በአርጀንቲና የግማሽ ማራቶን ውድድር አዲስ የዓለም ሪከርድ ያስመዘገበው ዮሚፍ ቀጄልቻ እና የቦታውን ሪከርድ አሻሽላ ያሸነፈችው ፎቴን ተስፋይ አዲስ አበባ ገብተዋል። በውድድሩ ዮሚፍ 56:51 በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለም ሪከርድ ሲሰብር፣ ፎቴን ደግሞ 1:03:57 በመግባት አንደኛ ወጥታለች።
ለእነዚህ አትሌቶች በቦሌ አየር መንገድ በፌዴራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ አጃቢነት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በስነ-ስርዓቱም ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች፣ አሰልጣኞች እና የአትሌቶቹ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

