የዩክሬን ስምምነት ከተቀመጠው የአሥር ቀን ቀነ ገደብ በፊት ካልተደረሰ፤ ዋሽንግተን በሩሲያ ላይ ማዕቀብ እንደምትጥል ትራምፕ ለአሜሪካ ሚዲያ በሰጡት ቃለ ምልልስ ደግመው ተናግረዋል፡፡
ባለፉት ጥቂት ወራት ስለፑቲን ያላቸው ሐሳብ ተቀየሮ እንደሆነ የተጠየቁት ትራምፕ፣ "የሩሲያው ፕሬዚዳንት ጽኑ ሰው መሆናቸው የታወቀ ነው" ብለዋል።
ፕሬዚዳንቱ ለዩክሬን የሰላም ስምምነት አዲስ ቀነ ገደብ ማክሰኞ ይፋ አድርገዋል፡፡ ቀነ ገደቡ እንዳበቃ ሩሲያን በሁለተኛ ደረጃ ታሪፎች አስፈራርተዋል፡፡
ሆኖም ክሬምሊን "የሩሲያ ኢኮኖሚ ማዕቀብ የሚቋቋምበት አንዳች የመከላከል አቅም አዳብሯል" ብሏል፡፡
(sputnik)
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

