በአይዳ ታደሰ ተፅፎና ተዘጋጅቶ ራሷና ባለቤቷ ያቀረቡት “ቃልና ቀለም” የ102 ደቂቃ ፊልም ለሕዝብ እይታ ሊበቃ ነው፡፡ ፊልሙ ባለፈው እሁድ በኢትዮጵያ ሆቴል በይፋ ተመርቋል፡፡ ከመጪው አርብ ጀምሮ በመንግሥት ሲኒማ ቤቶች መታየት የሚጀምረው ፊልም በእሁዱ ምረቃ ከሆቴሉ ሌላ በአጐና ሰራዊት፣ በሴባስቶፖል፣ በዓለም፣ በካፍደም፣ በሃበሻና በጂም ሲኒማዎችና በዓለም ገና ከተማ ታይቷል፡፡ በፊልሙ ላይ አበባው መላኩ፣ ወለላ አሰፋ፣ እልፍነሽ ሰይፉ፣ ህልዳና ተሾመና ቸርነት ወልደገብርኤል ይተውኑበታል፡፡