ከፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ

ከፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ (40)

  (ጦርነትን ቀድሞ የጀመረ ቅድመ ሁኔታን የማስቀመጥ ሞራል የለውም!)


             ጦርነቱ በተጀመረ በሁለተኛው ቀን ሴኩቱሬ በድምፀ ወያኔ ቀርቦ ጦርነቱን ሕወሓት እንደጀመረችው በግልፅ ቋንቋና ሰፋ ባለ ማብራሪያ ገለፀ፣ ሴኩቱሬ ይህን ገለፃውን በሚሰጥበት ወቅት በቴሌቪዥኑ እስክሪን ላይ የተጻፈው ርዕሰ ጉዳይ “የመጀመሪያው ምዕራፍ በድል የመጠናቀቅ አንድምታ” የሚል ነበር። ርዕሱ ሴኩቱሬ ይህን በሌላ በየትኛውም አግባብ መለቀቅ የሌለበትን ማስረጃ ለኢትዮጵያና ለዓለም ይፋ ያደረገበትን ምክንያት ግልፅ ያደርጋል፣ በአጭር ቃል ሴኩቱሬ በሰሜን ዕዝ ላይ ስኬታማ መብረቃዊ ጥቃትን መፈፀሙን እንደ መጨረሻው የድል ምዕራፍ ሳይቆጥረው አልቀረም። ሌላ ረዘም ያለ ጦርነት በቀጣይነት እንዳለ ቢያውቅ ኖሮ ይህን መግለጫ ባልሰጠም ብዬ አስባለሁ።
ሴኩቱሬ በ45 ደቂቃ ውስጥ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃቱ በቅድሚያ መፈፀሙን ይፋ ከማድረጉም ባለፈ ለድርጊቱ ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠትም የአቅሙን ያህል ሞክሯል። እሱ ያለው "...ከሰሜን በኩል አሃዳዊውና ወራሪው የአብይ መንግስት ደግሞ በደቡብ በትግራይ ሕዝብ ላይ ግልፅና የማይቀር (imminent) ጥቃት ሊፈፅሙ እንደሆነ እንደገመገምን ቀድመን በመብረቃዊ ምት ሰሜን ዕዝን “demobilize” አድርገናል...ነው።" በመቀጠልም ሴኩቱሬ እንደዚህ ዓይነት እርምጃ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ያለው ፅንሰ ሐሳብ መሆኑን ከገለፀልን በኋላ ስያሜውም በእንግሊዝኛ “Anticipatory Self defence” ተብሎ ይጠራል በማለት አብራርቶልናል። ታዲያ ይህ ዘዴ ትንንሽ ሀገራት በትላልቅ ሀገራት ሊዋጡ እንደሆነ ማስረጃዎች ሲገኙ ጥቅም ላይ የሚውል ራስን የመከላከል እርምጃ ነውም በማለት ነግሮናል።
ሴኩቱሬ ለቅድመ-ጥቃቱ ዓለም አቀፋዊ ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት የጠቀሰው “Anticipatory Self Defence” ምንን ያመላክት ይሆን? ራስን ከታለመ ወይም ከታቀደ ጥቃት ቀድሞ መከላከልን በተመለከተ የሚያጠኑ ምሁራን ሦስት የመከላከል ዓይነቶች እንዳሉ ያመለክታሉ።
1. ለማይቀረው ጥቃት የሚወሰድ የመከላከል እርምጃ (Anticipatory Self Defence)፦ ይህ አንድ ሀገር በሉዓላዊነቱ ላይ እጅግ በጣም ግልፅና በማስረጃ የተደገፈ ጥቃት ከሌላ ሀገር ወይም ታጣቂ ቡድን እንደሚሰነዘርበት እርግጠኛ ሲሆን ቀድሞ የሚወስደው የመከላከል እርምጃ ነው። ይህ ጥቃቱን እንደሚያደርስ ወደሚገመትበት ሀገር ድንበር ገብቶ እስከ ማጥቃት የሚዘልቅ የመከላከል እርምጃ ነው። ስለ ሕጋዊነቱ(Legitimacy) እመለስበታለሁ።
2. ከተገማች ጥቃት ለመከላከል የሚወሰድ እርምጃ (Pre-emptive Self Defence)
ይኼኛው የመከላከል እርምጃ ቀደም ሲል ከጠቀስኩት የሚለየው ጥቃቱ ከሚፈፅመበት የጊዜ ሰሌዳ አኳያ ነው። “Anticipatory Self Defence” ጠላት በጣም ቅርብ በሆነ ጊዜ ጥቃቱን እንደሚፈፅም በተረጋገጠ ጊዜ የሚወሰድ እርምጃ ነው። Pre-emptive Self defence ግን የተገመተው ጥቃት የሚፈፀምበት የጊዜ ሰሌዳ ከ”Anticipatory” ራቅ ሊል ይችላል።
3. Preventive Self Defence
ይኼኛው የመከላከል ዘዴ የታለመው ጥቃት የሚፈፀምበትን ወቅት በእርግጠኝነት ማወቅን እንደ ቅድመ ሁኔታ አያስቀምጥም። ጠላት ወደ ፊት በአሳቻ ጊዜ ጥቃት እንደሚፈፅም ሲታመን “Preventive Self defence” ተግባራዊ ይሆናል።
“Anticipatory Self Defence “ከዓለም አቀፍ ሕግና ከተባበሩት የዓለም መንግስታት ቻርተር አንፃር፦
ከ”Anticipatory” የመከላከል እርምጃ ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ የዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ሕጎች፣ የተባበሩት መንግስታት ቻርተር አንቀፅ 51 እና እ.ኤ.አ በ2004 በተባበሩት መንግስታት ዋና ፀሐፊ አማካይነት የተደረገው ውይይት ይጠቀሳሉ። ከነዚህ ውስጥ እ.ኤ.አ. በ1951 በተባበሩት መንግስታት ቻርተር ላይ የሰፈረውን እንደሚከተለው ላስቀምጥ፦
Article 51 of the UN Charter “Nothing in the present Charter shall impair the inherent right of individual or collective self-defense if an armed attack occurs against a Member of the United Nations until the Security Council has taken measures necessary to maintain international peace and security”
ከላይ እንደምትመለከቱት በዚህ አንቀፅ ውስጥ “Anticipatory Self Defence” የሚል ሐረግ የለም። ይህን የሚጨማምሩት ተርጓሚዎቹ ናቸው፣ እንደዚያም ሆኖ ሐረጉ በግልፅ ባለመቀመጡ እስከ ዛሬም አንቀፁ በአጨቃጫቂነቱ ቀጥሏል። በግልፅ እንደምንመለከተው አንቀፅ 51 የሚለው “If an armed attack occurs..” ነው።
ከተባበሩት መንግስታት ይልቅ ለ"Anticipatory Self Defence” የሚቀርበው እ.ኤ አ.አ በ2004 በተባበሩት መንግስታት ዋና ፀሐፊ በተዘጋጀው ውይይት ላይ የተቀመጠው ማጠቃለያ ነው።
“In 2004, the Secretary-General’s High-Level Panel on Threats, Challenges and Change stated “A threatened State, according to long established international law, can take military action as long as the threatened attack is imminent, no.other means would defelect it and the action is proportionate.”
