Saturday, 13 August 2011 09:10

..ድንግል ማርያም.. ነኝ ባይዋሴት ክስ ሊመሰረትባት ነው

Written by  ሰላም ገረምው
Rate this item
(3 votes)
  • አንዲት የ19 ዓመት ወጣት ሞታለች
  • • እናቴ ከመቃብር በመላዕክት ታጅባ አርጋለች
  • • ሦስት ልጆቿን በመንፈስ ቅዱስ ወለድኳቸው ትላለች፤  ባሏም ተስማምቷል
  • • ህፃናትን ለሦስት ቀናት፤ አዋቂዎችን ለስምንት ቀናትስታፆም ነበር

..የሥላሴ መንፈስ በእኔ ላይ አድሯል፤ ከእግዚአብሔር የተላክሁ ማርያም ነኝ.. በሚል ድንኳን በመኖሪያ ቤቷ አካባቢ ተክላ ተከታዮች ስታፈራና እምነቷን ስታስፋፋ የነበረችው ሴት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተካሄደባት ነው፡፡

በአምቦ ከተማ ገላን በተባለ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ተወልዳ በ1994 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ የመጣችው ትዕግስት ብርሃኑ ከ1999 ዓ.ም. ጀምሮ ..ማርያም ነኝ.. በሚል ማሳሳቻ ተከታዮችን አፍርታ እንደ ነበር ከፖሊስ የተገኘ ማስረጃ ይጠቁማል፡፡
በዚሁ ዓመት የፋሲካ በዓል ሰሞን ..እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞቼ በሦስተኛው ቀን እነሳለሁ.. በማለት ዝግጅት የጀመረችው ትዕግስት፤ የስቅለት ዕለት የእሾህ አክሊልና የምትሰቀልበትን መስቀል አዘጋጅታ ጀርባዋን እንደ ተገረፈች ታውቋል፡፡ በመስቀሉ ላይ መሰቀሏን ያየ ግን አልተገኘም፡፡ በሦስተኛው ቀን ትዕግስት ከሞት ተነሳች ተብሎ ለአካባቢው ህዝብ እንደታየች ምንጮች ይናገራሉ፡፡ የት ደርሳ እንደመጣች የጠየቃት ስለመኖሩ ግን የታወቀ ነገር የለም፡፡ አብረዋት ይኖሩ የነበሩት አባቷ አቶ ብርሃኑ ድርጊቷን አጥብቀው ይቃወሙ እንደነበር የሚናገሩ ምንጮች፤ ጠጥተው ቤት ሲገቡ በጉዳዩ ይነታረኩ እንደነበር ያወሳሉ፡፡ አባቷ ግን የልጃቸውን መለኮታዊ ነኝ ባይነት ማስቆም አልቻሉም፡፡ ትዕግስት ይባሱኑ ..የሥላሴ መልዕክተኛ ድንግል ማርያም ነኝ.. ማለት ጀመረች ይላሉ - ምንጮች፡፡
በዚህ አድራጐቷ የአካባቢው ነዋሪ ሕዝብ ተቃውሞውን በማሰማት ከአካባቢው አባረራት፡፡ ትዕግስት በዚህ ጊዜ ወንጪ ገዳም እንደገባች የገለው ፖሊስ፤ ሀይለገብርኤል ከተባለው ተከታይዋ ሦስተኛ ልጇን እንደ ወለደች ይናገራል፡፡ ከወንድ ጋር ተገናኝታ እንደማታውቅ የምትናገረው ትዕግስት፤ ሦስቱንም ልጆቼን በመንፈስ ቅዱስ ነው የወለድኳቸው ባይ ናት፡፡ የመጀመሪያ ባለቤቷም ይሄንኑ ይመሰክራል - ከእሷ ጋር ስጋዊ ግንኙነት ፈጽሞ እንደማያውቅና ሁለት ልጆቿን በመንፈስ ቅዱስ እንደወለደቻቸው በመናገር፡፡
