Saturday, 01 April 2023 20:25

The Big Art Sale ዓውደ ርዕይ በመጪው ሳምንት ለ18ኛ ጊዜ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በጥበብ አፍቃሪያኑና በጥበበኛው ዘንድ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠበቀው ’The Big Art Sale’ ዓውደ ርዕይ በመጪው ሳምንት ለ18ኛ ጊዜ ሊካሄድ መሆኑ ተገለፀ።
በዘንድሮው ታላቅ የሥዕል አውደ ርዕይ ላይ ከ5ሺ በላይ ጎብኚዎች እንደሚታደሙ ይጠበቃል ተብሏል።
 ’The Big Art Sale’ ተወዳጅ ከሆኑ የከተማችን የሥነጥበብ  ዝግጅቶች አንዱ መሆኑን የጠቀሰው አዘጋጁ “ዋትስ አውት አዲስ”፤ከሒልተን ሆቴል ጋር በመተባበር በዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄድ የጥበብ ዓውደ ርዕይ መሆኑን ጠቁሟል፡፡
የዘንድሮው አውደ ርዕይ እንደተለመደው በሒልተን አዲስ በመጪው ቅዳሜ መጋቢት 30 እና እሁድ ሚያዝያ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ እንደሚካሄድ ያስታወቀው አዘጋጁ፤በአውደ ርዕዩ ከ100 በላይ ሰዓሊያንና ቀራፂያን አዳዲስ ሥራዎቻቸውን ለጎብኚዎችና ለገዢዎች ያቀርባሉ ብሏል፡፡
ከጥበብ ስራዎች በተጨማሪ ጥበብ አፍቃሪያኑ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የሚዝናኑባቸው የመጠጥና የምግብ ኮርነሮች ሲኖሩ፤ለልጆች ልዩ የመጫወቻ ሥፍራም ተዘጋጅቶ ይጠብቃቸዋል ተብሏል፡፡ ይህ ልዩ ዓውደ ርዕይ ጠቢብያኑ ሥራቸውን እንዲሸጡ እድል የሚሰጣቸው ሲሆን ገቢውም  ለበጎ አድራጎት ሥራዎች እንደሚውል ተጠቁሟል።  


Read 5421 times