ይህ ውሳኔ ግን እስከዛሬ ድረስ በተባበሩት መንግስታት ቻርተር ስለ አለመግባቱ ልብ ይሏል። እስከ አሁን ይህን የመከላከል መብት በተመለከተ የሚደረጉ ክርክሮች እንደቀጠሉ ነው። ነገር ግን ከ9-11 ጥቃት ወዲህ ይህ የመከላከል እርምጃ በተለይም አሸባሪዎች ጥቃት እንደሚያደርሱ በማስረጃ ከተረጋገጠ ወዲያው ተግባራዊ መሆን እንዳለበት ብዙዎች የሚስማሙበት ነው።
በታሪክ “Anticipatory self Defence”ን ተግባራዊ ያደረጉ ብዙ ሀገራት አሉ፣ ለምሣሌ እንግሊዞች ካናዳን ቅኝ በሚገዙበት እ.ኤ.አ. በ1837 ዓ.ም የካናዳን አማፂያን የተሳፈሩበትን የካሮላይንን መርከብ ለመምታት በኒጋራ ፏፏቴዎች አቅጣጫ ወደ አሜሪካ ድንበር ዘልቀው ገብተው ጥቃት አድርሰዋል። ይህ እርምጃ “Caroline Incidence” ተብሎ ይታወቃል። እስራኤል እ.ኤ.አ. በ1967 ግብፅን አስቀድማ የመታችው በ”Anticipatory Self defence” መርህ ነበር። አሜሪካ ኢራቅን፣ አፍጋኒስታንና ሱዳንን በየወቅቱ ያጠቃችው በ”Anticipatory Self Defence” መርህ ነው። በተለይም በሱዳን ላይ ጥቃትን በሰነዘረች ጊዜ ያወደመችው እንደገመተችው የአሸባሪዎችን ካምፕ ሳይሆን የመድኃኒት ፋብሪካን ነበር፣ ይህም ከፍተኛ ውግዘትን አስከትሎባታል።
ይህን ሁሉ ርቀት የመጣሁት የሴኩቱሬን ቅጥ አምባሩ የጠፋውን ማብራሪያውን legitimize ለማድረግ እንዳልሆነ ብዙዎቻችሁ የምትረዱኝ ይመስለኛል። ሴኩቱሬ ግን አንድ ውለታ ውሎልን አልፏል፦ በቃ “Anticipatory Self-Defence” የሚለውን ፅንሰ ሐሳብ በተነፈሰበት ቅፅበት፣ ጦርነቱ በሕወሓት እንደተጀመረ በቪዲዮ የተደገፈ ግልፅ ማስረጃ ሰጥቶናል፣ ምክንያቱም ይህ እርምጃ ሁሌም የሚወሰደው በጠላትነት ከተፈረጀው ቡድን ጥቃት አስቀድሞ ነው። ታዲያ ታምራት ላይኔ በወቅቱ “ጦርነቱን ማን እንደጀመረው ወደፊት በገለልተኛ አካላት ይረጋገጣል” ብሎ ሲናገር ሰምቼው፣ የምር ይህ ሰው የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር ነበር? በማለት ራሴን እስከ መጠየቅ ደርሼአለሁ። ምክንያቱም ታምራት ጦርነትን ከማንም በላይ በተግባር ጭምር የሚያውቅ ሰው ነው፣ ነገር ግን ሴኩቱሬ በግልፅ በ”Anticipatory Self-Defence” ጦርነቱን የጀመርነው እኛ ነን እያለ ሲናገር፣ ታምራት ወደፊት ማን እንደጀመረው ይጣራል እያለ ከሴኩቱሬ ይልቅ ስለ ሁኔታው እንደሚያውቅ ሰው ሊተነትንልን ይሞክራል፣ አያድርስ ነው!
ሌሎች የሕወሓት አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች ደግሞ የሴኩቱሬን ማብራሪያ አንዴ “Pre-emptive” ሌላ ጊዜ ደግሞ ሁለት የጦር አይሮፕላን ቀደም ሲል በትግራይ ክልል ሲበር ነበር እያሉ ያለ የሌለ ማብራሪያ በመስጠት የሴኩቱሬን እውነተኛ ማስረጃ ለመሸፋፈን ደፋ ቀና ሲሉ ተስተውለዋል። Anticipatory ሌላ፣ pre-emptive ሌላ!
ሆኖም ግን ሴኩቱሬ ማስረጃውን ይስጠን እንጂ ማብራሪያዎቹ በሕፀፆች የታጨቁ ነበሩ።
1. “Anticipatory Self Defence” ቢፈቀድ እንኳን ትግበራው የሚመለከተው በተባበሩት መንግስታት ውስጥ በሀገርነት የተመዘገቡ ሀገራትን ብቻ ነው። የተባበሩት መንግስታት ቻርተር የሀገራት እንጂ የክልል መንግስታት ቻርተር አይደለም። ስለዚህ ዓለም አቀፍ ሕጎች የሚፈቅዱት ፅንሰ ሐሳብ ነው የሚለው ማብራሪያው ሙሉ በሙሉ ስህተት ነው። እሱን አይመለከተውም።
2. ሴኩቱሬ “Anticipatory Self Defence” የሚተገበረው... ትንንሽ ሀገራት (ትግራይን እዚህ ውስጥ ከትቷት ይሆን?) በትላልቅ ሀገራት ሊዋጡ እንደሆነ ማስረጃው ሲኖር... እያለ ያብራራውም ስህተት ነው። ይህ ራስን ከጥቃት አስቀድሞ የመከላከል ሕግ የሚሰራው ለሁሉም የተባበሩት መንግስታት አባል ሀገራት ነው። ትንሽ ትልቅ የሚል ተረት ተረት የለውም።
3. “Anticipatory Self Defence” መከወን ያለበት ከአቅም ግምገማ በኋላ ነው። ዘመን ያለፈበትን ክላሽ ይዘህ ድሮን የታጠቀውን ጦር በ”Anticipatory Self Defence” ቀድሜ እመታዋለሁ ብሎ መነሳት የኢንተለጀንስ ሥራ ድክመትን፣ የጦርነት መረጃ እጥረትን ያመለክታል። ሌሎቹ ሀገራት “Anticipatory Self Defence”ን የሚተገብሩት የጠላትን ጦር አቅም በሚገባ ከፈተሹ በኋላ ነው። የሚጠቃው ጠላት አቅሙ የደረጀ ከሆነ ምናልባትም በሰላም ምድር ጦርነትን እንደ መጥራት ይቆጠራል። በሰሜኑ ጦርነት በተግባርም ያየነው ይህንኑ ነው።
4. በመጨረሻም “Anticipatory Self Defence”ን መተግበር ከተጠያቂነት አያስመልጥም፣ ምክንያቱም አንድ ሀገር ይህን እርምጃ ከመውሰዱ አስቀድሞ መፈተሽ ያለባቸው በጥቂቱ ወደ አራት መስፈርቶች አሉ። በነገራችን ላይ ከላይ የጠቀስኳቸው ሀገራት ማለትም እስራኤልና አሜሪካ ጥቃቱን በተመለከተ ለተባበሩት መንግስታት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተጠርተው ነበር።
ሳጠቃልል፦ ትናንት ሕወሓት የደረደራቸውን ቅድመ ሁኔታዎች ተመለከትኩና ሴኩቱሬና መግለጫው ትዝ አሉኝ። የኢትዮጵያ መንግስት ይህን የሴኩቱሬን የማስረጃ አበርክቶት ለሙግቶቹ የተጠቀመበትን አግባብም ለማወቅ ፈለግሁኝ። በነገራችን ላይ እነ አሜሪካ ሕወሓት ጦርነቱን አስቀድማ እንደጀመረችው ያውቃሉ፣ በግልፅ ሲናገሩም ነበር፣ የኢትዮጵያ መንግስት ዲፕሎማቶች ግን በዚህ ረገድ ገፍተው የሄዱ አይመስለኝም። በእርግጥ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር በሶሻል ሚዲያ ለመግለጫው የእንግሊዝኛ ካፕሽን ጨምሮበት ለቅቋል። ከዚህ ባለፈ የዚህ ቪዲዮ ቅጂ ተተርጉሞ ለተባበሩት መንግስታት ተሰጥቶት እንደሆነ መረጃው የለኝም። ምክንያቱም በየትኛውም ሕግ ጦርነቱን አስቀድሞ የለኮሰው አካል ለደረሱት ድህረ ጦርነት ቀውሶች ቅድሚያ ተጠያቂ እንጂ ቅድመ ሁኔታ ደርዳሪ የመሆን ሞራል የለውም። እውነትን መያዝ ብቻውን በቂ አይደለም፣ እውነት በተግባቦት ጥበብ ተከሽና ካልቀረበች ባክና ትቀራለች። ካለመናገር ብዙ ነገር ይቀራል፣ ትኩረት ለዲፕሎማሲያችን!

  (አማን መዝሙር)
ጋሼ ... አንዳንዴ ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል። ህውሃት የትግራይ ህዝብ ጠላት ባይሆንም፣ ለትግራይ ህዝብ ግን ጠላት ሲገዛለት ነው የኖረው። ግራ ዘመሞቹ ህውሃቶች ትግራይ ከሰላሳ አመት በፊት ያልነበራት የችግር አረንቋ ውስጥ ጨምረዋታል። ከሰላሳ አመት በፊት ከተራ አተካሮ ባለፈ ኤርትራ የትግራይ ጠላት አልነበረችም። ከሰላሳ አመት በፊት ትግራይ ከአማራ ጋር ምንም አይነት የመሬት ግጭትም ሆነ ይሄ ነው የሚባል ጠብ አልነበራትም። ከሰላሳ አመት በፊት ትግራይ ከሱማሌ ከአፋር፣ ከደቡብ፣ ከኦሮሞ፣ ከአማራ ጦር ጋር ጋር እንዲህ በግልፅ ጠብ ውስጥ አልገባችም። ከሰላሳ አመት በፊት ትግራይ ከፌደራል የሚሄድላት በጀት አልተቋረጠባትም። መብራት፣ ስልክና ነዳጅ አልተቋረጠባትም። ከሰላሳ አመት በፊት የትግራይ ሰው በአማራም ሆነ በየትኛውም የኢትዮጵያ ክፍል ሄዶ ሲኖር ምንም የባይተዋርነት ስሜት አይሰማውም። በጥርጣሬም አይታይም ነበር።
አሁን
ትግራይ ወድማለች። ብዙዎች ተሰደዋል። ብዙዎች ተደፍረዋል። ብዙዎች በረሃብ አልቀዋል። ከፊት ብዙ ርሃብ አለ። ህዝቡ በዚህ ስቃይ ውስጥ ሆኖም ህውሀት ህዝቡን ለማይረባ pride እና ego ሲባል ለከባድ ጦርነት እያዘጋጀችው ነው።
ጥያቄ
ህዝቡ የፈለገውን የመደገፍ መብት አለው። ግን መች ይሆን ያልነበረውን ጠላት ያፈሩለት፣ እነሱ በዘረፉት ንፁሁን ሰው ባልበላው ያስወቀሱትን። 17 አመት በጦርነት አቆይተውት፣ አሁንም ለማያባራ ጦርነት ያዘጋጁትን ያረጁ ያፈጁ ሽማግሌዎች ቆም ብሎ የሚጠይቀው? ህውሀት ሃይማኖት ነች እንዴ። ደብረፂዮን ተሰቅሎልናል እንዴ? ጌታቸው አሰፋን ያመነ መንግስተ ሰማይ ይገባል እንዴ? አብዮታዊ ዲሞክራሲ ከሰማየ ሰማይ የወረደ እንከን አልባ ወንጌል ነው እንዴ? የህውሀት ማእከላዊ ኮሚቴዎች ለነፍሳቸው ያደሩ ደቀመዛሙርት ናቸው እንዴ?
ይሄ መልስ የሌለው ጥያቄ ስለሆነ ይብራብኝና አንድ ነገር ተናግሬ ላምልጥ ...
አለም ላይ የሌለ፣ ምርጫ ቦርድ የሌለበት፣ የክልል ምርጫ አካሂዳለሁ ያለችው ህውሃት። በየቀኑ የኮማንዶ ትርኢት እያሳዩ ክልሏን ሰሜን ኮሪያ ያስመሰሏት እነሱው፣ ምርጫ ካደረጉ በኋላ ከዚህ ወዲያ ለፌደራል መንግስቱ አንታዘዝም ብለው መግለጫ ያወጡት እነሱ፣ ከፌደራል መንግስቱ የሚላኩ አመራሮችን በመጡበት አውሮፕላን የመለሱት እነሱ። መጨረሻም መከላከያን ገድለው ህዝባቸውን ለስቃይ የተዉት እነሱ!
ትግራይ ህዝብ ላይ የደረሰው ስቃይ ቢያሳዝነኝም። ለዚህ ሁሉ ግፍ የመጀመሪያው ተጠያቂ ህውሃትና የህውሃት ደጋፊዎች ናቸው! ለትግራይ እናዝናለን ስንል «ምናገባህ?» የሚል የህውሃት አገልጋይ ይመጣል። ሰውዬ ስለ ትግራይ ለማሰብ ለማወቅ ያንተ አፕሩቫል አያስፈልገኝም። ትግሬ ስለሆንክ ከኔ በላይ ለትግራይ ታዝናለህ ማለትም አይደለም።
ብሔር የምርጫ ጉዳይ ነው። ደም አይደለም። ብፈልግ ነገ ተነስቼ ትግሬ መሆን እችላለሁ።


