Saturday, 06 May 2023 18:19

ለቻይና የጠቀሙ፣ያበለፀጉና ያፈረጠሙ ሦስት መርሆች ለኢትዮጵያም ይበጃሉ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

በአማራ ክልል በከባድ መሳሪያ በታገዘ ጥቃት ንፁሃን መገደላቸውን ኢሰመኮ አስታወቀ

  ሁሉም ወገኖች ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ጥሪ አቅርቧል


  በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በመከላከያ ሰራዊትና በታጣቂዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት በሰው ህይወት ላይ ጉዳት መድረሱን የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ መንግስት እያካሄደ ያለውን የህግ ማስከበር ዘመቻ በሰብአዊ መብቶች ላይ ያለውን ተፅዕኖ በቅርበት እየተከታተልኩ ነው ብሏል፡፡
ከህግ ማስከበሩ ዘመቻ ጋር በሰሜን ጎንደር፣ በሰሜን ወሎና በሰሜን ሸዋ ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች በመከላከያ ሰራዊትና በታጣቂዎች መካከል ግጭት መካሄዱን ያመለከተው የኮሚሽኑ መግለጫ፤ በተለይም በሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋ ሮቢት፣ አንፆኪያ ገምዛ፣ ማጀቴና አርማኒያ አካባቢ በከባድ መሳሪያ ጭምር የታገዘ ጥቃት መፈፀሙንና በዚህም ሳቢያ በሲቪል ሰዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን አመልክቷል፡፡
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ የሚወስደው መንገድ በተለያዩ ጊዜያት መዘጋቱን የጠቆመው የኮሚሽኑ መግለጫ፤ በክልሉ ያሉ የተወሰኑ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት የክልል ልዩ ሃይሎችን እንደገና የማዋቀሩን ውሳኔ በመቃወም የተካሄዱ ሰልፎችን መርተዋል አስተባብረዋል የተባሉ ወጣቶችና ከፋኖ ቡድን ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎች ለእስር መዳረጋቸውን አመልክቷል፡፡
ባለፉት ሁለት ዓመታት በሰሜን ኢትዮጵያ የተካሄደው ጦርነት ለሲቪል ሰዎች ላይ መጠነ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰትና ጉዳት አድርሷል ያለው ኮሚሽኑ፤ ሁሉም የሚመለከታቸው ወገኖች ችግሩን በሰላማዊ መንገድና በውይይት እንዲፈቱና ግጭቶችን ከሚያባብሱ ድርጊቶችና ንግግሮች እንዲቆጠቡ ጥሪ አድርጓል፡፡
በአካባቢዎቹ ስለተፈፀሙ ጥቃቶችና ስላደረሱት ጉዳቶች መንግስት አስፈላጊውን ምርመራ በማድረግ ተጠያቂነትን እንዲያረጋግጥና በማንኛውም ሁኔታ የሚፈፀሙ እስራቶች ህግን መሰረት ያደረጉና ከአድልዎ ነፃ መሆናቸውን እንዲያረጋግጥ ኢሰመኮ ጥሪ አቅርቧል፡፡


Read 1966 times