የግጥም ጥግ
እንደመግቢያክፍት የሥራ ቦታግጥም ፅፌ ፅፌ፣አላነብም ብሎ ሰዉ ቢያስቸግረኝ“ክፍት የሥራ ቦታ”፣ የሚል ከባድ ርዕስ-ያለው ግጥም ፃፍኩኝ!ማ ጮክ በል አለኝ?... ተሻማ ህዝብ ሁሉ፣ግጥሜን ገዛልኝ!በየቤቱ ሄዶ-ተስገብግቦ ጠግቦ፣ ዋለበት ቢመቸው-ሦስቴ አራቴ፣ አምስቴ፤ ደጋግሞ አነበበው-ግጥሙ እንዲህ አለቀ፡-“ውድ አንባቢዬ ሆይ በቢሮ፣ በቤትህ፣ በፍራሽ ላይ ያለህመንግስት ያላየውን፣…
Read 19803 times
Published in
የግጥም ጥግ
ፍቅር ሽልማት የለውም አንተ ግን ሽልማት አለህ!እንደ ትንቢት - ተናጋሪ፣ የነገን ዕውቀት አበጀህ!የእናት ያባት ዕውቀት ማለት፤ የልጅ ሽልማት ውብ ኩራት!!የራስህ ትምርት ትጋት የራስህ ትምርት ንጋት የዛሬህን ጐዶሎ፣በነገ ጥበብህ መሙላትይሄ ብቻ ነው ዓለምህ፣ የራስህ ፍቅር ጉልላት!!(ነ.መ፤ ኢዮብና አሥቴር ለፍቅር የትምህርት ድል)ሰኔ…
Read 4140 times
Published in
የግጥም ጥግ
አፈር-አፈር ይብላ፤ ለእግዜር እግዜር ይየው፤ እንዴት ነው የሣት ፍም በአፈር የሚቆየው እንዴት ነው ነበልባል - በእሣት የሚጋየው ኮከብ እንዴት ብሎ - ለአፈር ይገዛል? እንዴት ፀሐይ - ወርዶ መሬት ይያዛል?አፈር አፈር ብላ - አጥንቷ ይንሣህ ሥጋዋ ረፍት ይንሣህ ሀሣብዋ ይነቅንቅህ!መልክ አይሁንህ…
Read 3368 times
Published in
የግጥም ጥግ
ኩርማን መግቢያ እግዜር ከሞላው ኩሬ ውስጥ ፣ እስቲ እንዋኝ ብለን ገብተን ሳንጨርሰው ውሃው ደርቆ፣ መካከል ላይ ዋጋ ከፈልን!ለኩሬ ዋናው ተጥፈን በውቂያኖሱ ተቀጣን!***አለሥራችን ገብተን፣ አንጨቅጭቀው እግዜአብሔርን፤ ይቅርታ እንጠይቅ እንጂ፣ ስለመፈጠራችን፤ ለመኖሪያችንማ፣ “የቀን ውሎ - አበል” አልን!ተጠባባቂ ቤንች እንጂ፣ ቋሚ ተሰላፊ አደለን!የካምቦሎጆን…
Read 4664 times
Published in
የግጥም ጥግ
ትርጉም እያዛባ፣ቃል እያናናቀ፣ፍቺ እያጣረሰ፤ከበሽታ ሁሉ የደሃ ኩርፊያ ነውሃገር ያፈረሰ።እናንተ ብልሆች!ተስፋ−ተስፋ የሚሸት እቅድ ስታቅዱ፣ንቁ−ፍኩ እንዲሆን የለውጥ መንገዱ፤‘ካኮረፈ ደሃ’ ሃሳብ አትውሰዱ! የለቅሶ ቤት አዝማችተዝካር፣እዝን፣ድንኳን፣ንፍሮ፣ሰልስት፤12፣ 40፣ 80፣ ሙት−ዓመት፤“ጐጂ ነው!” አትበሉን አቦ እናልቅስበት!እናውቃለን እኮ!አዛኞች፣ አጽናኞች በሞሉባት አምባ፤‘ግማሽ ሳቅ’ ማለት ነው ሁሉ ያየው ዕንባ።
Read 5497 times
Published in
የግጥም ጥግ
አገሬን አገሬ እምላት “በባዶ እግርህ አትሂድ ሲሚንቶው ይቀዘቅዝሃል” ያለችኝ’ለት…ልክ እንደእናት፡፡ አገሬን አገሬ እምላት “ባዶ ሆድህን ነህኮእህል ባፍህ ይዙር እንጂ!”ያለችኝ’ለት…ልክ እንደእናት፡፡ አገሬን አገሬ እምላት “የውሃውን ደረሰኝደህና ቦታ አስቀምጥ ኋላከጠፋ ጣጣው ብዙ ነው!”ያለችኝ ለት…ልክ እንደ እናት አገሬን አገሬ እምላት“የመብራቱን ደረሰኝ ያዝ”ከጠፋ ጣጣ…
Read 4095 times
Published in
የግጥም ጥግ