ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት ከ50 ሚ. በላይ የሃገር ውስጥ ጎብኚዎችን እንደምትጠብቅ የቱሪዝም ሚኒስቴር ገለጸ፡፡
ዘርፉ ለኢኮኖሚው አቅም መሆን እንዲችል ሁሉንም በማሳተፍ እንደሚሠራ፤ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሣ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ውይይት ሲካሄድ መናገራቸው ተዘግቧል፡፡
የ2017 በጀት ዓመት 1.3 ሚሊዮን የውጭ ሀገር ቱሪስቶች ሀገሪቱን እንደጎበኙ የተጠቆመ ሲሆን፤ ከ48 ሚሊዮን በላይ የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች ጉብኝት አድርገዋል ተብሏል፡፡
በተጨማሪም፣ 228 ኢንቨስተሮችን ወደ ዘርፉ መሳብ እንደተቻለና በ “ቪዚት ኢትዮጵያ” የዲጂታል አሠራር የቱሪዝም ሀብትን የማስተዋወቅ ሥራ መከናወኑን ስፑትኒክ የሚኒስቴር መ/ቤቱን መረጃ ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
በበጀት ዓመቱ የሰላም ሁኔታና የሎጀስቲክስ ጉድለት እንዲሁም የሆቴል ደረጃ ምደባ በወቅቱ አለመቅረቡ በተግዳሮነት ተጠቅሰዋል፡፡


See insights and ads
Boost post
All reactions:
1919
