ይችን ጨቅላ መጽሐፍ፣ የምታነቡ ሁሉ
አደራ ስለኔ፣ ማሪያም ማሪያም በሉ።
ከሆዴ ያለውን፣ የትምርት ሽል
ያለጭንቅ እንድወልድ፣ እድገላገል
ከሃያ ስድስቱ፣ ወንዶች ፊደላት
አርግዣለሁና መዝገበ-ቃላት።
ስንት እልፍ አበው ናቸው፣ አርግዘው
የሞቱ
ቀኝ እጃቸው አጥሮ፣ ፊደል በማጣቱ!
ለትምክህት አይደለም፣ ይህን መናገሬ
ለማስቀናት-እንጂ፣ ሰነፉን ገበሬ
ሃዋርያው ሲናገር ወደ ምዕመናኑ
ለምትበልጥ ፀጋ ይላል ቅኑ አስቀኑ!
ከሣቴ ብርሃን
___________________________
Published in
የግጥም ጥግ