Wednesday, 05 August 2026 17:22

ሪያል ማድሪድ ያን ዶዮማንዴን ለማስፈረም ከስምምነት ደረሰ

Written by 
Rate this item
(0 votes)
ሪያል ማድሪድ ኮትዲቯራዊውን አማካይ ያን ዲዮማንዴ ከአርቢ ላይብዢግ ለማስፈረም መስማማቱን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል።
በአሁኑ ሰዓት ተጫዋቹ በኦስትሪያ የቅድመ ውድድር ዝግጅት እያደረገ ሲሆን በቀጣይ ሰዓታት ለጤና ምርመራ ወደ ማድሪድ የሚያቀና ይሆናል።
ሪያል ማድሪድ ለጀርመኑ አርቢ ላይብዢግ በተከታታይ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ ቢሆንም፤ በመጨረሻ ያቀረበው 125 ሚሊዮን ዩሮ ጥቅማጥቅሙ 140 ሚሊዮን ዩሮ የሚደርስ ዋጋ ተቀባይነት አግኝቷል።
ያን ዲዮማንዴ ላይብዢግን ከተቀላቀለ በኋላ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ባደረጋቸው 36 ጨዋታዎች 13 ግቦችን አስቆጥሮ፣ 10 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል።
Read 440 times