Saturday, 01 April 2023 19:49

‹‹ዓምና ኢትዮጵያ ውስጥ ከዩክሬን የከፋ ግድያና ግጭት ተፈፅሟል›› አምነስቲ ኢንተርናሽል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ለተገደሉበት ግጭት ዓለማቀፍ ተቋማት በቂ ምላሽ አልሰጡም ሲል ወቅሷል፡፡
       ባለፈው ዓመት በዓመት የጦር ወንጀል ከተፈፀመባቸው 20 አገራት አንዷ ኢትዮጵያ ናት ብሏል፡፡
               አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የአለም አገራትን የሰብአዊ መብት አያያዝ የሚፈተሽበትን ዓመታዊ ሪፖርቱን ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ ድርጅቱ በዚሁ ሪፖርቱ ባለፈው የፈረንጅ ዓመት በዓለማችን ከተፈፀሙ ግጭቶች እጅግ አስከፊውና ገዳዩ የተፈፀመው በዩክሬን ሳይሆን በኢትዮጵያ ነው ብሏል። ይህ በአገሪቱ የተፈፀመው ዘግናኝ በደል የተፈፀመውም ከአለም የትኩረት  አቅጣጫ ውጪ ነው ሲልም አምነሲት ጠቁሟል። አመልክቷል።
ከትናንት በስቲያ ይፋ በተደረገው በዚሁ የድርጅቱ አመታዊ ሪፖርት ላይ እንደተመለከተው ያለፈው የፈረንጆች አመት በአለም ዙሪያ እጅግ ዘግናኝ ግድያዎች የተፈፀሙበት ዝርፊያዎች፣ ፆታዊ ጥቃቶችና፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች የተፈፀሙበት አመት ነበር። ድርጅቱ በተለይ በኢትዮጵያ ተፈፀሙ ያላቸውን የግፍ ግድያዎች ህገ-ወጥ እስሮችና መልከ ብዙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የዘረዘረ ሲሆን እነዚህ የጦር ወንጀሎችና የግፋ ግድያዎች በአለማችን እጅግ ከባድ ተብለው ከሚጠቀሱት የሩሲያና ዩክሬን ጦርነትም የከፋ ነው ብሏል። ባለፈው የፈረንጆች አመት እጅግ ገዳዩ ግጭት የተፈፀመው ዩክሬን ሳይሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ብሏል ሪፖርቱ። በዚህ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ለተገደሉበት ግጭት አለማቀፍ ተቋማት ሰጡት ምላሽ በቂ አለመሆኑንም በሪፖርቱ አመልክቷል።
አሚኒስቲ ኢንተርናሽናል ሰሞኑን ይፋ ባደረገውና ባለፈው የአውሮፓውያን አመት በአለም ላይ በተከሰቱ ግጭቶችና ተቃውሞዎች ላይ ትኩረቱን ባደረገው በዚሁ ሪፖርቱ በኢትዮጵያ በሰሜኑ ክፍል በተካሄደው ጦርነትና በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በተቀሰቀሱ ተቃውሞዎች ምክንያት በርካታ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ተፈፅመዋል ብሏል።
ድርጅቱ ጥናት ካካሄደባቸው 156 አገራት መካከል በሃያዎቹ የጦር ወንጀሎችን ጨምሮ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መፈፀማቸውን ያመለከተው የድርጅቱ ሪፖርት በ79 አገራት ደግሞ ሃሳብን በነፃነት በሚገልፁ መብት ተሟጋቾችና አንቂዎች ላይ እስር ድብደባና በደል ተፈፅሞባቸዋል ብሏል። ባለፉት ሁለት ዓመታት በሰሜኑ አገራችን ክፍል የተካሄደውን ጦርነት በአለማችን ከተካሄዱ አውዳሚ ጦርነቶች መካከል አንዱ ነው ያለው የድርጅቱ አመታዊ ሪፖርት በጦርነቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል። ሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈፅሟል። ጦርነቱ በተካሄደባቸው በትግራይ፣ አማራና አፋር ክልል ውስጥ የሚኖሩ ከ8.35 ሚሊዮን በላይ ዜጎች እርዳታ ጠባቂ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል ብሏል።
አለም አቀፍ እርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ለግጭቱ የሰጡት ምላሽ በቂ አይደለም ሲልም ወቅሷል።አለም አቀፍ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ድርጅት ይፋ ባደረገው በዚሁ አመታዊ የአለም የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሪፖርት በኢትዮጵያ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት በከፍተኛ ሁኔታ መሸርሸሩንና ባለሞያዎች ታስረው እንደሚገኙ አመልክቷል።


Read 1353 times