Tuesday, 04 August 2026 14:06

ተንቀሳቃሽ ቤተ-መጽሐፍት፡ የስልክ ሱስን የሰበረው ባለታክሲ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ወጣት ሰሎሞን አማረ (በማርኬቲንግ ማኔጅመንት የተመረቀ) አዲስ አበባ ውስጥ የሚያበራራትን ሜትር ታክሲ ወደ "ተንቀሳቃሽ ቤተ-መጽሐፍት" በመቀየር አዲስ ፈጠራን አስተዋውቋል።

  •  ወጣቱ ከስልክና ማህበራዊ ሚዲያ ሱስ ተላቆ ወደ ንባብ ባህል እንዲመለስ ማስቻል፤ የትራፊክ መጨናነቅን ለንባብ አጋጣሚ መጠቀም።

  •  ተሳፋሪዎች በጉዞ ወቅት መጽሐፍትን ያነባሉ፤ ከተመቻቸውም እዚያው ገዝተው ይሄዳሉ።

  •  ከትራንስፖርት አገልግሎት ጎን ለጎን መጽሐፍትን በመሸጥ ድርብ ገቢ ያገኛል፤ በቲክቶክ (Sol Books) ገጹም መጽሐፍትን ያሰተዋውቃል።

  •  ሌሎች የትራንስፖርት አቅራቢዎችም ይህን አርአያነት ያለው ተግባር በመከተል ታክሲዎችን የዕውቀት ማዕከል እንዲያደርጉ ጥሪ ያቀርባል።

Read 2604 times