Saturday, 08 April 2023 19:31

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በቻይና ለሚካሄደው የመጨረሻዙር የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር አለፉ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በየዓመቱ ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የሚዘጋጀው ባለፈው ኖቨምበር 11 ቀን 2022 በተጀመረው ዓለማቀፍ የሁዋዌ አይሲቲ (ICT) ውድድር ከ1500 በላይ ተማሪዎች መሳተፋቸውንና ስድስት ተማሪዎች  በቻይና ለሚካሄደው የመጨረሻ ዙር ውድድር ማለፋቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በኢትዮጵያ ለ7ኛ ጊዜ በተካሄደው የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት ከ1500 በላይ ተማሪዎች ተመዝግበው በኦንላይን የተሰጠውን የመጀመሪያ ፈተና መውሰዳቸውን ሁዋዌ በላከው መግለጫ  አስታውሷል፡፡
ከእነዚህም መካከል 63 ተማሪዎች ፈተናውን አልፈው ከት/ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በተዘጋጀውና ዲሴምበር 28 ቀን 2022 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው አገር አቀፍ የአይሲቲ ውድድር ላይ የተሳተፉ ሲሆን 15 ያህሉ ለቀጣዩ ክልላዊ የአይሲቲ ፈተና ማለፋቸውን ኩባንያው አመልክቷል፡፡ እነዚህም 15 ተማሪዎች ማርች 22 ቀን 2023 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሁዋዌ ኢትዮጵያ ዋና መ/ቤት የተሰጠውንና ለስድስት ሰዓት የዘለቀውን የአይሲቲ ኦንላይ ፈተና   ወስደዋል።በውጤቱም ከጎንደር ዩኒቨርስቲ፣ ከዋቻሞ ዩኒቨርስቲ፣ ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ እንዲሁም ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርስቲ 6 ተማሪዎች ፈተናውን አልፈው ወደ መጨረሻ ዙር የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር ማለፋቸው ተገልጿል፡፡ እነዚህም ተማሪዎ ዘንድሮ በቻይና በሚካሄደው የመጨረሻው የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር ኢትዮጵያን ወክለው ይሳተፋሉ።እ.ኤ.አ ከ2015 ዓ.ም ወዲህ የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር ተፅእኖ እያደገ መምጣቱን ያመለከተው ኩባንያው፤ በ2022 የተካሄደው 6ኛው የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር ከ85 አገራትና ክልሎች የተውጣጡ 150 ሺ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ማሳተፉን  አስታውሷል፡፡

Read 1607 times