የሰሜን ኮሪያ ፕሬዚዳንት ከፑቲን ጋር በቤጂንግ ባደረጉት ውይይት፣" ሩሲያን ለመርዳት ሁሉንም ነገር እናደርጋለን፤ ይሄንንም እንደ ወንድማዊ ግዴታ እንቆጥረዋለን።" ብለዋል።
ኪም ጆንግ ኡን፣ የሩሲያና የሰሜን ኮሪያ ግንኙነት በሁሉም መልኩ እየተጠናከረ ነው ሲሉም ጨምረው ገልፀዋል።
ፑቲን በበኩላቸው፤ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች በሩሲያ ኩርስክ ግዛት ከዩክሬን ጋር በተደረገው ፍልሚያ በጀግንነት ተዋግተዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ለዚህም ለመላው የሰሜን ኮሪያ ሕዝብ ምሥጋና አቅርበዋል፡፡

