Thursday, 27 August 2026 10:49

የዓለም ሪከርድ የሰበሩት ጀግኖቻችን ዮሚፍ እና ፎቴን አዲስ አበባ ገቡ

Written by 
Rate this item
(0 votes)
በአርጀንቲና የግማሽ ማራቶን ውድድር አዲስ የዓለም ሪከርድ ያስመዘገበው ዮሚፍ ቀጄልቻ እና የቦታውን ሪከርድ አሻሽላ ያሸነፈችው ፎቴን ተስፋይ አዲስ አበባ ገብተዋል። በውድድሩ ዮሚፍ 56:51 በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለም ሪከርድ ሲሰብር፣ ፎቴን ደግሞ 1:03:57 በመግባት አንደኛ ወጥታለች።
ለእነዚህ አትሌቶች በቦሌ አየር መንገድ በፌዴራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ አጃቢነት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በስነ-ስርዓቱም ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች፣ አሰልጣኞች እና የአትሌቶቹ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Read 366 times