Saturday, 03 June 2023 20:02

“የቀን ፍርጃ” መፅሐፍ ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 በደራሲ ሰለሞን ደረሰ አመኑ የተሰናዳውና ለ67 ዓመታት በደራሲው ህሊና ውስጥ ሲጉላላ ነበር የተባለለት “የቀን ፍርጃ” መጽሐፍ ነገ ሀምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ በብሄራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መፃሕፍት ኤጀንሲ (ወመዘክር) አዳራሽ ይመረቃል።
መፅሀፉ ከ1940ዎቹ እስከ ኢትዮጵያ ሚሊኒየም 2000 ዓ.ም ድረስ ያሉ የደራሲው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረቱ ታሪኮችና ለ67 ዓመት ለደራሲው ምጥ ሆነው የቆዩ ድንቅ የሀገራችን ቤተሰባዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችና  ድብቅ ፍቅር ያመጣው መዘዝን ጨምሮ በርካታ አስደናቂ ታሪኮችን በውስጡ ይዟል።
ደራሲ ሰለሞን ደረሰ አመኑ ኑሮአቸውን በሀገረ አሜሪካ ካደረጉ የሰነበቱ ሲሆን ይህ መፅሐፋቸው ከ67 ዓመት በኋላ ለንባብ በቅቶ ለትውልድ መማሪያ ይሆን ዘንድ ሰሞኑን ወደ ሀገራቸው መግባታቸውም ተጠቁሟል።
በዕለቱ ከመፅሐፉ ጎን ለጎን የጥንቷ አዲስ አበባ ምን ትመስል እንደነበር የሚያሳይ የፎቶ ግራፍ አውደ-ርዕይ፣ የመጽሐፍ ዳሰሳ፣ ከመጽሐፉ የተወሰዱ ታሪኮች ለታዳሚ የሚቀርቡበት መርሃ ግብርና ሌሎችም ጉዳዮች ይከናወናሉ ተብሏል። በዕለቱ ደራሲያን፣ ምሁራን፣ የስነ-ጽሁፍ አፍቃሪዎች የደራሲው ቤተሰቦችና ጥሪ የተደረገላው እንግዶች ይታደማሉ ተብሏል።



Read 869 times