Saturday, 18 June 2022 19:58

የሌሊሣ ግርማ አዲስ መጽሐፍ ወጣ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በአጭር ልብወለድ ድርሰቶቹና በሃሳባዊ መጣጥፎቹ የምናውቀው ደራሲ ሌሊሣ ግርማ፣ በአዲስ የልብ-ወለድ መፅሐፍ በድጋሚ መጥቷል።
ሌሊሣ ግርማ ከዚህ ቀደም፣ “የንፋስ ህልም … “አፍሮጋዳ”፣ “መሬት-አየር-ሰማይ”፣ “የሰከረ እውነታ”፣ “እስቲ ሙዚቃ” እና “ነጸብራቅ” በተሰኙ የድርሰት እና የወግ ስብስቦቹ በአንባቢያን ዘንድ ይታወቃል። ብዙ  አድናቂዎችንም አትርፏል፡፡
እነሆ አሁን፣ “ይመስላል ዘላለም” በተሰኘ መፅሐፍ የአጭር ልብ-ወለድ የፈጠራ ድርሰቶች ተከስቷል የክረምቱን የንባብ ጥም ለመቁረጥ በቀረበ የኪነ ጥበብ ድግስ።
ሌሊሣ ግርማ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ከአስራ አምስት ዓመታት በላይ የሥነፅፍ ቤተኛ የኪነ ጥበብ ቤተሰብ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በፍትህ መጽሔት ላይም ለረጅም ጊዜ ጽሁፎቹን ሲያስነብብ ቆይቷል።
“ይመስላል ዘላለም”፣ በ231 ገጽ የተቀነበበ፣ ሰላሳ ገደማ አጭር የፈጠራ ድርሰቶችን የያዘ መጽሐፍ ነው። የመጽሐፉ ዋጋ 250 ብር ሲሆን፣ ዋና አከፋፋይ ጃፋር መጽሐፍት መደብር ነው። ከዛሬ ጀምሮ በገበያ ላይ ይገኛል።


Read 11606 times