ይህ እንዲሳካ በተለያዩ መንገዶች ላገዛችሁኝ፤ ረቂቁን በማንበብ ላበረታታችሁኝ፣ በ”የዳግማዊ ገፆች” ተስፋ ጥላችሁ በአዲስ ስራ እንድመጣ ናፍቃችሁ የገፋፋችሁኝ …….. ሁሉ ምስጋናችሁን ውሠዱ!
በ“የጨቀየ ጥለት” ፍቅር፣ ፖለቲካ፣ ማሕበረሠብ፣ ስነልቡና፣ ጥበብ፣ እውነት፣ ፍልስፍና ……. ብዙ ብዙ ርዕሠጉዳዮችን አንስቼበታለሁ፡፡
ሐሳብ ጠጥሮ እንዳያነቅፋችሁ፣ ጨዋታ ላልቶ እንዳያሠለቻችሁ፣ እናንተንም እኔንም እንዲመጥን እጅግ ብዙ ደክሜበታለሁ!
ጥቅምት 24 ድርብ በዓላችን ይሆናል!

