደርሰህ
ህዳር 2007 ዓ.ም

የ25 ዓመቷ አሜሪካዊት ጄድ ሲልቪስተር፤ በእርግዝና ወቅት በተፈጠረባት አምሮት መላቀቅ ዳገት ለሆነባት ክፉ ልማድ እንደተጋለጠች ትናገራለች፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት ነፍሰጡር ሳለች የጀመረችው የመፀዳጃ ቤት ወረቀት (ሶፍት) የመብላት ልማድ ከወለደችም በኋላ ሊላቀቃት አልቻለም፡፡ ዛሬ ያ አምሮት ወደ ሱስ ያደገ ይመስላል፡፡ በየቀኑ አንድ ጥቅል ሶፍት ታነክታለች፡፡
“ባረገዝኩ በሁለተኛ ወሬ ነው ሶፍት የመብላት አምሮት (ፍላጐት) ያደረብኝ፡፡ ለምን እንደሆነ ግን አሁንም ድረስ አላውቀውም፡፡
 ከጣእሙ ይልቅ ደስ የሚለኝ ሻካራነቱ ነው፡፡ ደረቅነቱን እወደዋለሁ” ያለችው ጄድ፤ “ቤተሰቦቼ ለጤናዬ ጥሩ አለመሆኑን ይነግሩኛል፤ ነገር ግን ለመተው አልቻልኩም” ብላለች፡፡
ልጇን ከተገላገለች አንድ ዓመት ከሦስት ወር ያለፋት ቢሆንም መፀዳጃ ቤት ገብታ በተቀመጠች ቁጥር ሶፍት እየቀረደደች መብላቷን ገፍታበታለች፡፡ በየቀኑም አንድ ሙሉ ጥቅል ሶፍት እንደ ምግብ አኝካና አጣጥማ እንደምትውጥ ተናግራለች፡፡ ነፍሰጡር ሳለች መፀዳጃ ቤት ገብታ ጥቅል ሶፍት ስታይ “ይሄንን መብላት አለብኝ” እያለች ትጐመዥና ትመኝ እንደነበር ያስታወሰችው ጄድ፤ ዛሬ ግን አንዳንዴ ወደ መታጠቢያ ከመሄድ ሁሉ ራሷን እንደምታቅብ ገልፃለች፡፡ “ምክንያቱም ከሄድኩኝ መብላቴ አይቀርም፡፡ ሽንት ቤት በሄድኩ ቁጥር ወደ 8 ገደማ የሶፍት ቁራጮች እበላለሁ አንዳንዴም ሶፍቱን ለመብላት ስል ብቻ መፀዳጃ ቤት ለመሄድ እገደዳለሁ” ትላለች፡፡
ለመብላት የምትመርጠውን የሶፍት አይነት ስትናገር ደግሞ፤ ከውዶቹ ይልቅ በየሱፐርማርኬቱ የሚገኙት ተራና ርካሽ ሶፍቶች ምርጫዋ እንደሆኑ ገልፃለች፡፡
“የተለያዩ የሶፍት ምርቶች የተለያየ ጣእም አላቸው፤ በመፀዳጃ ቤት ውስጥ አንድ ጥቅል ለምበላው፣ አንድ ጥቅል ደግሞ ለተለመደው አገልግሎት አስቀምጣለሁ” ብላለች ጄድ ሲልቪስተር፡፡ የመጨረሻ ወንድ ልጇን ከተገላገለች ጊዜ ጀምሮ (16 ወራት ገደማ ማለት ነው) ሶፍት መብላቷን ለመተው ብዙ ታግላለች፤ ሆኖም አልተሳካላትም፡፡ ልጅ ከወለድኩ በኋላ አምሮቱ የሚተወኝ መስሎኝ ነበር ያለችው ጄድ፤ ነገር ግን ሶፍት መብላቴን ላቆም አልቻልኩም ትላለች - ተስፋ በቆረጠ ቅላፄ፡፡
“ሶፍት መብላቴ ለሰውነቴ መልካም ሊሆን እንደማይችል አውቃለሁ፤ እስካሁን ግን ምንም የጤና ችግር ወይም ህመም አላስከተለብኝም” ያለችው ሚስ ሲልቪስተር፤ ሶፍት ስትበላ ልጆቿ እንዳያዩዋት ለመደበቅ እንደምትሞክር ገልፃ ድንገት ካዩዋት ግን እንደሚቆጧት ተናግራለች፡፡ ጄድ ሲልቪስተር የአምስት ልጆች እናት ናት፡፡ የአገራችን ሰው “አያድርስ ነው” የሚለው ለካ ወዶ አይደለም!!