ትዕግስት በወንጪ ገዳም ሳለች የሥላሴ መልዕክተኛ ነኝ ማለቷን - ገፍታ ቀጠለችበት፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ሌላ ጉድ መከሰቱን የሚናገሩ ምንጮች፤ እናቷ ወ/ሮ ባይሴ ኡዊሳ (በክርስትና ስማቸው ወለተ ሥላሴ) ነሐሴ 25 2000 ዓ.ም. ከቀኑ 9 ሰዓት ሞተው እንደተገነዙ፣ ከዚያም የዚያኑ ዕለት ከምሽቱ 4 ሰዓት ከሞት ተነሱ ተብሎ እንደተወራ ይናገራሉ፡፡ እናት ከሞት የተነሱት ከሰማይ የተላኩትን መልዕክት ለማድረስ እንደሆነ ገልው ..ወ/ሮ ትዕግስት ወይም በክርስትና ስሟ ምስለ ፍቅር ኢየሱስን ስሟት ተብላችኋል.. ካሉ በኋላ በነጋታው ተመልሰው እንደሞቱና ነሐሴ 27 2000 ዓ.ም. የቀብራቸው ሥነ ሥርዓት እንደተፈመ ምንጮች ተናግረዋል፡፡ ከሁለት ቀን በኋላ ግን መቃብራቸው ተከፍቶ እንዳረጉ ነው ልጃቸው ትዕግስት የተናገረችው፡፡
ነሐሴ 29 2000 ዓ.ም. ሌሊት ላይ ነጐድጓድ መብረቅ ሰምቶ ከጥበቃ ክፍሉ እንደወጣ የሚናገረው የገዳሙ የጥበቃ ሠራተኛ፤ የትዕግስት እናት (በክርስትና ስማቸው ወለተ ሥላሴ) መቃብር ላይ መላዕክት እንዳየ ለፖሊስ ገልል፡፡ በእጁ አብርቶ ይዞት የነበረው ባትሪ መጥፋቱንና መብረቁ ገፍትሮ እንደጣለው ለፖሊስ የገለው የጥበቃ ሠራተኛ፤ በድንጋጤ ወደ ክፍሉ ተመልሶ እንደገባ ተናግሯል፡፡ ሲነጋጋ ሁኔታውን ለማጣራት ወደ መቃብሩ ሲሄድ የወለተ ሥላሴ መቃብር ለሁለት ተከፍሎና መሃሉ ተሰንጥቆ፣ የአስከሬን ሳጥኑ ባዶ ሆኖ ማየቱን በሰጠው ቃል ገልል፡፡
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ትዕግስት ..የዓለም ፍጻሜ ደርሷል፤ ንስሀ ግቡ.. እያለች መስበክ እንደጀመረች ምንጮች ይናገራሉ፡፡
ሴትዮዋ የተቀበሩበት ስፍራ ታጥሮ በሰዎች እየተጐበኘ እንደሆነ የጠቆመው ፖሊስ፤ ሁኔታው የማጣራት ሥራ እንደሚፈልግም ይናገራል፡፡
በረቡዕ ቀን በሬና በግ አርዳ ነዋሪዎች በፆም ቀን ሥጋ እንዲበሉ ማስገደዷ ከነዋሪው ጋር ለተፈጠረው ግጭት መንስኤ ሲሆን፤ የፆም ቀን ቢሆንም አብርሃም ቤትም በሬ ተጥሎ ለሰዎች የመገበው ሐምሌ ሰባት እንደሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፏል በማለት ሐምሌ 7 2002 ዓ.ም. ነዋሪው ሥጋ እንዲበላ፣ ካልበሉ ግን ምድር ተከፍታ እንደምትውጣቸው ታስፈራራ ነበር ተብሏል፡፡ ሥጋውን የበላ ይማራል በማለቷ ግማሹ ነዋሪ ቢበላም ግማሹ አልበላም እንዳለ የጠቆሙ ምንጮች፤ በዚህም ምክንያት ትዕግስት ከአካባቢው ለቅቃ አዲስ አበባ እንደገባች ይናገራሉ፡፡
