የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በማሊ ከሚንቀሳቀሰውና ከአልቃኢዳ ጋር ግንኙነት ካለው አማፂ ቡድን ጋር በተያያዘ ወታደራዊ ጥቃት ለማድረስ እያሰበ መሆኑን የአሜሪካ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
ይህ ውሳኔ ከጸደቀ ማሊ በትራምፕ ሁለተኛ የፕሬዝዳንትነት ዘመን አሜሪካ ወታደራዊ ጥቃት የፈጸመችባት 8ኛዋ ሀገር ትሆናለች፤ ይህም አሜሪካ ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ የምታደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ይበልጥ የሚያሰፋው ይሆናል። እስካሁን ድረስ የተላለፈ የመጨረሻ ውሳኔ የሌለ ሲሆን በጉዳዩ ላይ በአስተዳደሩ ውስጥ ውይይቶች አሁንም ቀጥለዋል።