ከርቀት ስትታዘበው -
ተከዜ ወንዝ የሚመስል - በከርሱ ውሃ
የያዘ፤
ተሻግረኽ ስትጠጣው ግን -
ከባሩድ በላይ የሚገድል - በሄምሎክ
የተመረዘ፤
ሸለቆው ማዶ ቁጭ ብለህ -
ባሻገር ያለውን ጋራ - አድማሱን
ስታስተውለው፤
አልፈኸው እስክትሄድ ድረስ -
ሐኖሱ ድባቡ ሁላ - እናት ኢትዮጵያን
መሳይ ነው፤
‹‹ይሄ አገር ማን ነው›› የምትል -
ወንዙን ስትሻገረው፣ መርዙን
ስትጎነጨው፤
ጉድ ነው!
አገሬ ልንገርሽማ፥ ምን ምን እንዳጋጠመኝ-
ስሚማ በመይሳው ሞት
ሕይወቴ ያንቺ ሆኖ ሳለ - ስሜቱን
ከሥሙ ጋር - ለእኔ የሰጠ ድርጅት
ከሴት ደፋሪ መድቦኝ- ሥሜን እንደ ጥጥ
ሲያባዝት
ያንን የሰሜን አርበኛ -
ከአንበጣ ተርታ መድቦ - ጨፍጭፎ ያደረ
ባንዳ፤
ከዝንጀሮ ጋር ሸምቆ-
ሌባ ዘራፊ እያለ- ሲነዛ ፕሮፓጋንዳ፤
ቄስሽ መስቀሉን ጥሎ- ቦንብ ታቅፎ   
ሲንጋጋ
በምሞትለት ስጠቃ- በምዋጋለት ስወጋ፤
ደፍረውኝ እንደ ደፋሪ- ሰልበውኝ እንደ
ሰላቢ
ክደውኝ እንደ ከሃዲ - ወግተውኝ እንደ
ደብዳቢ
ሶሪያ እንደተገኘ-
በባዕድ ስሜት ተውጬ- ስልልሽ ‹‹ያላህ
ያረቢ››
አክሱም ጽዮንን አጥፍቶ- ለደብረ ጽዮን
የሚሰግድ፤
የሚረዳኝ ብቸኛ ጌታ -
ጌታቸው ረዳ ነው ብሎ - እግዜር አላሁን
የሚክድ፤
ሲገድል ጀጋኑ የሚባል - ሲሞት ንጹሕ
የሚሆን፤
ከተኩሶ ክሱ በርትቶ - ሲለቀልቀኝ
እድፉን፤
ታጣቂ ካላየ በቀር-
መባረቅ የማያሰኘው - መተኮስ
የማይችል ክላሽ፤
መያዜን ያወቀ ውርጋጥ -
ተኩሶ ከሸሼ ወዲያ - እኔን ሲያደርገኝ
ተከሳሽ፤
እናም እናታለሜ-
እንደ አምናው ሁሉ ዘንድሮም - ነፍሴን
ልሰጥሽ ወጥቼ
ጠላትሽን ከመታሁ ወዲያ -
እያነባሁ ነው የወጣሁ - ምድሩ ላይ
አንቺን አጥቼ፡፡

 ኢትዮጵያ ዘመም ስትልና ስትቃና የኖረች አገር ናት፤ በነዋሪዎቿ መካከል ያለው አንድነት ባንዱ ዘመን ይታመማል፤ በሌላው ዘመን ይታከማል::
ዛሬ ጋብ ባለ ጦርነትና መልኩ ባልታወቀ መጭ ዘመን መሀል ቆመናል፤ ተደባብረናል፤ ተጠማምደናል፤ “እንገንጠል” “ይገንጠሉ“ የሚሉ የቃላት ልውውጦች አየሩን ሞልተውታል፤
ግን ታሪክን ብናይ ሌላም አማራጭ ያሳየናል፤ ባንድ ዘመን እንቀሳሰፋለን፤ በሌላው ዘመን እንተቃቀፋለን፨
ከዘመነ መንግስታቸው ባንዱ ቀን፤ አጤ ዮሀንስ ከንጉስ ተክለሃይማኖት ጋራ ተጣሉና ወደ ጎጃም ዘመቱ፤ ለጊዜው አውራውን ቢያጡት ህዝቡን መቱት፤ ህዝቡም አጥብቆ ረገማቸው፤ የሳቸው ቤተ መንግስት ጸሃፊ “ንጉሱ ወደ ሰው በላው አገር ዘመተ" እያለ ጣፈ፤ ከጥቂት ጊዜ በሁዋላ በጎጃም ጌታና በንጉሰነገስቱ መሀል እርቅ ተደረገ፤ አጤ ዪሀንስ ተጠጠቱ፤ ጎጃምን “የሰው በላዎች አገር" በሚል የሚፈርጀውን ስድብ ከብራናው ላይ አስፋቁት፤ ብዙም ሳይቆዩ የበጌምድር ህዝብን ከጠላት ሲከላከሉ ከብዙ ትግራዮች ጋራ ተሰው፤
ከአመታት በሁዋላ ጣልያን በጀልባ ተሻግሮ ሲወር ጎጃሜ ለትግራይ ሊመክት ዘመተ፤ አገር ቀጠለ፤
በልጅ ኢያሱ ዘመን ደጃቸ አብርሃ ሸፈቱ፤ የደጃዝማች አባተ ጦር ተላከባቸው፤
“የዳኘው አሽከር የጦር ገበሬ
አይበገርም ላብርሀ ወሬ"
እያሉ እየፎከሩ ዘመቱ፤ አብርሃና ጭፍሮች ኮረም ላይ ተሸንፈው ተማርከው ወደ ሸገር ተወሰዱ፤ በኢያሱና በመኮንኖቹ ፊት ለፍርድ ቀረቡ፤ ካሸናፊዎች ወገን የሆነ አንድ ሰው እንዲህ አለ፤ “ይህንን ጥፋት ያጠፉት ትግሮች ሁሉ መክረው ነው እንጂ አብርሃ ብቻቸውን አልሰሩትምና ትግሬዎች ሁሉ ይቀጡልኝ"
ልጀ ኢያሱ የሰውየው እብሪት አገር የሚያነድ ክብሪት ሆኖ ታያቸው፤ ተናጋሪውን አስጥለው ጀርባውን ባርባ ጅራፍ ማሳጅ አስደረጉት፤ የጅራፉ ድምጥ ሲያባራ ሸዌና ትግራይ አብሮ መኖር ቀጠለ፤
እኛም እንዲሁ እምንቀጥል ቢመስለኝ ምን ይገርማል፤
በዘንድሮው ጦርነት በየፊናው የተጎዱ ዜጎች፣ ይህ ቃሌ እንደማይዋጥላቸው እገምታለሁ፤ ያልተነካ ግልግል ያውቃል ቢሉኝም አልፈርድባቸውም፤ ግን ያልተነካም ይሁን ያልተከካ ከሆነ ቦታ ገላጋይ መምጣት አለበት፤ ቀደምቶቻችን ከኛ በላይ ተደባድበዋል፤ የሽንፈትን መራራ ጥዋ በየፈረቃው ቀምሰዋል፤ ተገነጣጥለው ያልጠበቁን መገንጠል የሚባለው ነገር “ነፋስን መከተል" ሆኖ ቢታያቸው ነው፤ የጂኦግራፊ ቁራኛ ሆነህ አንዴ ከተፈጠርህ በሁዋላ መገንጠል የሚባለው ነገር ቅዠት ነው፤
አሁን ባለንበት ሁኔታ የማእከላዊ መንግሰት ሆነ የክልል መንግስት አውራዎች መጀመርያ ማድረግ ያለባቸው ዛቻ፤ አሽሙር፤
ጦርነት ጉሰማ መቀነስ ነው፤ ከዚያ የህዝቡን የጋራ ካፒታል ተጠቅሞ ለርቅና ለሰላም መስራት፤
ከጂኦግራፊ ባሻገር በትግራይና በአማራ ህዝብ መሀል ትልቅ ማህበራዊ ካፒታል አለ፤ የግእዝ ፊደል፤ ከብሉይና ሀዲስ የተቀዳ ባህል፤
“የጎንደር ሃይማኖት ቆማ ስታለቅስ
አንገቱን ሰጠላት አጤ ዮሀንስ”፤ “አይነትና መሰል የጋራ ሰማእትነት ታሪኮች ፤ ወዘተ፤
የቸከ ቢመስልም ይህንን ለማለት እፈልጋለሁ፤
ምላጭ የሚያስውጥ እልህህን ዋጥ አደርገህ ቁጭ ብለህ ተነጋገር፤ ስለ እርቅ፤ ስለ ጉማ፤ የጋራ አገርን አልምቶ በጋራ ስለ መክበር ተነጋገር፤ ያለፈው አልፏል፤ በህይወት የቀረነው አብረን እንድንኖር ተፈርዶብናል፤ ምርጫ ካለን በሁለት ነገሮች ላይ ብቻ ነው፤ እየተራረድን ወይስ እየተራረምን እንኑር? ሁለተኛውን ተስፋ አደርጌ ልተኛ!

Tuesday, 15 June 2021 20:03

ከፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ

Written by
“ማመቅ” ወይስ “ማሟሟት”?!
ሙሼ ሰሙ
 
የማሳቹሴት ገዢና 5ኛው የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት የነበሩት ኤልብሪጅ ጄሪ፣ የዴሞክራቲክ ፓርቲ እጩዎች እንዲያሸንፉ በሚያመቻች መልኩ ዲስትሪክቶቻቸውን በአዲስ መልክ እንዲካለሉ የሚፈቅድ ቢል ማጽደቃቸውን ተከትሎ፣ “ጄሪ ማንደሪንግ” የሚባል ቃል ተፈጠረ።
“ጄሪ” ከኤልብሪጅ ጄሪ ስም የተወሰደ ሲሆን “ማንደር” ደግሞ “ሳላማንደር” ከተባለው የድራገን ዝርያ በመዋስ የተፈጠረ ድቅል ቃል ነው። “ሳላማንደር” የሚለው ቃል መነሻው አንዱ አዲስ “ክልል” የአፈ ታሪኩን ድራገን “ሳላማንደር” በመምሰሉ ነበር። ዛሬ ላይ ቃሉ ከመለመዱ የተነሳ ምርጫን ለማጭበርበር አዳዲስ አከላለልን የሚፈጥሩ መንግስታት መጠርያ ሆኗል።
የሳላማንደር “መንግስታት” በሳላማንደሪንግ ድምጽን ለማፈን ሁለት ስትራቴጂ እንደሚጠቀሙ ይወሳል።
1ኛ) መፈልቀቅ/ማሟሟት (Cracking) ይባላል። የተቃዋሚ ፓርቲ መራጮችን በሰፊ አከላለል ውስጥ በመበተን ወይም ወረዳን ወደ ክፍለ ከተማ በማሳደግ የተቃዋሚን ድምጽ በማሟሟት (Dilute) ድምጻቸውን ማሳሳት ነው።
2ኛ) ማመቅ (Packing) ይባላል። የተቃዋሚ ፓርቲ መራጮችን ድምጽ በአንድ አካባቢና ዝቅተኛ መስተዳድር፣ ቀበሌ ወይም ወረዳ እንዲታጨቅ በማድረግ ድምጻቸውን ማፈን ነው።
በነገራችን ላይ ኢህአዴግ በ1997 ላይ አንዳንድ የአዲስ አበባ ወረዳዎችን በማጣመርና ሌሎችን በመክፈል ጄሪ ማንደሪንግ ሰርቷል። ለምሳሌ ወረዳ 17 ላይ 4 ገበሬ ማህበር በመደበል፣ ከወረዳ 15 ላይ ግማሹን ከወረዳ 18 ጋር በመቀላቀል፣ ቃሊቲና አቃቂን በማዋሃድ ወዘተ...
6ኛው የአዲስ አበባ ምርጫ እጩ አቀራረብ፣ ከወረዳ ወደ ክፍለ ከተማ መስፋፊያዎችን ከነባሮቹ ጋር ማጣመሩና 6 እጩ ከማቅረብ በክፍለ ከተማ ደረጃ 14 እጩ ወደ ማቅረብ መሸጋሸጉ የትኛውን “ጄሪ ምንደራ” ሊመስል ይችላል?! “ማመቅ” ወይስ “ማሟሟት”?! ከውጤቱ የምናየው ይሆናል?!!



አንዳንዴ ደሞ ጎህ ቀዶ
አብሮኝ ያደረው ደወል፤ ከራስጌዬ
ተጠምዶ
ከወፎች ቀድሞ ሲያመጣልኝ “ነግቶብሃል”
የሚል መርዶ
ብትት ብዬ፤ ደንብሬ
ግማሽ ፊቴን ትራሴ ውስጥ ቀብሬ
“እኮ ዛሬም እንደወትሮ
ካውቶብስ ወደ ቢሮ
ከኬላ ወደ ኬላ
ዛሬም በግንባሬ ወዝ ልበላ
እሺ ከዚያስ በሁዋላ?”
እያልሁ ልቤን ስሞግት፤ መልሱን
አያመለክተኝ
ይሄን ያህል ነው የታከተኝ፤
ጉዞዬ፤ ካዋላጅ እቅፍ፤ እስከገናዦች አልጋ
ባራት አግር ተጀምሮ፤ ባራት ሰው ሸክም
እስኪዘጋ
መንገዱ መንገድ እየሳበ
ትንንሹ ዳገት ፤ለትልልቁ እያስረከበ
እንደ ሀረግ ስጎተት፤ እንደ ጥንቸል ስፈጥን
“ምን ሽልማት ታሰበልኝ? ይህ ልፋቴን
የሚመጥን
እያልሁኝ ሳውጠነጥን፤
አንዳንዴ ደሞ ሲመረኝ
እንደ ለማዳ ፈረስ፤ ሞትን በፉጨት
መጥራት ሲያምረኝ፥
ዛፉን የተቀማ አሞራ
በኮረንቲ ምሶሶ ላይ፥ ጎጆው ባዲስ መልክ
ሲሰራ
ማርዋን የተዘረፈች ንብ፤ በየአበባው
ስትሰማራ
አይና
እንዲህ እንዲህ እላለሁ፤ እርስ በራሴን
ሳጽናና፡ -
ሺህ ጊዜ ብትራቀቅ ፤ ቃላት መርጠህ
ብትገጥም
ከዚህ አሞራ አታንስም ከዚች ንብም
አትበልጥም
ተፈጥሮ ትግልን እንጂ፤ የድል ዋስትናን
አትሰጥም
ቻለው!

