Wednesday, 27 May 2026 11:34

ቡርኪና ፋሶ የቀንድ ከብት ወደ ውጭ መላክን በጊዜያዊነት አገደች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)
ቡርኪና ፋሶ የአገር ውስጥ የእንስሳት አቅርቦትን ለማሟላት ስትል ማንኛውንም ዓይነት የቀንድ ከብትና እንስሳት ወደ ውጭ መላክን በጊዜያዊነት አግዳለች። ባለሥልጣናቱ እንደገለጹት፥ ውሳኔው በአገር ውስጥ ያለውን የአቅርቦት እጥረት ለመቅረፍና የዋጋ መናርን ለማረጋጋት ያለመ ነው።
ይህ እርምጃ በብዙ የአገሪቱ ዜጎችና ተጠቃሚዎች ዘንድ አዎንታዊ ምላሽ ያገኘ ቢሆንም፥ የእንስሳት ነጋዴዎች ግን እገዳው በንግድ ሥራቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰባቸውና ከአካባቢያዊ ንግድ ያገኙት የነበረውን ዋና የገቢ ምንጭ እንደገደበባቸው በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።
Read 10195 times