በአንድ ሳምንት አምስት ቴአትሮችን እየሰራ ስላለው ብርቱው ተዋናይ ትእዛዙ ታዬ ጥቂት መረጃ አድርሼ ነበር። እሱን ተንተርሶ ተጨማሪ ሀሳብ አርቲስት መርዕድ ተስፋዬ አከለበት። እንዲህ ሲል፦
***
በጣም የሚገርመኝ የትዕዛዙ ልዩ ችሎታ ደግሞ የሌሎች ተዋንያንን ገፀ ባህሪ በአጭር ጊዜ አጥንቶ ተክቶ በመስራት ብዙ ቴአትሮችን ከመዘጋት ታድጓል!!!.....ቁጠሩ እንግዲህ....
ለምሳሌ ለመጥቀስ ያህል:-
1."ህንደኬ" ላይ....ተዋናይ ደረጄ ደመቀን ተክቶ
ሰርቷል፡፡
2."ሶስተኛው ችሎት" ላይ....ተዋናይ ፈለቀ የማር ውሀ አበበ እና ተዋናይ ሱራፌል ተካ የሚሰሩትን ገፀ ባህሪ ተክቶ ሰርቷል፡፡
3."አሉ" ቴአትር ላይ ተዋናይ ሳሙኤል ተስፋዬን
ተክቶ ሰርቷል፡፡
4."መንታ መንገድ" ላይ ተዋናይ ተስፋዬ ገ/ሐናን
ተክቶ ሰርቷል፡፡
5.አሁን በቅርቡ ደግሞ "12ቱ እንግዶች" ላይ ተዋናይ ዳንኤል አሸናፊን ተክቶ ሰርቷል!!!......ይሔኔ እኮ ያልጠቀስኩትም ይኖራል!!!.......ለማንኛውም ትዜ ከትወናውም ውጪ ቴአትርን በብዙ ነገር እየደገፈ ያለ ጎበዝ እና ልበ ቅን ባለሙያ ነው!!!
***
ባለሙያ በቅንነት እንዲህ ማድነቅ ሲችል ደስ ይላል። እናመሰግናለን መርዕድ።
ውድነህ ክፍሌ-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና

