Saturday, 08 April 2023 19:44

ሥራ ፈጣሪዎቹ ወንድማማቾች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 “ሰው ከተሰማራ እንደ የስሜቱ ከዋለበት ስፍራ አይቀርም ማፍራቱ” ይባላል። ሁለቱ ወንድማማቾች ፍፁም ዘካሪያስ እና ነብዩ ዘካሪያስ፣ ለዚህ አባባል ሁነኛ ምሳሌዎች ናቸው።
 ፍፁም ዘካሪያስ፤ በአዲስ አበባ ከተማ፣ ታህሳስ 26 ቀን 1979 ዓ.ም ተወለደ። ቅድመ መደበኛ ትምህርቱን በስድስት አመቱ፣ በአቃቂ ክፍለ ከተማ ከሚገኘው የሠ/ማ/ጉ የአፀደ ህፃናት ት/ቤት ካጠናቀቀ በኋላ፣ መደበኛ ትምህርቱን በአቃቂ አድቬንቲስት ሚስዮን ት/ቤት  ከአንደኛ እስከ አስረኛ ክፍል ተምሯል። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱንም  በFTS ት/ቤት በከፍተኛ ውጤት አጠናቆል። ከዚያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ  በትያትሪካል አርት የትምህርት  ክፍል በመግባት፣ ትምህርቱን መከታተል ጀመረ።
ሆኖም በንግድ ስራ ላይ ባለውጥልቅ ፍላጎትና ጉጉት ምክያንት፣. የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን በማቋረጥ በወላጆቹ  የሆቴል ንግድ ሥራ ላይ ተሰማራ። በኋላም ስለ ንግድ ስራ አዳዲስ  ሃሳቦችንና የዘመኑን በቴክኖሎጂ የታገዘ የንግድ ስራ ክህሎት ለመቅሰም በማሰብ ወደ አውሮፓ ተጓዘ፡፡ በኔዘርላንድ፣ ቤልጅየም ፣ ኒውዘርላንድ ፣ ጀርመንና ሌሎች አገራትም በመዘዋወር  ሁኔታዎችን ሲያጠና ቆይቶ፣ የተለያዩ መረጃዎችንና የቢዝነስ ሃሳቦችን በመያዝ ወደ አገሩ ተመለሰ።
ወንድሙ ነብዩ ዘካሪያስም፣ በአዲስ አበባ፣ በ1983 ዓ.ም ጳጉሜ 4 ቀን ተወለደ። የቅድመ መደበኛ ትምህርቱን የአሁኑ አቃቂ ክፍለ ከተማ በሚገኘው የሠ/ማ/ጉ የአፀደ ህፃናት ትምህርቱን አጠናቀቀ። የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአፄ ቴዎድሮስ ፣ ሌስፔራንስ ት/ቤት፣ ቃሊቲ በሚገኘው ብሔራዊ ትምህርት ቤት ከተከታተለ በኋላ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ሳሪስ በሚገኘው አይጎዳ  (school of Igoda ) ት/ትቤት በ2002 ዓ.ም አጠናቋል፡፡  የከፍተኛ ደረጃ ትምህርቱን ም፣በመቀሌ ዩኒቨርስቲ ማርኬቲንግ ማኔጅመንት በመማር በ2006 ዓ.ም የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀብሏል።ከዚያም  በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በንብረት ክፍል ውስጥ ተቀጥሮ ለአጭር ግዜ ካገለገለ በኋላ፣ ከወንድሙ ፍፁም ዘካሪያስ ጋር በመሆን ወደ ንግዱ ዓለም ተቀላቅሏል።
ወደ ንግዱ ዓለም የተሳቡት ገና በልጅነታቸው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በሚገኘው በእናታቸው ስም በተሰየመው ሮሚ ሆቴል ንግዱን መለማመዳቸውን ይናገራሉ። ከፍ ሲሉም በግል ብንቀሳቀስ ይሻላል በማለት ላይ ታች ሲሉ ከርመዋል። ከዓመታት በፊት አስቀድመው የዳቦ ቤት ንግዱን ሲያከናውኑ የቆዩት ወንድማማቾች በሃገራችን  ያልተሰራ ምን አለ ብለው ቆም ብለው ማሰብ ጀመሩ ።
