ፑስ በሽሬክ ፊልሞች ከ2ኛው ክፍል ጀምሮ እየሰራ ያለና የመስከቲርስ ባህርይ ያለው ጀብደኛ ገፀባህርይ ነው፡፡ ሰሞኑን በሰሜን አሜሪካ 35 ሚሊዮን ዶላር ያስገባው “ፑስ ኢን ዘቡትስ” ቦክስ ኦፊስን የመራ የመጀመርያው የአኒሜሽን ፊልም ሆኗል፡፡
ሌላው የድሪምዎርክስ ፊልም በስቲቨን ስፒልበርግ የተሰራው “ዘ አድቬንቸርስ ኦፍ ቲንቲን፡ ዘ ሴክሪት ኦፍ ዩኒኮርን” ሲሆን ባለፈው ሰሞን በመላውዓለም ሲታይ 56 ሚሊዮን ዶላር አስገብቶ የቦክስኦፊስን የሳምንታዊ ገቢ ደረጃ በበላይነት መርቷል፡፡ ስቴቨን ስፒልበርግ ዘንድሮ በሰበሰበው 107 ሚሊዮን ዶላር
ከፍተኛ ገቢ ያገኘ የሆሊውድ ዲያሬክተር ሆኗል፡፡ በ175 ሚሊዮን ዶላር በጀት የተሰራው ፊልሙ ለፕሮሞሽንና ለሌሎች 100 ሚሊዮን ዶላር የወጣበት ሲሆን ገቢው 500 ሚሊዮን ዶላር እንደሚደርስ ተገምቷል፡፡