Saturday, 01 April 2023 20:45

ከሶሻል ሚዲያ በጨረፍታ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ለህሊናቸው “ምን ሥንሰራ ውለን መጣን” ብለው ይነግሩት ይሆን ?
                        ቴዎድርስ ተ/አረጋይ

       እያንዳንዳችን የብቻችን ሰዓት አለን። ማታ ቤት ገብተን በጀርባችን ተንጋለን ስለ ውሏችን፣ ድካማችን፣ ደስታችን፣ ሀዘናችን ለአፍታም ቢሆን የምናስብበት ቅጽበት አለን። በዚያች ቅጽበት መንፈሳዊነት ካለን ከአምላካችን፣ ኢ - አማኒም ከሆንን ከህሊናችን ጋር እንገናኛለን። ከራሳችን ጋር ጥያቄና መልስ እናደርጋለን። እነዚህ የስራ ጠባያቸው ቤት ማፍረስ የሆኑ ወንድሞቻችን፣ ማታ ደክሟቸው ቤታቸው ገብተው አረፍ ሲሉ ምን ያስቡ ይሆን? ለሚስታቸው ፣ለልጃቸው ወይም ለህሊናቸው “ምን ስንሰራ ውለን መጣን” ይሉ ይሆን? የንጹሀንን ቤት ስናፈርስ? ቤታቸውን የሚያፈርሱባቸውና ንብረታቸውን የሚያወድሙባቸውን ዜጎች ዓይን ሲያዩ ምን ይሰማቸው ይሆን ? የሰውን ተስፋ የመስበርን ስሜት እንዴት ይቋቋሙት ይሆን ? ለአምላክም ለሰውም ይቅር፣ ለህሊናቸው ምን ብለው ነው የሚነግሩት? “ሥራ ነው” ነው የሚሉት? የሰዎችን ሀዘን ከማየት በላይ፣ የሀዘናቸው ምንጭ መሆን ምን ያህል መራር እጣ ፈንታ ነው ?


Read 1424 times