 መኪናዎች በድንገት በመንገድ ላይ ሲበላሹ በፍጥነት እርዳታ የሚሰጥ በማይገኝበት በሃገራችን ለአሽከርካሪዎች የሚሆን መላ አልነበረም ቢኖርም ከእንግልት የሚያድንበት አንዳችም ስልት አልነበረም። በባህር ማዶ  አቅንተው የነበሩት ፍፁም እና  ዘካሪያስ ግን  ይህንን እንግልት ለማስቀረት የመንገድ ዳር የመኪና ብልሽት የእርዳታ ሰጪ ድርጅትን ለመፍጠር ተነሱ እናም  ኑሃ የመንገድ ዳር የመኪና  ብልሽት እርዳታ ሰጪ ድርጅትን ፈጠሩ። 1915 ዓ.ም በአሜሪካ ሃገር የተጀመረው ይህ አገልግሎት በሌሎችም ዓለም ሃገራት እንዲሁም በእንዲሁም በእዚው በአህጉራችን አፍሪካም ኬንያ ፣ በደቡብ አፍሪካም ልምዱ ያለ ነው።
 ከ100 ዓመት በሃላ ወደ ሃገራችን አምጥተነዋል። እኛ የፈጠርነው አዲስ ያለውን የመንገድ ፍሰት ችግር ይሄን ችግር ሊቀርፍ የሚችል ምንድነው ብለን ይሄ ነው በውስጣቸን የመጣው ሲልም አክሎ ተናግሮዋል። አንድ ስራ ሲጀመር ከባድ ቢመስልም በሃላ በሂደቱ እየተማሩ ብዙ መለወጥ እንደሚቻል ያምኑ ነበር።
ዘመኑ ቲክኖሎጂ ያደገበት እንደመሆኑ መጠን የመኪና የመኪና መንገድ ዳር ብልሽት  የሚያመጣውን እንግልት ለማስቀረት ይህን ተቋም እውን ለማድረግ በርካታ ትግሎችን አድርገዋል። የፊልድ መካኒኮች በየአቅራቢያው መኖራቸውን የሚገልጡት መስራቾች በአዲስ አበባ በሁሉም ክፍለ ከተሞች አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን መተግበሪያውን ከplay store በማውረድ ወይም በአጭር የመስመር ቁጥራቸው 6516 ላይ በሚጠሩበት ሰዓት መካኒኮቹ ፈጣን አገልግሎት እንደሚሰጡ ተናግረዋል። የክፍያ ሂደቱም በወር 275ብር በ ሶስት ወር 825 በስድስት ወር 1500 ብር እና በአንድ አመት 3,000 ብር ጥቅል እንዳላቸው ከመስራቹ አንዱ የሆነው ነብዩ ዘካሪያስ ተናግሩዋል።
  በስራ አለም ውስጥ ማንኛውም ከባድ ነገር በትዕግስት ካለፉት የሚቻል ነው ብለው ያምናሉ። የመንገድ ፍልሰቱን ሚዛናዊ የሚያደርገው የኑሃ ፕሮጀክት ባሳለፍነው መጋቢት 20/2015 በተመረቀበት እለት አትሌት ሀይሌ ገ/ስላሴን ጨምሮ ታላላቅ እንግዶች ታድመው የወጣቶቹን ጥረት አድንቀዋል። ኢ/ር አሰፋ መዝገቡ በመንገድ ደህንነት ዙሪያ የሰሩ ባለሙያ ሲሆኑ የኑሃ ሰዎችንም በማማከር ሙያዊ እውቀታቸውን አካፍለዋል። ኢንስፔክተሩም አንድ ተሽከርከሪ መንገድ ላይ ቆሞ ረጅም ጊዜ ሲቆይ አደጋ ማስከተሉ የማይቀር መሆኑን ገልጠው አገልግሎቱ እጅግ ጠቀሜታ ያለው መፍትሄ አምጪ ነው ብለዋል።
በሌሎች ሃገራት ኢንሹራንሶች በፕራይም ጥቅላቸው ውስጥ በማካተት ሰዎች አገልግሎቱን የሚያገኙበትን መንገድ እንደሚያመቻቹ የሚገልጠው ነብዩ ይሄንን ካየን በሃላ ወደ እኛ ሃገር በማምጣት እርሱንም አርቅቀን በምን መንገድ መሆን እንዳለበት ከውንድሜ ጋር ተወያይተን ከጨረስን በሃላ መተግበሪያውን ለማበልጠግ ስድስት ወር ገደማ አቆይቶናል ሲል ገልጠዋል።
በዚህ አምስት አመት ውስጥ ከአዲስ አበባ ውጪ ባሉ ከተሞች እና በሌሎች ክልል ከተሞች እንደሚስፋፋ እንዲሁም ደግሞ ከሁለት ወር በሃላ ሌላ ይፋ የሚያደርጉት የስራ ዘርፍ እንዳለ ገልጠዋል።

Read 1406 times