Saturday, 18 June 2022 20:35

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

ይችን ጨቅላ መጽሐፍ፣ የምታነቡ ሁሉ
አደራ ስለኔ፣ ማሪያም ማሪያም በሉ።
ከሆዴ ያለውን፣ የትምርት ሽል
ያለጭንቅ እንድወልድ፣ እድገላገል
ከሃያ ስድስቱ፣ ወንዶች ፊደላት
አርግዣለሁና መዝገበ-ቃላት።
ስንት እልፍ አበው ናቸው፣ አርግዘው
የሞቱ
ቀኝ እጃቸው አጥሮ፣ ፊደል በማጣቱ!
ለትምክህት አይደለም፣ ይህን መናገሬ
ለማስቀናት-እንጂ፣ ሰነፉን ገበሬ
ሃዋርያው ሲናገር ወደ ምዕመናኑ
ለምትበልጥ ፀጋ ይላል ቅኑ አስቀኑ!
ከሣቴ ብርሃን




___________________________

Read 1601 times