Saturday, 19 October 2024 12:41

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(10 votes)

እንዲያው ማሳዘኑ!
   ተበዳዩ ጨቋኝ. . .
   በዳዩ ተጨቋኝ. . .
 የተገላቢጦሽ ኾኗል ነገሩማ፤
   ፍትሕ ተዘንብላ
   ስትወድቅ በአፍጢሟ
 የድረሱልኝ ጥሪ ሩቅ ስታሰማ፤
ሮሮዋን ሰምቶ - አዝኖ ቀረበና
 ሊያነሳት ቢሞክር ተበዳዩ ጨቋኝ፤
 አልተቻለው ከቶ ቢለፋ ቢሞክር
 ከወደቀችበት ሽቅብ ቀና እንድትል
 ማድረጉ ተሳነው የቱን ያህል ቢጥር።
 ሞት አፋፍ ላይ ኾና ጣርን ስታጣጥር
 ጩኸትና ዋይታ አብዝቶ ተሰማ
ከተበዳይ ጨቋኞች ከምስኪኖች ዘንዳ።
 የኩኔዎች ባልተቤት በዳዩ ተጨቋኝ
 ፍትሕን ፈላጊ እሷኑኑ አዳኝ
 መስሎ ቀረበና. . .
 በደስታ - በተድላ - በአሸናፊነት ስሜት
 በወኔም ተሞላ በድል አድራጊነት!
 ዳግም ላታበራ የወደቀችውን ገድሎ ቀበረና
 ደግሞም ላዩ አዝኖ ብሎም ጆሮ ዳባ
 ዓይኑን በጨው አጥቦ የአዞ እንባ እያነባ
 ቀርቦም ተጭቁኖች፣ ተገፊዎች ዘንዳ
 በመርዛም ምላሱ መስሎም ለዘብተኛ
 ይነዛ ጀመረ የአይዟችሁ ጥሪ
 በዳዩ ተጨቋኝ የፍትሕ ቀባሪ!
 እንዲያው ማሳዘኑ. . . .
 (በዒምራን ዑመር

Read 1094 times