Tuesday, 16 August 2022 07:39

ኮሮናን በቤት ውስጥ ለመመርመር የሚያስችል መሳሪያ በገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአገራችን የተመረተና የኮቪድ 19 በሽታን በቤት ውስጥ ለመመርመር የሚያስችል መሳሪያ ገበያ ላይ የዋለ ሲሆን መሳሪያው የመድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን እውቅናና ፍቃድ የተሰጠው መሆኑም ተገልጿል፡፡
ጥሬ ዕቃዎችን ከአሜሪካ በማስመጣት ምርቱን በአገራችን እያመረተ ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ገበያዎች በማቅረብ ላይ የሚገኘው “Access bio inc” ትናንት ምርቶቹን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
የኮቪድ 19 በሽታን በቤት ውስጥ ለመመርመር ያስችላል የተባለውና “care start የሚል ስያሜ የተሰጠው መሳሪያው በ10 ደቂቃ ውስጥ ውጤቱን ለማወቅ የሚያስችል ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኙ ፋርማሲዎች ለገበያ ቀርቧል ተብሏል፡፡
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በአሁኑ ወቅት በአለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ መጠን እየጨመረ መሆኑን ያመለከቱት የ“አክሰስ ባዮ ኢንክ” የስራ ኃላፊዎች፤ በአገራችንም በበሽታው ተይዘውና ፅኑ ህሙማን ክፍል የሚገቡና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መሆኑን አስታውቀዋል። ህብረተሰቡ በበሽታው መያዝ አለመያዙን ለማወቅ በቀላሉ በፋርማሲዎች በሚያገኛቸው “care start” የመመርመሪያ መሳሪያዎች እራሱን በመመርመር ማረጋገጥ እንደሚችል ተገልጿል፡፡
አክስስ ባዩ ኩባያው ከዚህ ቀድም የወባ መመርመሪያን መሳሪያዎች ወደ ህንድና የተለያዩ የአፍሪካ አገራት በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማስገኘቱን ያስታወሱት የድርጁቱ የስራ ኃላፊዎች፤ አሁን ደግሞ ይህንኑ ቤት ለቤት የኮቪድ 19 በሽታን ለመመርመር የሚያስችል መሳሪያ እያመረተ ወደ ውጭ አገር በመላክ፣ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኝ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

Read 7259 times