Saturday, 08 April 2023 19:35

‹‹አዲስ አበባን ለማወቅ እሮጣለሁ›› ታላቅ የጎዳና ላይ ሩጫ ሊካሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 አዲስ አበባ ከተማን ለማስተዋወቅ ያለመና ከከተማ አስተዳደሩ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በትብብር የተዘጋጀ የጎዳና ላይ ሩጫ ሊካሄድ ነው፡፡ሚያዝያ 16/2015 ዓ.ም የሚካሄደውና ኤም ጆይስ ኢቨንትስት ማርኬቲንግ ከአሀዱ ግሎባል ኔትወርክ ጋር ያዘጋጀው ይኸው የጎዳ ላይ ሩጫ በርካታ፤ ጉዳዮችን ያካተተ ሲሆን የረመዳንን ፆም ምክንያት በማድረግ የአስር ቀና የአፍጥር ግብዣ፤ ፋሲካን በማስመልከት የምሳ ግብዣ እንዲሁም የጎዳ ላይ ሩጫና የተለያዩ የመዝናኛ ፕሮግራሞች መዘጋጀታቸውን ዛሬ አዘጋጆቹ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል። በመስቀል አደባባይ ተጀምሮ እዚያው መስቀል አደባባይ በሚያበቃው የአምስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ከ20ሺ እስከ 30ሺ ሰው ይሳተፍበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Read 1590 times