Saturday, 24 September 2022 17:00

ስማርት ፊልም ዓለማቀፍ የፊልም ፌስቲቫል በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 በስማርት ስልክ የተቀረጸው የሙሉ ጊዜ ፊልም ለዕይታ ይበቃል


        ሁሉም የፊልም እንዲሁም የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች የራሳቸውን ተረክ በስማርት ስልኮች በመሰነድና በማዘጋጀት ለዕይታ ማብቃት የሚችሉበትን ዓለማቀፍ መድረክ መፍጠርን ዓላማው ያደረገው ስማርት ፊልም ፌስቲቫል፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ አዘጋጅነት በአዲስ አበባ እየተካሄደ እንደሚገኝ ተገለጸ።
በትላንትናው ዕለት  በሃያት ሬጀንሲ ሜትሮ በተከፈተውና ዛሬም በሚቀጥለው  በዚህ ስማርት ፊልም ፌስቲቫል ላይ አጫጭር ፊልሞች  ለዕይታ የሚቀርቡ ሲሆን የፓናል ውይይትም ይካሄዳል ተብሏል።
በፌስቲቫሉ  ላይ ኦውታፕ የተሰኘ ለጥበብ ሥራ ፈጣሪዎች የበለጠ ክህሎት በመስጠት ለተሻለ ደረጃ የሚያበቃ ፕሮግራም ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚተዋወቅና የስማርት ፊልም የሽልማት ስነ-ስርዓት እንደሚከናወን ታውቋል።
የፌስቲቫሉ አዘጋጆች ለአዲስ አድማስ በላኩት መግለጫ እንዳመለከቱት፤ ትላንት ዛሬ እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ ፌስቲቫል፤ ከጠዋቱ 4 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት የተለያዩ አጫጭር ፊልሞች ለታዳሚ የሚቀርቡ ሲሆን የፓናል ውይይቶችም ይካሄዳሉ።
ከዚህ በተጨማሪም ለመጀመሪያ ጊዜ በስማርት ስዕልክየተቀረጸው የሙሉ ጊዜ ፊልም ለዕይታ የሚበቃ ሲሆን አዘጋጁ ሃሳባቸውን እንደሚገሩም ተጠቁሟል።
ፌስቲቫሉን ዘሌማን ኮሚዩኒኬሽንስ፤ ከስማርት ፊልም ፌስት፣ ፍሎውለስ ኢቨንትስ እና ሃያት ሬጀንሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው መሆኑ ታውቋል።


Read 11099 times