 በጦርነት ወቅትም ሆነ በድህረ ጦርነት በሲቪሎች ላይ የሚደርሱትን ሰብዓዊ ጥቃቶችን እቃወማለሁ፣ በተለይም በሴቶች ላይ የሚደርስ የትኛውም ዓይነት ጥቃት መወገዝ ያለበትና ጥቃት አድራሾቹንም ለፍርድ ማቅረብ አሌ የማይባል ነው። በዚህ ርዕሰ ጉዳይ በሰሜኑ ጦርነት ወቅትም ሆነ በድህረ ጦርነቱ ከአንዴም ሁለቴ የተቃውሞ ሐሳቤን አጋርቼአለሁ።
በአሁኑ ወቅት የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ በተፈጠረው ሰብዓዊ ጥቃቶች ዙሪያ የውጭ ሀገር መንግስታት ድምፃቸውን እያሰሙ ነው፣ ለዚህም ራሷን እንደ ዓለም አቀፍ ፖሊስ የምትቆጥረው አሜሪካ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳለች፤ አሁን ደግሞ በተለይም በሴቶች ዙሪያ የሚፈፀሙትን ጥቃቶች ተከትሎ የሰሜን አትላንቲክ ስምምነት ድርጅት (ኔቶ) በየትኛውም ሀገር ጣልቃ መግባት የሚችልበትን መንገድ እየጠራረገች ትገኛለች።
ሁሌም በተደጋጋሚ እንደሚባለውና የአሜሪካ መንግስትም ሰርክ እንደሚናገረው፣ የአሜሪካ የውጭ ፖሊሲዋ የተመሠረተው ገና ከመነሻው የአሜሪካን ጥቅም ከማስቀጠልና ከማስጠበቅ አኳያ ነው። ለዚህ ዋና አጀንዳዋ የአሜሪካ መነሻ ሰበቧ ግን ሌላ ሊሆን ይችላል። በእኔ ዕይታ በተለይም በጦርነት ወቅትም ሆነ በድህረ ጦርነት በሴቶች ላይ በሚፈፀሙ ወሲባዊ ጥቃቶች ዙሪያ አሜሪካ ራሷን ንፁሕ አድርጋ ሌሎችን ለመክሰስ ተፍ ተፍ የምትልበት ፍጥነት ትዝብት ላይ የሚጥላት ነው። ምክንያቱም በኢራቅና አፍጋኒስታን ከሴቶች ወሲባዊ ጥቃት ጋር በተገናኘ የአሜሪካ ወታደሮች የነበራቸው ስም እጅግ አሳፋሪና ዘግናኝ ነበር።
አሜሪካ በወታደሮች የሚፈፀሙ ጥቃቶችን በተመለከተ ሌሎችን ለመኮነን በአጭር ታጥቃ በተነሳች ቁጥር ትዝ የምለኝ የኢራቃዊቷ የ14 ዓመት ሕፃን “Abeer Qassim Hamza al-Janabi” የመደፈርና የመገደል ሰቆቃ ነው። ነገሩ እንደዚህ ነው፦ እ.ኤ.አ. በ2006 ዓ.ም. “Steven Dale Green” የተባለ የአሜሪካ ወታደር ከሌሎች ሦስት ባልደረቦቹ ጋር በመሆን ከባግዳድ 30 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ወደምትገኝ መንደር አብረው ከሄዱ በኋላ ከላይ የጠቀስኩላችሁ ሕፃን ልጅ ቤት ይገባሉ። እነዚህ የአሜሪካ አረመኔ ወታደሮች ወደ ቤት ከገቡ በኋላ የልጅቷን አባት እናትና ታናሽ እህቷን አስቀድመው ከገደሉአቸው በኋላ በተለይም “Steven Dale Green” የተረፈችውን የ14 ዓመት ሕፃን ከደፈራት በኋላ እሷንም ይገድለታል፤ ይህም አልበቃ ሲለው አስከሬኗን በእሳት አቃጠለ። “Steven Dale Green” ለፈፀመው ወንጀል የዕድሜ ልክ እስር ከተፈረደበት በኋላ እ.ኤ.አ.በ2009 ዓ.ም. ራሱን በታሰረበት ክፍል አጥፍቶ ተገኝቷል።
አሜሪካ የሴቶች ወሲባዊ ጥቃት ጠበቃ ሆና በምትቆምበት ቅፅበት ሁሉ ከኢራቃዊቷ “Abeer Qassim Hamza al-Janabi” በተጨማሪ ትዝ የምትለኝ አሜሪካዊቷ “Jessica” ነች። የአሜሪካ ወታደሮች የወሲባዊ ጥቃት ወንጀል ለገዛ ዜጎቻቸውም ጭምር የሚዳረስ ነው። “Jessica” የአሜሪካ ሚሊተሪ አባል ነች (ስሟ ለደህንነቷ ሲባል ተሰውሯል)፣ ነገር ግን በሚሊተሪ አለቆቿ ወሲባዊ ጥቃት ደርሶባታል። በአሜሪካ የሚሊተሪ ተቋም ከሶስት ሴቶች በአንዷ በአለቆቻቸው ወሲባዊ ጥቃቶች እንደሚደርሱ ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ (As many as one in three women in the US military are raped during their service, studies suggest [GALLO/GETTY])
ታዲያ ችግሩ በዚህ ብቻ የሚቆም አይደለም። ብዙዎቻችን አሜሪካ ፍትሕና ዲሞክራሲ የሰፈነባት ሀገር ስለሆነች ወሲባዊ ጥቃቱን በሚፈፅሙ የሚሊተሪ አባሎቿ ላይ ፈጣን እርምጃ እንደምትወስድ አድርገን እንቆጥር ይሆናል፣ ነገር ግን ጥቃቱ የደረሰባቸው የሚሉን ተቃራኒውን ነው። ይልቁን ወሲባዊ ጥቃቱ የደረሰባቸው ሴት ወታደሮች ጥቃቱን ሪፖርት በሚያደርጉበት ወቅት ፍትሕ ማጣታቸው እጅግ የሚዘገንን ነው። እስቲ ከላይ የጠቀስኳት የጥቃቱ ሰለባ የምትለውን ከራሷ አንደበት እንከታተል፦
“My experience reporting military sexual assault was worse than the actual assault.The command has so much power over a victim of sexual assault. They are your judge, jury, executioner and mayor: they own the law. As I saw in my case, they are able to crush you for reporting an assault.”
የአሜሪካ ወታደሮች በኢራቅና አፍጋኒስታን ቆይታቸው የፈፀሙአቸው ወሲባዊ ጥቃቶች ተቆጥረው የሚያልቁ አይደለም፣ አምኒስቲ ኢንተርናሽናል እና ሂዩማን ራይትስ ዎች ቆጥረው ይዝለቋቸው። በወቅቱ የቡሽ አስተዳደር ይህን ገመናውን ለመሸፈን የተቀረፁትን ምስሎችንም ሆነ ቪዲዮችን ለመሰወር የማያደርገው ጥረት አልነበረም። ታዲያ ይህ ሁሉ ግፍ ሲፈፀም የዛሬው ኔቶ የት ነበር? አሜሪካ ዓይኗ ውስጥ የተሰነቀረውን ግንድ የሚያክል ገመናዋን ደብቃ የሌሎችን ጉድፍ ለማየት የሞራል ድፍረቱን ያገኘችው ከወዴት ነው? ወሲባዊ ጥቃትን ማውገዝና መቃወም በአሜሪካኖቹ አያምርባቸውም፣ ይልቁን የተሻለ ሞራልና ሰብዕና ያለውን የሚሊተሪ ተቋማትን የገነቡ ሀገራት ቢቃወሙ መልካም ነበር። ስለዚህም አሜሪካ ከሁሉ አስቀድማ ኔቶን በራሷ ላይ ታስዘምት! ፅዳቱ ከራስ ይጀምር!


Saturday, 12 June 2021 13:16

ብድር በምድር!!

Written by

  የመሳፍንት ዘመን አብቅቶ አንዲቷን አትዮጵያ የማየት ህልም የነበረው ደጃች ካሳ (አፄ ቴዎድሮስ)፤ ራስ አሊንና ደጃች ጎሹን አሸንፎ ሀይሉን አጠንክሮ፣ሰራዊቱን አብዝቶ፣ የጎጃሙን ደጃች ብሩን “ግባ” ብሎ ሰደደበት። ደጃች ብሩ ልበ ደንዳና፣ ትዕቢተኛ ነበርና በንቀት “አንተ የኮሶ ሻጭ ልጅ፤ ወንድ ከሆንክ ግጠመኝ” ብሎ መልዕክት ልኮበት፣ እርሱ “ሶማ አምባ” የምትባል ቦታ ላይ ከተተ!
ደጃች ካሳም ወደ ጎጃም ዘልቆ፣ ሶማ አምባን ከቦ ተቀመጠ። ጉዳዩን በሰላም መጨረስ የፈለገው ደጃች ካሳ፤ ለመግባቢያ ይሆን ዘንድ አሽከሩን ወደ ደጃች ብሩ ልኮ፤ “የፈረስዎን ስም አባ ዳምጠውን ለኔ ይተውልኝ ፤ አይሆንም ያሉ እንደሆነ ለፈረሴ ሌላ ስም ያውጡልኝ” አለው።
ትዕቢተኛው ደጃች ብሩ “ፈረስህን "ትንጓለል በለው” ብሎ ላከበት፡፡ የዚህን ጊዜ ካሳ በብስጭት ፀጉሩን እስኪነጭ ድረስ ተናደደ።
የሶማ አምባ ምሽግ ጠንካራ እንደሆነ የተረዳው ካሳ፤ አዘናግቼ እይዘዋለሁ ብሎ ወደ ሜንጫ ተመለሰ። የካሳ የሰራዊት ብዛት ከጠበቀው በላይ የሆነበት ደጃች ብሩ፣ የካሳን ምሽግ መፍታት እንዳወቀ እግሬ አውጭኝ ቡሎ ወደ ኩታይ ኦሮሞ ሸሸ !! የኦሮሞ ፈረሰኞችም “በካሳ ታስፈጀናለህ፤ አንደብቅህም” ብለው ለካሳ ይዘው አስረከቡት። ደጃች ካሳም አርባ አምባ አስገብቶ ከሚስቱ ነጥሎ አሰረው!
የደጃች ብሩ ሚስት የሆነችው የውብዳር ከእስር ቤቱ አሽከሮች መካከል አንዱን መርጣ ውሽማ አደረገችው፡፡ ውሽማውም መሸት ሲል ጠብቆ እየገባ፣ የውብዳርን አጮጩሇ ይወጣ ጀመር። ይህንን ነገር ደጃች ብሩ በሰማ ጊዜ አዘነ! መጫወት በሚወደው በገናውም እንዲህ ብሎ አዜመ!
መከራን እንዲያ በሰው ላይ ሳቀለው
ምነኛ ከበደኝ እኔ ስይዘው
መከራ ሲመጣ አይናገርም አዋጅ
ሲገሰግስ አድሮ ቀን ይጥላል እንጅ
ደጃች ብሩ ይህንን የገጠመው እርሱ የጎጃም ገዥ በነበረበት ወቅት ህዝብ ላይ የሰራው ግፍ ትዝ ብሎት ነው። ደጃች ብሩ የጎጃም ህዝብ ላይ ከሰሩት ግፍ መካከል በጣም የሚያስገርሙትን ሶስቱን ልጥቀስ!
አሁን ላይ ከድታው በአሽከር ሞፈር የምትታረሰው የውብዳር፣ ቀድማ ቤተ ክርስቲያን ሳትገባ በፊት ማንም መግባት አይችልም ነበር። ገብቶ የተገኘ ሰው እንደ በረዶ ዱላ ይወርድበት ነበር!
ቤተ መንግስቱን ከምስጥ ለመከላከል ብሎ ህዝብን በወረዳ በወረዳ አደራጅቶ፣ አስር አስር እንስራ ጉንዳን እንዲያመጡ አዟቸው ነበር። ባላገሩ ጉንዳን እያደነ በሳምባ ሰብስቦ፤ እንስራውን ይዞ ሲሄድ ጉንዳኑ እየነከሰ ቢያስቸግረው በእንጉርጉሮ መከራውን እንዲህ ብሎ ገልጦ ነበር፡-
ከመከራው ሁሉ የጉንዳኑ ባሰ
የገባሪውን ጆሮና ትከሻ እየነከሰ
"ለበቅሎዬ የሆድ ቁርጠት መድሃኒቱ የሴት ብልት ፀጉር ስለሆነ አምስት አምስት መስፈሪያ ጠጉር አምጡ; ብሎ ህዝብን አስለቅሶት ነበር። ያን ጊዜ ሴት ዘመድ የሌለው ሰው፤ ጭገር ልመና በየሰው ቤት ተንከራተተ። እንግዲህ እኒህ እና ሌሎች ግፎቹ ትዝ ቢሉት ነው።
መከራን እንዲያ በሰው ላይ ሳቀለው
ምነኛ ከበደኝ እኔ ስይዘው
--ብሎ የገጠመው!

