ሼህ መሐመድ የምንጊዜም የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ናቸው! በኢትዮጵያ ታላላቆቹ ሀገራዊ ሥራዎችና የደግነት ምግባራት ውስጥ የእሳቸው ለጋስ እጅ ያላረፈበትን ነገር መጥቀስ ይከብዳል። ሲለግሱና ዕንባ ሲያብሱ፣ ቃል እስኪቸግራቸው ስለኢትዮጵያ የልባቸውን አውጥተው ሲናገሩ፣ ከአጠገባቸው ሆኜ የማድመጥን ብዙ ዕድል አግኝቻለሁ።
ከብዙ አመታት በኋላ በሚድሮክ የቤተሰብ ቀን ላይ በቀረበው ቪዲዮ የተቀረፀውን ድምጻቸውን በመስማቴና ምስላቸውን ማየት በመቻሌ እጅግ በጣም ተደስቻለሁ። ወደሚወዷት፣ በልባቸው በሚያስቡላትና ከአንደበታቸው ወደማትጠፋው ሀገራቸው በጤና ተመልሰው፣ የልጅ ከሚመስለው ፈገግታቸው ጋር በአካለ ሥጋ እናያቸው ዘንድ እንፀልያለን!
ረዥም ዕድሜና ሙሉ ጤናን እመኝልዎታለሁ!
-ከያኒና ጋዜጠኛ ተስፋዬ ማሞ -

