ቡርኪና ፋሶ የአገር ውስጥ የእንስሳት አቅርቦትን ለማሟላት ስትል ማንኛውንም ዓይነት የቀንድ ከብትና እንስሳት ወደ ውጭ መላክን በጊዜያዊነት አግዳለች። ባለሥልጣናቱ እንደገለጹት፥ ውሳኔው በአገር ውስጥ ያለውን የአቅርቦት እጥረት ለመቅረፍና የዋጋ መናርን ለማረጋጋት ያለመ ነው።
ይህ እርምጃ በብዙ የአገሪቱ ዜጎችና ተጠቃሚዎች ዘንድ አዎንታዊ ምላሽ ያገኘ ቢሆንም፥ የእንስሳት ነጋዴዎች ግን እገዳው በንግድ ሥራቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰባቸውና ከአካባቢያዊ ንግድ ያገኙት የነበረውን ዋና የገቢ ምንጭ እንደገደበባቸው በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።