   በጦርነት ወቅትም ሆነ በድህረ ጦርነት በሲቪሎች ላይ የሚደርሱትን ሰብዓዊ ጥቃቶችን እቃወማለሁ፣ በተለይም በሴቶች ላይ የሚደርስ የትኛውም ዓይነት ጥቃት መወገዝ ያለበትና ጥቃት አድራሾቹንም ለፍርድ ማቅረብ አሌ የማይባል ነው። በዚህ ርዕሰ ጉዳይ በሰሜኑ ጦርነት ወቅትም ሆነ በድህረ ጦርነቱ ከአንዴም ሁለቴ የተቃውሞ ሐሳቤን አጋርቼአለሁ።
በአሁኑ ወቅት የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ በተፈጠረው ሰብዓዊ ጥቃቶች ዙሪያ የውጭ ሀገር መንግስታት ድምፃቸውን እያሰሙ ነው፣ ለዚህም ራሷን እንደ ዓለም አቀፍ ፖሊስ የምትቆጥረው አሜሪካ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳለች፤ አሁን ደግሞ በተለይም በሴቶች ዙሪያ የሚፈፀሙትን ጥቃቶች ተከትሎ የሰሜን አትላንቲክ ስምምነት ድርጅት (ኔቶ) በየትኛውም ሀገር ጣልቃ መግባት የሚችልበትን መንገድ እየጠራረገች ትገኛለች።
ሁሌም በተደጋጋሚ እንደሚባለውና የአሜሪካ መንግስትም ሰርክ እንደሚናገረው፣ የአሜሪካ የውጭ ፖሊሲዋ የተመሠረተው ገና ከመነሻው የአሜሪካን ጥቅም ከማስቀጠልና ከማስጠበቅ አኳያ ነው። ለዚህ ዋና አጀንዳዋ የአሜሪካ መነሻ ሰበቧ ግን ሌላ ሊሆን ይችላል። በእኔ ዕይታ በተለይም በጦርነት ወቅትም ሆነ በድህረ ጦርነት በሴቶች ላይ በሚፈፀሙ ወሲባዊ ጥቃቶች ዙሪያ አሜሪካ ራሷን ንፁሕ አድርጋ ሌሎችን ለመክሰስ ተፍ ተፍ የምትልበት ፍጥነት ትዝብት ላይ የሚጥላት ነው። ምክንያቱም በኢራቅና አፍጋኒስታን ከሴቶች ወሲባዊ ጥቃት ጋር በተገናኘ የአሜሪካ ወታደሮች የነበራቸው ስም እጅግ አሳፋሪና ዘግናኝ ነበር።
አሜሪካ በወታደሮች የሚፈፀሙ ጥቃቶችን በተመለከተ ሌሎችን ለመኮነን በአጭር ታጥቃ በተነሳች ቁጥር ትዝ የምለኝ የኢራቃዊቷ የ14 ዓመት ሕፃን “Abeer Qassim Hamza al-Janabi” የመደፈርና የመገደል ሰቆቃ ነው። ነገሩ እንደዚህ ነው፦ እ.ኤ.አ. በ2006 ዓ.ም. “Steven Dale Green” የተባለ የአሜሪካ ወታደር ከሌሎች ሦስት ባልደረቦቹ ጋር በመሆን ከባግዳድ 30 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ወደምትገኝ መንደር አብረው ከሄዱ በኋላ ከላይ የጠቀስኩላችሁ ሕፃን ልጅ ቤት ይገባሉ። እነዚህ የአሜሪካ አረመኔ ወታደሮች ወደ ቤት ከገቡ በኋላ የልጅቷን አባት እናትና ታናሽ እህቷን አስቀድመው ከገደሉአቸው በኋላ በተለይም “Steven Dale Green” የተረፈችውን የ14 ዓመት ሕፃን ከደፈራት በኋላ እሷንም ይገድለታል፤ ይህም አልበቃ ሲለው አስከሬኗን በእሳት አቃጠለ። “Steven Dale Green” ለፈፀመው ወንጀል የዕድሜ ልክ እስር ከተፈረደበት በኋላ እ.ኤ.አ.በ2009 ዓ.ም. ራሱን በታሰረበት ክፍል አጥፍቶ ተገኝቷል።
አሜሪካ የሴቶች ወሲባዊ ጥቃት ጠበቃ ሆና በምትቆምበት ቅፅበት ሁሉ ከኢራቃዊቷ “Abeer Qassim Hamza al-Janabi” በተጨማሪ ትዝ የምትለኝ አሜሪካዊቷ “Jessica” ነች። የአሜሪካ ወታደሮች የወሲባዊ ጥቃት ወንጀል ለገዛ ዜጎቻቸውም ጭምር የሚዳረስ ነው። “Jessica” የአሜሪካ ሚሊተሪ አባል ነች (ስሟ ለደህንነቷ ሲባል ተሰውሯል)፣ ነገር ግን በሚሊተሪ አለቆቿ ወሲባዊ ጥቃት ደርሶባታል። በአሜሪካ የሚሊተሪ ተቋም ከሶስት ሴቶች በአንዷ በአለቆቻቸው ወሲባዊ ጥቃቶች እንደሚደርሱ ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ (As many as one in three women in the US military are raped during their service, studies suggest [GALLO/GETTY])
ታዲያ ችግሩ በዚህ ብቻ የሚቆም አይደለም። ብዙዎቻችን አሜሪካ ፍትሕና ዲሞክራሲ የሰፈነባት ሀገር ስለሆነች ወሲባዊ ጥቃቱን በሚፈፅሙ የሚሊተሪ አባሎቿ ላይ ፈጣን እርምጃ እንደምትወስድ አድርገን እንቆጥር ይሆናል፣ ነገር ግን ጥቃቱ የደረሰባቸው የሚሉን ተቃራኒውን ነው። ይልቁን ወሲባዊ ጥቃቱ የደረሰባቸው ሴት ወታደሮች ጥቃቱን ሪፖርት በሚያደርጉበት ወቅት ፍትሕ ማጣታቸው እጅግ የሚዘገንን ነው። እስቲ ከላይ የጠቀስኳት የጥቃቱ ሰለባ የምትለውን ከራሷ አንደበት እንከታተል፦
“My experience reporting military sexual assault was worse than the actual assault.The command has so much power over a victim of sexual assault. They are your judge, jury, executioner and mayor: they own the law. As I saw in my case, they are able to crush you for reporting an assault.”
የአሜሪካ ወታደሮች በኢራቅና አፍጋኒስታን ቆይታቸው የፈፀሙአቸው ወሲባዊ ጥቃቶች ተቆጥረው የሚያልቁ አይደለም፣ አምኒስቲ ኢንተርናሽናል እና ሂዩማን ራይትስ ዎች ቆጥረው ይዝለቋቸው። በወቅቱ የቡሽ አስተዳደር ይህን ገመናውን ለመሸፈን የተቀረፁትን ምስሎችንም ሆነ ቪዲዮችን ለመሰወር የማያደርገው ጥረት አልነበረም። ታዲያ ይህ ሁሉ ግፍ ሲፈፀም የዛሬው ኔቶ የት ነበር? አሜሪካ ዓይኗ ውስጥ የተሰነቀረውን ግንድ የሚያክል ገመናዋን ደብቃ የሌሎችን ጉድፍ ለማየት የሞራል ድፍረቱን ያገኘችው ከወዴት ነው? ወሲባዊ ጥቃትን ማውገዝና መቃወም በአሜሪካኖቹ አያምርባቸውም፣ ይልቁን የተሻለ ሞራልና ሰብዕና ያለውን የሚሊተሪ ተቋማትን የገነቡ ሀገራት ቢቃወሙ መልካም ነበር። ስለዚህም አሜሪካ ከሁሉ አስቀድማ ኔቶን በራሷ ላይ ታስዘምት! ፅዳቱ ከራስ ይጀምር!


Saturday, 12 June 2021 13:11

የማለዳ እንጉርጉሮ

Written by

አንዳንዴ ደሞ ጎህ ቀዶ
አብሮኝ ያደረው ደወል፤ ከራስጌዬ
ተጠምዶ
ከወፎች ቀድሞ ሲያመጣልኝ “ነግቶብሃል”
የሚል መርዶ
ብትት ብዬ፤ ደንብሬ
ግማሽ ፊቴን ትራሴ ውስጥ ቀብሬ
“እኮ ዛሬም እንደወትሮ
ካውቶብስ ወደ ቢሮ
ከኬላ ወደ ኬላ
ዛሬም በግንባሬ ወዝ ልበላ
እሺ ከዚያስ በሁዋላ?”
እያልሁ ልቤን ስሞግት፤ መልሱን
አያመለክተኝ
ይሄን ያህል ነው የታከተኝ፤
ጉዞዬ፤ ካዋላጅ እቅፍ፤ እስከገናዦች አልጋ
ባራት አግር ተጀምሮ፤ ባራት ሰው ሸክም
እስኪዘጋ
መንገዱ መንገድ እየሳበ
ትንንሹ ዳገት ፤ለትልልቁ እያስረከበ
እንደ ሀረግ ስጎተት፤ እንደ ጥንቸል ስፈጥን
“ምን ሽልማት ታሰበልኝ? ይህ ልፋቴን
የሚመጥን
እያልሁኝ ሳውጠነጥን፤
አንዳንዴ ደሞ ሲመረኝ
እንደ ለማዳ ፈረስ፤ ሞትን በፉጨት
መጥራት ሲያምረኝ፥
ዛፉን የተቀማ አሞራ
በኮረንቲ ምሶሶ ላይ፥ ጎጆው ባዲስ መልክ
ሲሰራ
ማርዋን የተዘረፈች ንብ፤ በየአበባው
ስትሰማራ
አይና
እንዲህ እንዲህ እላለሁ፤ እርስ በራሴን
ሳጽናና፡ -
ሺህ ጊዜ ብትራቀቅ ፤ ቃላት መርጠህ
ብትገጥም
ከዚህ አሞራ አታንስም ከዚች ንብም
አትበልጥም
ተፈጥሮ ትግልን እንጂ፤ የድል ዋስትናን
አትሰጥም
ቻለው!

Page 2 of 3