የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን፣ ዘለንስኪን ወደ ሞስኮ የጋበዙት ለውይይት እንጂ እጅ እንዲሰጥ አይደለም ሲል ክሬምሊን ባወጣው መግለጫ አመለከተ፡፡
“ይህ ነው የፑቲን ሀሳብ ነው” ያሉት ዲሚትሪ ፔስኮቭ፤ ዘለንስኪ ሃሳቡን ውድቅ እንዳደረገ ተመልክተናል ብለዋል።
ዘለንስኪ የሰላም ድርድር ለማድረግ ወደ ሞስኮ መምጣት እንደሚችሉ ፑቲን በቤጂንግ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ መናገራቸው ይታወሳል፡፡
የፑቲንን ግብዣ ተከትሎ ዩክሬን ፤“በሞስኮ የሚደረግ ስብሰባ ተቀባይነት የለውም” ስትል ጥሪውን ውድቅ አድርጋለች፡፡
"ፑቲን ዘለንስኪን ወደ ሞስኮ የጋበዙት እጅ እንዲሰጥ አይደለም" ብሏል ክሬምሊን በመግለጫው፡፡


