Friday, 05 September 2025 16:19

"ፑቲን ዘለንስኪን ወደ ሞስኮ የጋበዙት እጅ እንዲሰጥ አይደለም"

Written by 
Rate this item
(0 votes)
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን፣ ዘለንስኪን ወደ ሞስኮ የጋበዙት ለውይይት እንጂ እጅ እንዲሰጥ አይደለም ሲል ክሬምሊን ባወጣው መግለጫ አመለከተ፡፡
“ይህ ነው የፑቲን ሀሳብ ነው” ያሉት ዲሚትሪ ፔስኮቭ፤ ዘለንስኪ ሃሳቡን ውድቅ እንዳደረገ ተመልክተናል ብለዋል።
ዘለንስኪ የሰላም ድርድር ለማድረግ ወደ ሞስኮ መምጣት እንደሚችሉ ፑቲን በቤጂንግ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ መናገራቸው ይታወሳል፡፡
የፑቲንን ግብዣ ተከትሎ ዩክሬን ፤“በሞስኮ የሚደረግ ስብሰባ ተቀባይነት የለውም” ስትል ጥሪውን ውድቅ አድርጋለች፡፡
"ፑቲን ዘለንስኪን ወደ ሞስኮ የጋበዙት እጅ እንዲሰጥ አይደለም" ብሏል ክሬምሊን በመግለጫው፡፡
May be an image of 2 people and text that says 'SPUTNIK'
 
 
 
 
Read 383 times