አዲስ አበባ ከተከታዮቿ አንዷ በሆነችው ሃና ብሩክ በተባለች ግለሰብ መኖሪያ ቤት (ሳር ቤት አካባቢ) ያረፈችው ትዕግስት፤ ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 16 የሚደርሱ ህፃናትና ጐልማሶች አብረዋት ይኖሩ እንደነበር ታውቋል፡፡ ህፃናቱን ለልመና ተግባር ትጠቀምባቸው እንደነበር የጠቆመው ፖሊስ፤ እሷን ተከታይ እንደሆኑና ደረታቸውን በድንጋይ እንዲደልቁ ታደርጋቸው እንደነበር እንዳረጋገጠ አመልክቷል፡፡
አብዛኞቹ ተከታዮቿ ራሳቸውን የማያውቁና ከትክክለኛ አዕምሯቸው እንደተለዩ የሚናገረው ፖሊስ፤ የሴትዬዋ ድርጊት የተጋለጠው ህፃናቱ ለጐረቤት ..እመብርሃን ናት፤ ደሟን እየቀዳች የክርስቶስ ደም ነው እያለች ትሰጠናለች.. ብለው ከተናገሩ በኋላ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪ ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በመጠቆም ወ/ሮ ትዕግስት ብርሃኑ በቁጥጥር ስር እንደዋለች ገልል፡፡
በወቅቱ ፍተሻ አለማካሄዱን የጠቆመው ፖሊስ፤ ህፃናቱ የት እንዳሉ እንደማያውቅና ምርመራ ላይ መሆኑን የገለ ሲሆን ከሦስት ዓመት በፊት ከተከታዮቿ አንዷ የነበረችው የ19 ዓመቷ ትዕግስት ያለው ለስምንት ቀን ያለምግብ በመቆየቷ፤ ደረቷን በድንጋይ እንድትደልቅና የተበጠበጠ ምንነቱ ያልታወቀ ቅጠል እንድትጠጣ በመደረጉ ህይወቷ እንዳለፈ ገልል፡፡ የወጣቷን አስከሬን በማውጣት የአሟሟቷን ሁኔታ ለማጣራት ከህክምና ባለሙያዎች ጋር እየተመካከረ እንደሆነም ፖሊስ አክሎ ገልል፡፡
ከወ/ሮ ትዕግስት ብርሃኑ ጋር በተያያዘ ትዳራቸው የፈረሰ፣ ንብረታቸውን ያጡ ግለሰቦች እንዳሉም የፖሊስ መረጃ ይጠቁማል፡፡
አዲስ አበባ ቤቴል የተባለው ሰፈር ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ አለሚቱ ጉቱ በትዕግስት በደል እንደደረሰባት ቃሏን ለፖሊስ ሰጥታለች፡፡ ቤተሰቧቿ ወደ አምቦ ምዕራብ ሸዋ ዞን ጉደር ከተማ የወሰዷት፣ ወ/ሮ ትዕግስት በበል ከህመምሽ ትፈውስሻለች በሚል እንደሆነ የተናገረችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ከተጠመቀች በኋላ ከቲቢ ካንሰር ተፈውሰሻል ብለው ህዝብ ተሰብስቦ በቪዲዮ እንደተቀረች ለፖሊስ ገልጻለች፡፡
ከዚህ በኋላ ደግሞ ልጆቼንና ወርቄን ነጥቃኛለች የምትለው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ልጆችሽ የእኔ እንጂ ያንቺ አይደሉም መባሏን ትናገራለች፡፡ ..አንድ ቀን የትንሿን ልጄን ጉር ሳበጥር ለምን ነካሻት ተብዬ እስከምዝለፈለፍ ድረስ ተደብዳቤአለሁ.. ትላለች፡፡
ከእኔ የትም አታመልጡም ስለምትል ሁሉም ይፈራታል የምትለው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ተከታዮቿ ..እመቤታችን ናት አምልኳት.. እንደሚሉ ትናገራለች፡፡ ..በምስል ታመልካላችሁ፤ ይኸው በአካል መጥታለች አምልኳት.. ይሉናል ብላለች፡፡ በየቀኑ ፆም አለ፤ በቀን አንዴ ንፍሮ እንበላለን ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ፆሙ የአዋቂ ብቻ ሳይሆን ከስድስት ወር ጀምሮ ያለ ህፃንም እንዲፆም ይደረጋል - ለሦስት ቀን ጡት አይሰጠውም ብላለች፡፡
