Saturday, 26 November 2022 00:00

“በአገራችን 37 በመቶ ሕፃናት የመቀንጨር ችግር አለባቸው”

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  ከሽንብራ ዱቄትና ከተለያዩ የምግብ ግብአቶች የሚዘጋጅ ብስኩት መመረት ጀመረ

       በአገራችን የመቀንጨር አደጋ 37 በመቶ የደረሰ ምጣኔ ያለው ሲሆን ችግሩ በስፋት የሚታየው ዕድሜያቸው ከአምስት አመት በታች በሆኑ ህጻናት ላይ እንደሆነ ተገለፀ። ይህ የተገለጸው ለህጻናት አካላዊና አዕምሮአዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል የተባለና ከሽንብራ ዱቄትና ከተለያዩ የምግብ ግብአቶች የሚዘጋጅ ብስኩት መመረት መጀመሩ ይፋ በተደረገበት መርሃግብር  ላይ ነው።
መሰረቱን በዴንማርክ ያደረገውና በልማትና እርዳታ ላይ አተኩሮ በአገራችን በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በአፋርና በጋምቤላ ክልሎች ውስጥ በስፋት የሚንቀሳቀሰው “Dan Church Aid (DCA)” ህፃናትና እናቶች ላይ ትኩረት ባደረገውና “Sustianable Food partnership for better Nutrition through inclusive value chain in Ethiopia (SFP)” በተሰኘው ፕሮጀክቱ፣ በሞያ የምግብ ኮምፕሌክስ መመረት የጀመረው ሰኒ ብስኩት፤ ህፃናትን ለመቀንጨር ችግር የሚዳርጋቸውን የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ለመቅረፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሏል።
ይህ ለህጻናት እድገት አስፈላጊ በሆኑ የምግብ ግብዓቶች ተመርቶ የቀረበው ብስኩት፤ በአገራችን በተለይም ችግሩ ባለባቸው አካባቢዎች ላይ በስፋት ለማዳረስ ጥረት እንደሚደረግም በዚሁ ዝግጅት ላይ ተገልጿል።

Read 8551 times