በፋብሪካ ላይ ፋብሪካ እየከፈተ የመጣ ስንት የሀገራችን ኩባንያ ትጠራለህ? ብሎ ይጠይቃል ኃይሌ።
ኃይሌ የብዙ ስኬታማ ቢዝነስ ተቋማት መሥራችና ባለቤት ነው። ድንበር ተሻጋሪው ታላቁ ሩጫ፣ በደቡብ ኮርያዎች የተደነቀው የሃዩንዳይ መኪና መገጣጠሚያ፣ በአገልግሎት አሰጣጡ የተደነቀው የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት፣ የቡና እና ማር ኤክስፖርት፣ ትምህርት ቤት፣ ...
ዋው! ኃይሌ ቢዝነሱን እያሯሯጠው ነው።
"እኔም ኃይሌ ነኝ!" የሚሉ የባለቤትነት ስሜት ያላቸው በርካታ ሠራተኞችን አፍርቷል።
ኃይሌ ከሩጫ ይልቅ የቢዝነስ ውድድር ከባድ መሆኑን ተናግሯል።
ከበርካታ አስደሳች ንግግሮቹ መካከል ያለነው መሬትን እንደ ትልቅ ሀብት በሚያይ የፊውዳል ስርዓተ- ማህበር ውስጥ ይመስለኛል ያለው ሊሰመርበት የሚገባው አባባል ነው።
"እኛ መሬት አጥረን ስንፋጅ ሌላው አየሩን ይዞታል" ያለው የኪዮሳኪ አባባል ኃይሌ ጥሩ አማካሪ እንዳለው አስረጂ ነው።
በርታ ኃይሌ!
Get Toughe zer-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