ወ/ሮ ትዕግስት ትምህርት ሃጢያት ነው በሚል አቋም ልጆች እንዳይማሩ እንደምታደርግ አለሚቱ ለፖሊስ ተናግራለች፡፡
የ12 ዓመት ልጄን ከዚህ እንግልት ለማዳን እንጥፋ ብዬው ነበር፤ እሱ ግን ፈርቶ እምቢ አለኝ የምተለው - አለሚቱ፤ የባሰው መከራ የመጣው ግን የ3 ዓመት ልጄ ለ3 ቀን ያለ እህል ውሃ ፆም ፀሎት መያዝ አለበት ስትላት እንደሆነ ተናግራለች፡፡ ትልቁ ልጄ አሻፈረኝ ስላለ ሌላ ሙከራ ባደርግ ይገድሉኛል ብዬ ትንሿን ልጇን ይዛ እንደጠፋች ተናግራለች፡፡ የወንድ ልጇ ነገር ያላስቻላት ወ/ሮ አለሚቱ፤ ተመልሳ ወደ አምቦ መሄዷን ትናገራለች፡፡
ሆኖም ሰው ሁሉ ስለጠላቸው ወደ አዲስ አበባ ሄደዋል ተብላ መመለሷንና ልጇን ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማግኘቷን ገልጻ ለሳምንት ያህል አብሯት ከቆየ በኋላ እንደጠፋ ገልጻለች፡፡ ፖሊስ ልጇን ለሁለተኛ ጊዜ አግኝቶ የሰጣት ቢሆንም ተስማምተው ሊኖሩ እንዳልቻሉ እናት ትናገራለች፡፡ እኔን እንደ እናቱ ሳይሆን እንደ ጠላት ነው የሚያየኝ ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ..ማርያምን ከሰሻት እኔ ካንቺ ጋር አልኖርም.. ይላት እንደነበር ገልጻለች፡፡ ልጄ ..እኛ ምድራዊ አይደለንም፤ ሰማያዊ ነን.. እያለ እሷ የምትናገረውን ሲደግም ነገሩ ከአቅሜ በላይ እንደሆነ ስለገባኝ ወደ እነሱ እንዳይመለስ በማረሚያ ቤት እንዲቆይ ተደርጓል የምትለው እናቱ፤ አሁን ትንሽ ቢሻሻልም፤ እሷን ግን እንደጠላት እንደሚመለከታት ትናገራለች፡፡ ልጄ ጤነኛ አይደለም ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ንብረቴን በሙሉ አጥቼአለሁ ከምንም በላይ የሚጽተኝ ግን ልጄን ማጣቴ ነው ብላለች - እንባዋን እያፈሰሰች፡፡ ወ/ሮ ትዕግስት አበራ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በእስር ላይ ስትሆን ጉዳይዋ ወደ ፍርድ ቤት ተልኮ በጊዜ ቀጠሮ ላይ እንደሆነ ታውቋል፡፡ወ/ሮ ትዕግስት ለፖሊስ በሰጠችው ቃል ..የሥላሴ መልዕክተኛ ነኝ እኔ ከወንድ ጋር አልተኛሁም፤ ተርፌሳም ማርያም ዮሴፍን ይጠብቃት እንደነበር ጠባቂዬ ነው፤ ሦስት ልጆች ቢኖሩኝም በመንፈስ ነው የወለድኳቸው፤ ይህንን ሁሉ ያደረኩት ሥላሴዎች አዘውኝ ነው፤ አላጠፋሁም.. ብላለች፡፡

 

Read 10824 times Last modified on Saturday, 13 August 2011 15:30